Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, April 26, 2015

በጨርቆስ አካባቢ የሚኖሩ ሙስሊም ወጣቶች ሃዘን ለደረሰባቸው ቤተሰቦች የአርባሺህ ብር ድጋፍ አደረጉ




ፍትህ ራዲዬ /ዕለተ ቅዳሜ ሚያዚያ 17/2007
۩○◙◙○◙◙○◙◙○◙◙○۩


በሊቢያ ልጆቻቸው በግፍ የተገደሉባቸውን ኢትዬያውያንን ለማፅናናት የጨርቆስ አካባቢ ሙስሊም ወጣቶች ሃዘን ለደረሰባቸው ቤተሰቦች የ 40.000 ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የፍትህ ራዲዬ ባልደረቦች አስታውቀዋል፡፡

በሊቢያ በግፍ ከተገደሉት ኢትዬጲያውያን ክርስቲያኖች መካከል 5 የሚሆኑት የጨርቆስ አካባቢ ተወላጆች መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን በጨርቆስ አካባቢ የሚኖሩ ሙስሊም ወጣቶችም በሰፈራቸው ወጣቶች ላይ የደረሰውን አሳዛኝ ግድያ በማውግዝ ለቤተሰቦቻቸው የ 40.000 ብር ድጋፍ ማድረጋቸው ተገልፆል፡፡

ሙስሊም ወጣቶቹ በሃገራችን ለረጅም አመታት የቆየውን የመረዳዳት እና የመደጋገፍ ባህላችንን ህያው በማድረግ ኢስላም በመልካም መረዳዳት የሚያዝ መሆኑን በተግባር ለተጎጂ ቤተሰቦች አቅማቸው የፈቀደውን ወጣቶቹ ገንዘብ በማዋጣት አጋርነታቸውን ማሳየታቸው ተዘግቧል፡፡

መንግስት በሊቢያ የተደሉትን ወገኖች ለግሉ የፖለቲካ ፍጆታ በማዋል በሙስሊም እና በክርስቲያኑ መካከል የማየበርድ እልቂት ለምፍጠር ከፍተኛ ቅስቀሳ እያደረገ በሚገኝት በዚህ ወቅት ህዝበ ሙስሊሙ እና ክርስቲኑ ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ መደጋገፉን በማጠናከር በሃዘን እና በደስታ ጊዜ በጋራ አየተረዳዳ ይገኛል፡፡

የጨርቆስ አካባቢ ሙስሊም ወጣቶች ከራሳቸው የሰበሰቡትን 40.000 ብር ለ 5ቱ ተጎጂ ቤተሰቦች ሃዘናቸውን በመግለጽ አላህ መፅናናት እና ብርታቱን እንዲሰጣቸው በመማጸን ገንዘቡን እንዳከፋፈሏቸው ተዘግቧል፡፤

ይህ ድንቅ የአብሮነት እና የመረዳዳት ባህል በመንግስት እኩኝ በሆነ ሰይጣናዊ የፕሮፖጋንዳ የማሸረሸር መሆኑን የጨርቆስ አካባቢ ሙስሊም ወጣቶች በተግባር አሳይተዋል፡፤

የጨርቆስ አካባቢ ሙስሊም ወጣቶች ሃይማኖት ሳይገድባቸው አደጋ ለደረሰባቸው ለክርስቲያን ወገኖች ያደረጉት ድጋፍ ለሁሉም ኢትዬጲያዊ ትልቅ የአብሮነት መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው፡፡

የኢትዬጰያን ህዝብ በእምነት ከፋፍሎ ለማፋጀት የሚደረገው ሴራ አይሳካም!!

አላሁ አክበር!!

80 ኢትዮጵያዊያን በኬንያ ተያዙ



ዳዊት ሰለሞን
ኢትዮጵያዊያኑ በኬንያ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የገቡት ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚያሻግሯቸው ተስፋ በሰጧቸው ደላሎች አማካኝነት እንዲያርፉባት በተደረገች ክፍል ውስጥ ተደራርበው እንደተኙ ነው፡፡
አየሩ በታፈነ ክፍል ውስጥ ታጭቀው የተያዙት ወጣቶች የሚበዙት ከደቡብ ኢትዮጵያ ተነስተው ሞያሌን አቋርጠው ናይሮቢ የደረሱ ነበሩ፡፡ቤተሰቦቻቸው የነበረቻቸውን መሬትና ከብቶቻቸውን ሸጠው፤የገሚሶቹ ተበድረው ጥቂት የማይሰኙት ደግሞ በአዲስ አበባ ጭምር ለዓመታት በጫማ ጠራጊነት ተሰማርተው ያጠራቀሟትን ገንዘብ ለደላሎች በመክፈል ደቡብ አፍሪካን በዓይነ ህሊናቸው እየሳሉ ስጋቸውን ባሳረፉበት ቅጽበት ፖሊሶች ‹‹ወደ አገራችን በህገ ወጥ መንገድ በመግባታችሁ በቁጥጥር ስር ውላችኋል አሏቸው፡፡
በኤልዶሬት አካባቢ የተያዙት 80 ኢትዮጵያዊያን በኢሲኦሎ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም በግዜው አስተርጓሚ ባለመገኘቱ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ከዚህ በፊት በተለያዩ የኬንያ ክፍሎች የተያዙ ኢትዩጵያዊያን በፍርድ ቤቶች በህገ ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ በመግባት የሚል ክስ እየተመሰረተባቸው ከ500-800 ዶላር የሚደርስ የገንዘብ ወይም ከ6 ወር እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ ቅጣት ሲበየንባቸው መቆየቱ ይታወሳል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ሁለት ሰው አዘዋዋሪዎችን በኢንተርፖል አማካኝነት እጃቸውን ይዤ ወደ አገር አስገብቻለሁ ቢልም የወጣቶቹ ፍልሰት አለመቆሙ የሚያሳየው አሁንም የአዘዋዋሪዎቹ መረብ አለመበጠሱን ነው፡፡

"የችግሩ መሰረታዊ ምንጭና መፍትሔው ፓለቲካዊ ነው'!! አቶ ኤርምያስ ለገሰ



መሰረታዊ ምንጭና መፍትሔው ፓለቲካዊ ነው’!!
ሰሞኑን በኢትዬጲያውያን ላይ የመከራ ዶፍ እየዘነበ ነው። ይህ የድቅድቅ ጨለማ ናዳ ባስከተለው አደጋ የተፈጠረው ቁጭትና መብከንከን ከቃላት በላይ ሆኗል። በኢትዬጲያውያን ዘንድ ከዚህ ውጭ የመተከዣ አጀንዳ ያለ አይመስልም። እንባ እንደ ጐርፍ እየወረደ ነው። የእናቶቻችን ደረት በእሳት የተለበለበ እስኪመስል ድረስ እየተደለቀ ነው። ወጣቶቻችን ከአረመኔዎች ጋር ግብግብ እየገጠሙ ነው። በመንገድ፣ በትራንስፓርት፣ በምግብ ቤት፣ በስራና በተለያየ አጋጣሚ የምናገኛቸው የባእድ አገር ሰዎች ሳይቀር የሀዘናችን ተካፋዬች መሆናቸውን እየነገሩን ነው። ነግረውን ብቻ አያቆሙም ። አያይዘው ፣
“ችግሩ ለምን እናንተ ኢትዬጲያውያን ላይ ባሰ?፣ ሀገራችሁን ትታችሁ ስደትን ለምን እንደ አማራጭ ወሰዳችሁ? ለምን እንደ ጨው ዘር ትበተናላችሁ?፣ ሰብሳቢ የላችሁም ወይ? ” የሚል ጥያቄ ያስከትላሉ። የሚገርመው ነገር እንደዚ አይነት ጥያቄ በግለሰብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን እንደተቋምም እየቀረበ ነው። ለዚህ አባባል አብነት የሚሆነኝ ባለፈው አርብ አርቲስት ታማኝ በየነ ያጫወተኝ ወግ ነው። ከእሱ ጋር በፍሎሪዳ ግዛት በነበረን ቆይታ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን / ዩኤን ኤች ሲአር / ጋር እሱና የስራ ባልደረቦቹ በነበራቸው ስብሰባ ያነሱለትን ጥያቄ አንስቶ ነበር ውይይታችን የተጀመረው። ዩኤን ኤች ሲአሮች እንዲህ በማለት ነበር የጠየቁት፣
” እናንተ ኢትዬጲያውያን ሀገራችሁን ጥላችሁ በመሰደድ ተወዳዳሪ የሌላችሁ ሆናችኃል። ሌላው ቀርቶ በኢኮኖሚ አቅሟ ከእናንተ በምንም የማትሻለዋና የተንኮታኮተች ( የደቀቀች) ሀገር ወደ ሆነችው የመን እንዴት ትሰደዳላችሁ? ”
ይህ መሰረታዊ ጥያቄ ነው።እያንዳንዱ ኢትዬጲያዊ ከጊዜያዊ ዋይ ዋይታ ተቆጥቦ ከእኛ የማትሻለውን “የመን” አማትረን የምንመለከትበት ባይነኩላር ለምን እንዳስገጠምን መነጋገር ይኖርብናል። ከፊታችን እየመጣብን ያለው አደጋ ክብደትና አስፈሪነት በግልጵ አውጥተነው ችግሩን መነጋገር ያስፈልጋል።ይህን ማድረግ ካልቻልን ከራሳችን በላይ የምናስቀድማት ” ኢትዬጲያ ሀገራችን” የመኖርና ያለመኖር የህልውና አደጋ ይጋረጥባታል። ርግጡን እንነጋገር ከተባለ አሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት እየፈረስን ነው። የኢትዬጲያ ህዝቦች ላይ የተጠመደ ፈንጂ ለመፈንዳት ጊዜውን እየጠበቀ መሆኑ እየታየ ነው።
ቢያድለን ኖሮ ይህን አጀንዳ መክፈት የነበረበት መንግስት ነበር። ለጵድቅ ሳይሆን ከመንግስት ዋነኛ ሀላፊነቶች አንዱ ዜጐቹን ከውጭ ጥቃት የመከላከልና የህዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ የሚጣልበት በመሆኑ ። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የመንግስትን ትርጉም እንደሚከተለው ገልፀውታል፣
“መንግስት ማለት የአንድን ህዝብ መሰረታዊ አቋሞች ፣ አንድነትና ነጳነት ከውጭ ጠላት የሚከላከል፣ የሕዝቡን ደህንነት ፣ እድገትና መሻሻል የሚመራ ፣ ሕዝቡ ከውስጥ እርስ በእርሱ ያለውን ግንኙነት ፣ መብትና ግዴታ በሕግና በስርአት እየወሰነ የስልጣን ባለአደራ ሆኖ የሚያስተዳድር ድርጅት ነው” በማለት ። ” መንግስታችን!” ፕሮፌሰሩ ባስቀመጡት ሁሉም መስፈርት በዜሮ ተባዝቷል። ይህም የውርደታችን ምንጭ ሆኗል። የባእዳን ማላገጫና አፍ መፍቻ ሆነናል።
ትላንት የውጭ ዜጐችን በስብሰባ፣ በትምህርት… ወዘተ ባገኘን ቁጥር ” ሉሲን ታውቃታለህ?፣ አስራ ሶስት ወር ሙሉ የፀሀይ ብርሀን ፀጋ እንዳለን ታውቃለህ?፣ ከአፍሪካ ሀገሮች በቀኝ ግዛት ያልተያዝነው እኛ እንደሆንን ይገባሀል? ” በማለት ደረታችንን ነፍተን እንናገር ነበር። ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ ይህን ማስታወሻ ስጵፍ አንድ ሁልጊዜም የማልረሳው ታሪክ አስታወሰኝ። ታሪኩ እንዲህ ነበር፣
በ1993 አ•ም• በአዲሳአባ ምክርቤት አዳራሽ በኢህአዴግ / ህውሀት የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ ላይ ውይይት እያደረግን ነበር። የእለቱ ውይይት በፓሊሲው መግቢያ ላይ ባለው ” ብሔራዊ ውርደት” በሚለው ርእስ ላይ ነበር። በጉዳዩ ላይ አስተያየት ለመስጠት እጁን ያነሳው በወቅቱ የኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ፕሬዝዳንት የነበረው ዶክተር ዘሪሁን ነበር። በአንድ የውጭ ኮንፍረንስ ላይ ጥናታዊ ጵሁፍ ሊያቀርብ ያጋጠመውን ነበር የነገረን። ዶክተር ዘሪሁን እንደ መንደርደሪያ ” ሉሲ፣ አስራ ሶስት ወር፣ በኮለኒ ያልተያዘች…ወዘተ” እያለ ሲደሰኩር የአንድ አፍሪካዊ እጅ ይቀሰራል። አፍሪካዊው ፍቃድ ሳይጠይቅ ” ዶክተር ለምን ጨምረህ መዝገበ ቃላት “ቸነፈር” የሚለውን ሲያብራራ ኢትዬጲያን እንደ ምሳሌ ማንሳቱን አትነግረንም?፣ …ለምን ሀገራችሁ የሟሸሸ መንግስታት በመሆኗ እንደ ሀገር መቀጠል እንዳቃታችሁ አትነግረንም?፣… ለምን በዘርና በጐሳ ተከፋፍላችሁ እንደምትኖሩ አትነግረንም?…ለምን ህዳጣን ብዙሀኑን እየገዙ መሆኑን አትነግረንም… ወዘተ ” በማለት በጥያቄ ያፋጥጠዋል። ኬሚስቱ ዶክተር ዘሪሁን በወቅቱ የሚመልሰው መልስ አልነበረውም። ጥያቄው አናሊቲካል ወይም ባዬ-ኬምስትሪ አልነበረምና!!
ዛሬም ይህ ኢትዬጲያ መሬት ላይ ያለ ሀቅ አልተቀየረም። እየባሰበት ሄደ እንጂ!…
በሀገራችን ጥቂቶች የአውሮፓና የአረብ ቅምጥል የሚኖረውን ኑሮ እየኖሩ፣ ብዙሀን በችጋር እየተገረፋ ነው።… በሀገራችን ጥቂቶች ልጆቻቸውን በአሜሪካን ሀገር በሚገኙ እጅግ ውድ ዩንቨርስቲዎች በዶላር እያስተማሩ ( የአራት ጀነራል ልጆች በጆርጅ ታወን ዩንቨርስቲ ያስተምራሉ)፣ ብዙሀን ልጁን የሚያበላው አጥቶ ከትምህርት ቤት ያስቀራል።…ጥቂቶች ባል ሜጀር ጀነራል፣ ሚስት ኮረኔል፣ ልጅ ፓይለት የመሆን እድል ይመቻችለታል፣ ብዙሀኑ “ድንጋይ ማነጠፍ ” ለመስራት አሊያም ” አፍራሽ ግብረሀይል” በቀበሌ ለመቀጠር ቦታ የለንም ይባላል።…በሀገራችን ጥቂቶች የለውጥ ውቅያኖስ ገብተው የሀብት ጋራ እንዲቆናጠጡ ይደረጋል፣ ብዙሀኑ በአፍአዊ ለውጥና ከንቱ ተስፋ እንዲሞሉ ይደረጋል። …ጥቂቶች የህሊና እምብርት ሳይበጅላቸው የሀገር ሀብት ወደ ውጭ ያወጣሉ ( በዚህ አመት ከአፍሪካ ተሰርቆ ከወጣው ቢሊዬን ዶላር ውስጥ 28•5% ከኢትዬጲያ መሆኑን ልብ ይሏል)፣ ብዙሀን በአፍሪካ ጫካ የአውሬ ራት ይሆናሉ…በሰሀራ በረሀ እንደ ሎጥ ሚስት ደርቀው ይቀራሉ… በአረብ ሀገራት እንዳበደ ውሻ ይክለፈለፋሉ ( የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል እንደወረደ!)…ጐማ ተጠቅልሎባቸው በእሳት ይጋያሉ…እንደ ዶሮ አንገታቸው ተቀንጥሶ ይጣላሉ።
ወደድንም ጠላንም የዚህ ሁሉ አቢይ መንስኤ ፓለቲካዊ ነው። የፓለቲካው መበላሸት የፈጠረው ችግር! የውስጣዊ አድልዎ ፓሊሲ የፈጠረው ችግር !…እውነት እንነጋገር ከተባለ በአድሎዋዊው ፓሊሲ ምክንያት እኩል የመማር፣ የመስራት፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች የማግኘት እድል የለም። የፓለቲካው መበላሸት የህግ ልእልና እንዳይሰፍን አድርጓል። የህግ ልእልና ባለመስፈኑ ምክንያት ደግሞ ሀሳብን በነጳነት የመግለጵ፣ የመደራጀትና በሰላም ወጥቶ የመግባት መሰረታዊ መብት ዝግ ሆኗል። የህግ የበላይነት ባለመኖሩ ሁሉም የሀይማኖት ተቋማት በጣልቃ ገብነት እየታመሱ ይገኛሉ። በዚህም ሳይወሰን የእምነት ተቋማቱ በካድሬ ተጵእኖ በመውደቃቸው ምክንያት የእምነት ነጳነት ከስም የማያልፍ ሆኗል።
ከውስጣዊው የአድሎ ፓሊሲ ባልተናነሰ የውጭ ፓሊሲያችንም “መርህ አልባ” መሆን እና ” ጠላት ሳትፈጥር አትኑር! ” የሚለው የመለስ አስተምህሮ ለችግራችን መባባስ አስተዋጵኦ አበርክቷል። በሱማሊያ የተወሰደው የጣልቃ ገብነት እርምጃ የሳጥናኤል ጭንቅላት የተገጠመላቸው የሰው ዘር ባልሆኑት አይሲሶች ጥርስ እንዳስገባን የአደባባይ ሚስጥር ነው። በህዳር 21 ቀን 1999 አ•ም• ወደ ሱማሊያ ስንገባ አቶ መለስ ፣” ወቅታዊና ተጨባጭ የሉአላዊነት አደጋ ገጥሞናል። በኢትዬጲያ ላይ የጅሀድ ጦርነት ታውጇል ። ይህን ወቅታዊና ተጨባጭ አደጋ በአጭር ጊዜ ቀልብሰን ወደ ልማታችን እንመለሳለን” የሚል ነጋሪት በፓርላማ ጐስሞ ነበር። “ቀስ ብለን እናጢነው”፣ ” በኃላ ማጠፊያው እንዳያጥረን” ” የራሷ አሮባት የሌላውን ታማስላለች እንዳይሆንብን” እያሉ ተማጵእኖ ያሰሙትን አንጋፋ ፓለቲከኞች ( ዶክተር በየነ፣ ዶክተር መራራ፣ አቶ ቡልቻ…) ” የኢትዬጲያን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፈው የሰጡ ከሀዲዎች፣ የሻእቢያ ተላላኪዎች” የሚል መልእክት ቀርፀን አብጠልጥለናል። ሰፋፊ መድረኮች ከፍተን ከፍ ዝቅ አድርገናል። እውነታው ግን የሱማሊያ ችግር እንኳን በአጭር ጊዜ ሊፈታ የኢትዬጲያ ወታደሮች ሱማሊያን ለቀው ሳይወጡ አስርተ አመት ሊደፍኑ አንድ አመት ብቻ ቀርቶአል። ውጤቱም ወንድሞቻችን በሰው በላ የዲያብሎስ መልእክተኛ በሆኑ አይሲሶች አንገታቸው መቀላት ሆኗል። የራሳችን አሮ የሌላውን እያማሰልን ነው!!

ሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ ፖስተሮች በገዥው ፓርቲ እየተቀደዱብኝ ነው ሲል ገለጸ





ሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ ፖስተሮች በገዥው ፓርቲ እየተቀደዱብኝ ነው ሲል ገለጸ

• ‹‹ወንብድና ነግሷል›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ

የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተሮች በገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ሆን ተብለው እየተቀደዱበት እንደሆነ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለፀ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የለጠፋቸው ፖስተሮችን የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች እየተከታተሉ እንደቀደዷቸውና ላያቸው ላይ ማስታወቂያ እንዲለጠፍባቸው እየተደረገ መሆኑን አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡


‹‹ፖስተሮቹ የተቀደዱት አንድ ቦታ ላይ አይደለም፡፡ በአሁኑ ወቅት ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ እያደረገ የሚገኘው ገዥው ፓርቲ ሆን ብሎ እየተከታተለ እያስነሳ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ የሰማያዊ ፖስተሮች ሲቀደዱ የኢህአዴግ ፖስተሮች ላይ ግን ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም፡፡ ይህ ከፍርሃቱ የመነጨ ነው›› ያለው አቶ ዮናታን ተስፋዬ የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሰማያዊ ፓርቲን ፖስተሮች እየቀደዱ ከህዝብ እንዳይደርስ ለማድረግ ቢጥሩም በህዝቡ ትብብር አማራጫቸውን በማቅረብ ላይ በመሆናቸው ገዥው ፓርቲ ባሰበው መልኩ እንቅፋት መፍጠር እንዳልቻለ አስታውቋል፡፡

‹‹ውንብድና ነግሷል›› ያለው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ሆኖም ሰማያዊ ይህን የገዥው ፓርቲ ህገ ወጥነት በሞራል የበላይነት እና ከህዝብ ጋር በመተባበር እስከመጨረሻው ድረስ ለህዝብ እንደሚያጋልጥ ገልጾአል፡፡ የገዥውን ፓርቲ ድርጊት ሰማያዊ ፓርቲ ለምርጫ ቦርድም እንደሚያሳውቅ የገለጸው አቶ ዮናታን ፓርቲው ይህን የሚያደርግው ሂደቱን ለመጠበቅና የትግሉ አንድ አካል በመሆኑ እንጅ ምርጫ ቦርድ በጉዳዩ ላይ መፍትሄ ይሰጣል ብለን አይደለም ብሏል፡፡
አቶ ዮናታን አክሎም ‹‹ኢህአዴግ ወደ ህዝብ እንዳንደርስ የቻለውን ሁሉ ሊያደርግ ይችላል፡፡ በቀጣይነትም የዕጩዎችን ፎቶዎችና ሌሎች ፖስተሮችን ስንለጥፍ እንደሚቀዱ እናውቃለን፡፡ እኛም ወደ ትግሉ ስንገባ ኢህአዴግ እንዲህ አይነት ባህሪ እንዳለው ስለምናውቅ ይበልጡን ትግላችን እናጠናክራለን እንጅ ወደኋላ አንልም፡፡ እሱ 20 ፖስተሮችን ሲቀድ እኛ 40 ፖስተሮችን እየለጠፍን ወደ ህዝብ እንደርሳለን፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡

Saturday, April 25, 2015

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሚካደውን ምርጫ አስመልከቶ የተለያዩ አስተያዮችን ሲቀበል ዋለ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሚካደውን ምርጫ አስመልከቶ የተለያዩ አስተያዮችን ሲቀበል ዋለ

ሚያዝያ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህብረቱ የተለያዩ የፖለቲካ እና ሲቪክ ማህበራት መሪዎችን በመጋበዝ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከ4 ሰአት በላይ ውይይት አድርጓል።
የአውሮፓ ህብረት የእንግሊዝ ተወካይ፣ ወ/ሮ ጁሊ ዋርድ፣ በህብረቱ የፖርቱጋል ተወካይ ወ/ሮ አና ጎሜዝ፣ የስዊድኖቹ፣ ሶራያ ፖስትና ቦዲል ሲቢሎስ እንዲሁም የስፔን ተወካይ ሚ/ር ጆርዲ ሴባሲቲያ  እና ሌሎችም የህብረቱ ባለስልጣናት በውይይቱ ላይ ተገኝተዋል።
“ካርቶን ዲሞክራሲ፣ በኢትዮጵያ የሚታየውን አምባገነን አገዛዝና ምርጫ” በሚል ርዕስ የተካሄደው ውይይት በ3 ክፍሎች ተካሂዷል።
የኦጋዴን ነጻነት ግንባር፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር፣ የአርበኞች ግንቦት7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ፣ የሲዳማ ነጻነት ንቅናቄ እንዲሁም የአኝዋክ ሰርቫይቫል ተወካዮች በኢህአዴግ የብሄር ፖለቲካ ምክንያት የደረሰውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ዙሪያ አስተያየታቸውን አቅርበዋል።
 

24በህገወጥ መንገድ ሰው አስተላላፊዎች ተያዙ። አንዱ ኢትዮጵያዊ ሃያው ትውልደ ኤርትራ መሆናቸው ታውቋል።




ከተለያዩ አገራት የሚሰደዱትን ወደተሻለ ሥፍራ እናድረሳቸሁዋለን በማለት ህገወጥ የሰው ማስተላለፍ ስራ ሲሰሩ የነበሩ 24 ግለሰቦች ጣሊያን ውስጥ መያዛቸውን EastAfro.com የጣሊያኑን agrigentonotizie.it በApril 20, 2015 ያወጣውን ወደ እንግሊዝኛ ተርጉሞ አቅርቦዋል::


ጋና፤ ጊኒ እና ሽይቮሪ ኮስት የተወለዱ መሆናችወ ከተነገረው ሶስት በስተቀር አንዱ ኢትዮጵያ መወለዱ የተጠቀሰ ሲሆን ሌሎቹ በሙሉ ኤርትራ የተወለዱ መሆናቸውን ዜናው ያስረዳል::

በህገወጥ ሰው አስተላላፊነት፤ ወደ አረብ አገራት በባዶ ተስፋ ሴቶችን በማጋዝ፤ ህጻናትን በጉዲፈቻነት ለአውሮጳውያን "በመሸጥ"፤. . . ኢትዮጵያ ካለው አገዛዝ ጋር እየተሞዳሞዱ ኪሳቸውን ያደለቡ "የዘመኑ ባለጸጎች" በአገር ውስጥ ከህግ በላይ ሆነው እንደሚኖሩ ይታወቃል::

በዜናው ላይ የሰፈሩት ከነስማቸውና ያመኑብት (የተናገሩት) ትውልድ ስፍራቸው እንደሚከተለው ቀርቦዋል:-

Medhanie Yehdego Mered, 34, born in Eritrea;

Ghermay Ermias, born in Ethiopia and lives in Libya, already a fugitive following a previous order for custody;

Asghedom Ghermay , 40, said "Amice", born in Eritrea and domiciled in Catania;

Matywos Melles , 48, was born in Asmara (Eritrea) and resident in Agrigento ;

Mulubrahan gurum, 41, born in Eritrea and domiciled at the CARA Mineo (Catania);

Andemeskel Yaried, 26, alias Wedi Keshi born in Eritrea and already domiciled at the CARA Mineo;

Netsereab Goitom , 36, born in Eritrea and domiciled at the CARA Mineo;

Habtom Teklehaimanot, 41, born in Eritrea, a resident of Foggia, but domiciled in Catania ;

Nahome Kerebel Gutama , 31, said "Nahom", born in Eritrea, a resident of Lecce, but domiciled in Catania;

Afomia Eyasu , 34, born in Eritrea, a resident of Santa Elisabetta (Agrigento) and domiciled in Catania;

Provide Ibrahim Omer , 20, said "Munir", born in Eritrea and domiciled in Catania;

Gebititoys Yonas, 27 years old, born in Eritrea and domiciled at the CARA Mineo;

Fitiwi Negash, 61, born in Eritrea and lives in Catania;

Tsegay Berih , 29, born in Erytheia and domiciled at the CARA Mineo;

Redae Yonas , 29, born in Dekamhare (Erytheia), already domiciled at the CARA Mineo;

Arouna Said Traore , 25, said "Rasta", born Ivory Coast and lives in Catania;

Mohammed Elias , 47, was born in Ghana and is domiciled in Catania,

Ibrahima Diallo , 30, born in Guinea and lives in Catania;

Yirga Abrha , 24, born in Eritrea and domiciled in Bari;

Muktar Hussein, 23, was born in Eritrea and domiciled in Catania;

Andebrahan Tareke , 26, said "andat", born in Ayekebetsu (Eritrea) and lives in Catania;

Efrem Amare , 22, born in Eritrea and domiciled in Milan;

Habte Madege Micheal , 34, said "Miky", born in Eritrea and domiciled in Milan;

Mudeser Mahamed Omer, 20, was born in Eritrea, resident in Mascalucia (Catania) and domiciled in Milan.

በጣሊያንኛ የተዘገበውን ዜና ከነቨዲዮው እዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል::
http://www.agrigentonotizie.it/…/nomi-fermati-operazione-gl…

Friday, April 24, 2015

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ

የአ/አ ገዳማትና አድባራት ሰንበት ት/ቤቶች በዛሬው የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የጸሎተ ፍትሐት ሥነ ሥርዐት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን
‹‹ርትዕት ሃይማኖቶሙ ለቅዱሳን አበዊነ = የአባቶቻችን ሃይማኖት የቀናች ናት›
ራሱን እስላማዊ መንግሥት (አይ ኤስ አይ ኤስ) እያለ የሚጠራው የጨካኝ አረመኔዎች ስብስብ፣ በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ላይ ያካሔደው ዘግናኝ ግድያ ሳይበቃው ይህን እኩይ ድርጊቱን በልዩ ልዩ ምክንያት ከአገር ተሰድደው በሊቢያ በነበሩ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ላይ ፈጽሟል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ‹‹ሃይማኖቱን ገልጦ የማይናገር በክብር የተገለጠ አይኾንም››/ሃይ.አበ. 63÷41/ እንዳለው ‹‹ሃይማኖታችንን አንክድም፤ ማዕተባችንን አንበጥስም›› ባሉ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ላይ ኢሰብአዊነት በተሞላበት ግፍ አንገታቸውን በሰይፍ በመቅላት እና ጭንቅላታቸውን በጥይት በመበታተክ በጭካኔ አገዳደል ገድሏቸዋል፡፡
ይህ ቡድን ከጨካኝ እና አረመኔ የግድያ ድርጊቱ አንጻር የአባላቱን ሰብአዊ ፍጥረት አጠራጣሪ የሚያደርገው ነው፡፡ እጆቻቸው በደም የተሞሉ ናቸው፡፡ ቅዱስ ዳዊት፣ ‹‹የሰውን ደም ለማፍሰስ እግራቸው ፈጣን ነው፤ በመንገዳቸው ኃሣር መከራ አለ፤ የፍቅርን መንገድ አያውቋትም፤ በልቡናቸው እግዚአብሔርን መፍራት የለም፤›› እንዳለው ነው፡፡ መዝ. 13(14)÷1-4፡፡
Addis Ababa sunday school students
ስለኾነም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥር የምንገኝ ሰንበት ት/ቤቶች፡-
  • በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ ክርስትናን በማስገደድ እና በመቀሰጥ ለመለወጥ የሚደረገውን ዘመቻ እና እንቅስቃሴ በጥብቅ እንቃወማለን፡፡
  • ራሱን አይ ኤስ አይ ኤስ ብሎ የሚጠራውን ቡድን ድርጊት በጥብቅ እናወግዛለን፡፡
  • በዚኹ ቡድን እና በቡድኑ የአሸባሪነት ድርጊት ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣቸውን የአቋም መግለጫዎች በሙሉ እንቀበላለን፤ በአፈጻጸሙም እንታዘዛለን፡፡
  • በደቡብ አፍሪቃ በዜጎች እና ሌሎችም ወገኖች ላይ የሚፈጸመውን ጥላቻ እና ዘረኝነት የወለደው ግድያ እና ዘረፋ በጥብቅ እናወግዛለን፡፡
  • በአዲስ አበባ ያሉ ሰንበት ት/ቤቶች ኹሉ መርሐ ግብር በማውጣት በየቤተሰቦቻቸው ቤት በመገኘት ሐዘንተኞችን የሚያጽናኑ ይኾናሉ፡፡
ወደፊትም ኹኔታውን እየተከታተልን የሚጠበቅብንን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መኾናችንን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን፣ በተጋድሎ ላለፉት ወንድሞቻችን ደግሞ ዕረፍተ መንግሥተ ሰማያትን ልዑል እግዚአብሔር እንዲሰጥልን እንለምናለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በሃይማኖታችን ያጽናን፤ ለዓለሙም ሰላም ይስጥልን፤ አሜን፡፡
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

ኢህአዴግ የሞቱትን ወገኖች ክብር እያራከሰ ነው ሲል ሰማያዊ ወቀሰ

ኢህአዴግ የሞቱትን ወገኖች ክብር እያራከሰ ነው ሲል ሰማያዊ ወቀሰ
• ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ጉዳዩን በዝምታ አያልፈውም›› አቶ ዮናታን ተስፈዬ
ኢህአዴግ አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም በሚል በሚጠራቸው ሰልፎች ሰማያዊን በማውገዝ ላይ መጠመዱንና ይህንም ሰማያዊ ፓርቲ በዝምታ እንደማያልፈው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ትናንት ሚያዝያ 15/2007 ዓ.ም በባህርዳር፣ ሆሳና እና ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰልፈኞቹ አይ ኤስን ሳይሆን ሰማያዊ ፓርቲን የሚያወግዙ መፈክሮችን ይዘው እንደወጡ የታወቀ ሲሆን አብዛኛዎቹ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ደም ከማፋሰስ ተግባሩ መቆጠብ አለበት›› የሚሉ መፍክሮችን ይዘው ወጥተዋል፡፡ 
ይህ የሆነው አዲስ አበባ ውስጥ መንግስት የጠራው ሰልፍ ላይ ሰልፈኞች መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ ምልሽ አልወሰደም በሚል ተቃውሞ ካሰሙ በኋላ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ገና ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ ተቃውሞውን ያሰማው ሰማያዊ ፓርቲ ነው ብለው ከወነጀሉ በኋላ ፓርቲያቸው የያዘው አቋም እንደሆነ ኃላፊው ገልጾአል፡፡ አቶ ዮናታን ይህን የኢህአዴግ አቋምም ‹‹እጅግ አሳፋሪና አፀያፊ ነው›› ብሎታል፡፡ የባህርዳርና የሆሳና ሰልፈኞች ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ በያዟቸው መፈክሮች ፊታቸውን እንደሸፈኑ የገለፀው አቶ ዮናታን ሰልፈኞቹ በኢህአዴግ ተገድደው እንጅ አምነውበት እንዳልወጡ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ መስጠት ሲያቅተው የሚነሱበትን ተቃውሞዎች ሰማያዊ ፓርቲና ድምጻችን ይሰማ የፈጠሯቸው አድርጎ መወንጀሉ ለስርዓቱም ሆነ ለሀገሪቱ አደጋ የሚፈጥር ነው ያለው አቶ ዮናታን ለአይ ኤስ አይ ኤስ ተብሎ የተጠራውን ሰልፍ ለራሱ የፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ማዋሉ የሞቱትን ወገኖቻችን ክብር የሚያረክስ፣ ርካሽና ፀያፍ ፕሮፖጋዳ ነው ሲል ወቅሷል፡፡
ኢህአዴግ እንደ መንግስት መስራት ያለበትን ባለመስራቱ የሚነሱበትን ተቃውሞዎች ለመሸፈን እና አጀንዳ ለማስቀየስ ሲል በሰማያዊ ላይ እየፈጠራቸው ያሉትን ውንጀላዎች ፓርቲው በዝምታ እንደማያልፋቸውና ክስ እንደሚመሰርትም አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡


Like · Comment ·  · 611924

የአንድነትና የሠማያዊ ድጋፍ ማህበሮች በሰሜን አሜሪካ አስተባባሪ ኮሚቴ አገዛዙን በጋራ እናሽቀንጥረው አለ


ከሰማያዊና ከአንድነት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች ማህበራት የተሠጠ መግለጫ


በዚህ ባሣለፍነው ሣምንት በኢትዮጵያውያን ላይ በሊቢያና ደቡብ አፍሪካ የደረሰው እጅግ በጣም ዘግናኝ ጭካኔ የጅምላ ግድያ ማለትም በሊቢያ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን ወደ ዕስልምና እንዲቀየሩ ጠይቀዋቸው እምቢ ስላሏቸው ብቻ ግማሾቹን በቢላዋ አንገታቸውን አርደዋቸዋል፡፡ ግማሾቹን ደግሞ በጥይት እራሣቸውን በመምታት ሠላሳ(30) ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን በግፍ አይስል (ISIL) ተብሎ በሚጠራው የእስላማዊ አሸባሪ ቡድን ተሰውተዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካም እንዲሁ ኢትዮጵያውያን ሰደተኞች ላይ ቤንዚን በማርከፍከፍ ከተሽከርካሪ ጐማ ጋር በማሰር ሦስት ኢትዮጵያውያን በእሣት ተቃጥለው እንዲሞቱ ተደርጓል፡፡ በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውን ስደተኞችን በእሣት ያቃጠሉት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ዜጐች ናቸው፡፡ በሁለቱም አገሮች የደረሰው አሠቃቂው የኢትዮጵያውያን ጅምላ ሞት ምከንያት ስር መሠረቱ ቁጥጥር ያጣው የአገሪቱ ሕዝብ ስደት ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያውያን ከየትኛውም የአገሪቱ ክልሎች በየቀኑ በጣም ከፍተኛ ሕዝብ በሕገ-ወጥ ደላሎች ከቤታቸው እንዲኮበልሉ እየተደረገ የስደት ገፈት ቀማሽ እንዲሆን ተገዷል፡፡

ህውሃት/ኢህአዴግ የሚቆጣጠራት የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ለዜጐቿ ምቹ አልሆነችም፡፡ አገዛዙ በራሱ በሚቆጣጠረው የመገናኛ ብዙሃን እንደሚለፈፈው አገሪቱ በሁለት እጥፍ እያደገች ሣይሆን በተቃራኒው ኢትዮጵያ ለዜጐቿ የማትመች፣ ፍትህ የሌለባት፣ ሰው በነፃነት የማይኖርባት፣ ችግርና መከራ የበዛባት፤ ለአብዛኛው ዜጎቿ የማትመች የመከራ ምድር በመሆኗ የአገዛዙን የጭቆና ቀምበር መሸከም ስላልቻለ፣ ኑሮ ስለከበው እልፍ-አእላፍ ዜጐች በስደት መከራ እንዲሰቃዩ ተደርገዋል፡፡ የአገዛዙ ባለስልጣኖች ሠሞኑን በስደተኛ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን እጅግ አሠቃቂ ግድያ ማውገዝ እንኳን ሲያቅታቸው ተስተውለዋል፡፡ የኢህአዴግ የዘዉግ መንግሥት ዘመንኛ ገዢዎች የተጐጅ ወገኖቻችንን ኢትዮጵያዊነት እውቅና ላለመስጠት የፈለገበት ምክንያት ለሕዝቧና ለአገሪቱ ካላቸው ስር የሰደደ ጥላቻና ግድየለሽነት የመነጨ ነው፡፡ ገዳዮቹ አሸባሪዎች “የጠላታችን የኢትዮጽያ ቤተክርስቲያን የመስቀል ጦረኞች ልጆች” ብለው ሲነግሩን ከሁሉም በላይ ደግሞ የወገኖቻችን ደምና መልካቸው እየታዬ የኢህአዴግ አምባገነን ገዢዎች ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ለመቀበል ተስኗቸዉ ተስተውሏል፡፡ ይህም ድርጊታቸው ኢትዮጵያውያንን እጅግ አሣዝኗል፤ አበሣጭቷልም፡፡ የአዲስ አበባና የአካባቢው ሕዝብ ሃዘኑን ለመግለፅ ከሰኞ ዕለት ጀምሮ ወደ ጎዳና በመውጣት ምሬቱን ሲያሠማ ተስተውሏል፡፡ ይሁን እንጂ ትናትናና ዛሬ በአዲስ አበባ ሠልፈኞች ላይ እጅግ ከፍተኛ ድብደባ በፀጥታ አስከባሪ ቅልብ ፖሊሶች ተፈጽሟል፡፡ አገዛዙ እራሱ ሠልፍ ጠርቶ መልሦ ሕዝቡን በዱላና በጥይት እያሠቃየው ይገኛል፡፡ በባዕዳን የፈሰሰው ደም ሣይደርቅ ዓለም እንኳን ይታዘበናል ብለው ሣያፍሩ ሣይሰስቱ በሰልፈኛው ሕዝብ ላይ መሣሪያ በመተኮስ ብዙ ወገኖች ከፍተኛ አደጋ ደርሦባቸዋል፡፡ ብዛት ያላቸዉ ሠልፈኞች ታሥረዋል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ፡-

የዚህ ሁሉ የማያልቅ መከራ የዕለት-ተዕለት ክስተት ዋናው ምክንያት አገሪቱ ውስጥ ያለው የመልካም አስተዳደር እጦት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለጥቂቶች ገነት ለብዙሃኑ ገሃነም የሆነች አገር ሆናለች፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ፍትሕ የለም፣ ነፃነት የለም፣ ሰዎች ባገራቸው ከቦታ ቦታ መዘዋወር አይችሉም፣ የአገዛዙ ካድሬዎች ሕዝቡን በዘርና በቋንቋ በመከፋፈል እርስ በርሱ እንዳይተማማንና እንዳይግባባ አድርገውታል፡፡ ኢትዮጵያውያን በነፃነት በእኩልነት መብታቸው ተከብሮ የመኖር ዋስትናቸው እንዲረጋገጥና ስደት እንዲቀር እንዲሁም አገራችን የጥቂቶች ሣይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን እንድትሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በነቂስ አገዛዙን መቃወምና ስርዓቱን ከስር መሠረቱ መቀየር ያስፈልጋል፡፡ስለሆነም ኢትዮጵያውያን በውስጥም በውጭም ያሣለፍነው የመከራ ዘመን ከኋላችን እንዲቀር ከተፈለገ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በሌላው ዓለም እንደታየው ሁሉ እኛም ዕጅ ለዕጅ ተያይዘን አገዛዙን በመቃወም በጋራ አሽቀንጥረን መጣል ይገባናል፡፡

ድል ለኢትዬጵያ!



የአንድነትና የሠማያዊ ድጋፍ ማህበሮች በሰሜን አሜሪካ አስተባባሪ ኮሚቴ

Not a safe planet to be an Ethiopian. By Yilma Bekele

The terrorist group ISIL murdered twenty eight Ethiopians in cold blood in the deserts of Libya. In Durban South Africa two Ethiopian brothers aged twenty two and twenty four were locked inside their ‘container shop’ and set on fire. In Beirut Lebanon a young girl jumped from her employee’s residence on the fourth floor and was badly hurt while across town another one committed suicide by hanging herself.
Thousands of Ethiopians are stranded in Yemen where there is practically no government leaving them at the mercy of warlords and smugglers. The jails from Kenya to South Africa are filled with immigrant Ethiopians with no paper.
ethiopians
The simple question is why are they roaming the planet and exposing themselves to great danger? If it is dangerous out there why are they leaving their homeland? When they do come across danger who looks after them?
The Ethiopian government has shown its indifference during the last exodus out of Saudi Arabia. They are again showing their absolute lack of respect to their fellow citizens by not even acknowledging the sad situation.
Their Ambassador to Egypt did not show shame splitting hair by explaining that based on his research Ethiopians in Libya are held by ‘smugglers not ISIS’. It is good to know our embassies are in touch with the underground. The Ethiopian government first pretended not to know, announced it is in the process of confirming their nationality and finally proclaimed a period of mourning.
We Ethiopians have no one to appeal to regarding our safety as human beings. We have no organized body like a Government that would do what is necessary to protect our life and property. There is no one that would assume responsibility to what is happening to Ethiopians all over the world. The Ethiopian government and the Ethiopian people are second to none at pointing fingers.
Under normal circumstances anywhere such a government that leaves its citizens to face danger in such a callous way would collapse in no time. First and foremost the citizens will demand accountability and the government would show remorse and submit its resignation.
The Ethiopian Government would of course condemn International terrorism and use the occasion to point out how they are victims themselves. The Diaspora Ethiopians will vent out at ISIS, South Africa and Arabs etc. Last week I would have said the Ethiopian People would grumble a little and pray a lot.
This might be the beginning of the Ethiopian Spring which we all have been waiting for. The Ethiopian youth has become hip to what is happening and are in the process of taking things in their hands.
The news from South Africa followed by the tragedy in Libya has angered our people. Meskel Square and Gotera area saw the potential of people’s power.
Just a week ago US Under Secretary of State for Political Affairs Wendy Sherman gave a clean bill of democratic health to the TPLF dominated government. It is sad but not surprising. Sometimes we confuse rhetoric for reality. The US government has never shied away from propping up, coddling or enabling such rogue regimes all over the world. Often the need for stability triumphs over the oath to respect basic human values. In the end the US does what is best for the US. At the moment the Woyane regime is the only game in town and it has managed to stifle all dissent, scare all enemies, jail all opponents and seems to have a grip on the situation and that is good enough to our western enablers.
It is a different story this week. The youth that compromises over seventy percent of our population is realizing the nature of the beast that is called Woyane. They are witnessing the bankruptcy of the system. They know the people that died in Libya. They are familiar with their brothers and sisters that are getting burned in South Africa, jailed in Zambia, being humiliated by Arabs in the Middle East and they are ready to say enough.
We cannot be mad at the savages of South Africa. We cannot dump it on the ISIS monsters that took advantage of young boys with no evil in their heart to score a cheap political point with the west. We cannot fume at the grotesque and degenerate Lebanese that gets his kicks by acting like an animal.
Our business is with our government. Our task is to ask accountability from those that purport to be elected. That is what our people are starting to do. That is what our children are asking us to do to help them with this noble act of saying enough to dictators and war lords.
What exactly are they asking us to do? It is not a major sacrifice when you think about it. They are asking us to do the right thing for a good cause. There will be no one watching over your shoulder, there will be no one checking on you. It is all based on an honor system. Your conscience is the only one that is keeping score.
The task is simple. Don’t we all claim we would do anything to help our country be free and our people enjoy the fruits of what life has to offer? When is a good time than today to show our solidarity with our people and actually stand up for what we claim to believe? Condemnation is good but it does not carry weight.
What is being asked of you is to ‘boycott’ anything and everything to do with Woyane’s Ethiopia. They caused South Africa, they facilitated Beirut and they exposed us to ISIS with their war in Somalia and association with Yemen. All disasters that affect us is due to the greedy, illiterate and money centered policy of the TPLF mafia.
Our people are waking up to do what must be done. Our task from outside where we live free is to help them achieve that goal by doing all we could to help not harm the cause.
In our case in North America boycott of Woyane is a very simple task. Before we buy enjera we should ask where the Teff is grown. There is no harm in eating bread as a substitute for people and country’s sake. We should avoid all Ethiopian produced beer. It is not about Heineken but the Woyane owners. We should not fly Ethiopian (Woyane) Airlines. Paying a hundred dollar more is not such a sacrifice for freedom. We should definitely stop getting involved in the Ponzi scheme of condominium building on stolen land. All major building material supply is owned by Woyane and their subsidiaries.
We Ethiopians in North America are enjoying the fruits of victory achieved by African Americans that used boycott as a means of protest. When it was felt boycott of the Bus system was important they walked instead of riding the bus. You are asked to take a different airlines. Is that too much to ask?
Wendy Sherman can affix any stamp on Woyane for all we care. It is not what a foreign official say that is important here but what our people think and feel about Woyane is what matters. We know it, we feel it in our bones and we are working very hard to overcome fear but no one can tell us about the good nature of the people in authority. Their actions towards our people is not different from ISIS. Our rulers are too smart and use western jargon to fool the foreigners that they pay dearly and our people were deliberately kept in the dark. But no more.
Our youth were screaming ‘Woyane Leba’ as they marched. Their fight is not with South African thugs or ISIS terrorists but their quarrel is with the bully in those masquerading as a legitimate government.
We in the west have to be careful in our response to such a disaster befalling our people in all corners of the world. Mere condemnation by the affected party is not enough. The whole world is unanimous in condemning the acts of the ISIS terrorists. All persons of authority including the pope have spoken against the inhuman act.
We Ethiopians should go beyond that. If we meet for a vigil in our Church, Mosque or town square we should use the common ground that brought us together to open a dialogue so we do not have to meet again for such sad situation. We are all sad but we should channel our strength to do something positive with it to improve the lives of our people. It is not easy but it is a necessary step so we avoid future calamities like this.
It is the real Ethiopian Spring. Time to start the new season with something fresh and something new. Our young people have finally decided it is enough. They are going to make their stand at home. The running away is not the solution. Cleaning one’s own house is the way to go. I believe we are entering a whole new world. Spring is here!

http://amharic.voanews.com/content/ethiopian-youth-and-2015-elections-debates-on-voa-04-18-15/2728160.html
http://ethsat.com/

አቶ ሃይለማርያም ተሳስተው ለስደቱ መንስኤ የፍትሃዊ ስርዓት እና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል መጥፋቱ መሆኑን ተናገሩ


የሃዘኑ ድባብ በዱላ ታጅቦ… ክንፉ አሰፋ

የሃዘኑ ድባብ ከመብራቱ መቆራረጥ ጋር ተዳምሮ ጨለማውን አብሶታል። የአሁኑ መብራት መቋረጥ ግን ከወትሮ ፈረቃ ለየት ያለ ነው። ሆን ተብሎ የተደረገ ይመስላል። ከጥቂት ስፍራ በስተቀር ሁሉም ቦታ በአንዴ እንዲጠፋ ነው የተደረገው። ከሬድዋን ሁሴን እና ከሃይለማርያም የቴሌቭሽን ዲስኩር በኋላ ሃገሩ ሁሉ ጨለማ እንዲሆን አደረጉ። ይህንን ለማድረግም በቂ ምክንያት ነበራቸው። ሃዘን ያልወጣለት ህዝብ አደባባይ ወጥቶ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት በማህበራዊ ድረ-ገጽ እንዲታይ አልተፈለገም። ህዝቡ እርስበርስ መረጃ እንዲለዋወጥ መፍቀዱም አደጋ አለው። ስልኩም ጠፋ!
ለጥቂት ጉልበተኞች ግን ይህ መብራት ከቶውንም አይጠፋም። ግዜው እስኪደርስ፣ የሚመኩበት ጉልበታቸው እስኪፈታ ድረስ ይበራል። እስከዚያው ብዙሃኑ በጨለማ ይኖራሉ።
የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ግን ከቴድሮስ አድሃኖም ጋር ትንሽ የሚጣረዝ ይመስላል። ድህነታችን ለስደት እንደዳረገን ነበር ሃይለማርያም በአደባባይ ይናገሩ የነበረው። ተሳስተው ነው? ወይንስ በጥድፍያው ምክንያት አልተናበቡ ይሆን? ልማታዊ መንግስት ድህነት የምትለዋን አይጠቀምም። ቴዎድሮስ አድሃኖም ግን በፌስ ቡክ ገጻቸው “ሁላችንም ወያኔ ነን” አዎ አሁንም ሁላችንም ወያኔን ነን። ወያኔነት ልማት፣ ኩራትና ዴሞክራሲ ነው።..ይህን ችግር የሚፈታውም ወያኔነት ነው!” ብለውናል። በመስቀል አደባባይ ወታደራቸውን አሰልፈው የሰላማዊውን ህዝብ ሃዘን በወያኔነት ሲመልሱትም አሳዩን። በሊቢያ፣ በየመን እና በደቡብ አፍሪካ በሰቆቃ ያሉ ወገኖች የሚሉትንም እየሰማን ነው። “የኛ የምንለው መንግስት የለንም! … ጨለማ ውስጥ ሆነን እየጸለይን ነው።” ይህ ነው የወያኔነት ወጤት።
አቶ ሃይለማርያም ተሳስተው አንድ እውነት ተናገሩ። አንድ ነገር ቢጨምሩበት ጥሩ ነበር። ለስደቱ መንስኤ የፍትሃዊ ስርዓት እና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል መጥፋቱ መሆኑን። ለማንኘውም በውስጥ ግምገማ ላይ ይህችን ለምን እንደተናገሩ ያስረዱ ይሆናል።
ለሃዘን የወጣ ህዝብ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት ሮይተርስ ከአዲስ አበባ አሳይቶናል። ዜጎች ሲቀጠቀጡ የሚያሳዩ የቪድዮ ምስሎች በማህበራዊ ድረ-ገሶች በስፋት ተበትነዋልል። ሬድዋን ሁሴን ግን ወታደሮቹ አንድም ሰው እንዳልነኩ ነገሩን። ታድያ ዥጉርጉሩን የፌዴራል ልብስ ያጠለቀ አይሲስ ነበር እንዴ በመስቀል አደባባይ ህዝቡን ሲያሸብር የነበረው? ሃፍረት ያልፈጠረባቸው፤ የሰብአዊ ፍጡር ህሊና የሌላቸው ውሸታሞች ናቸውና ይህን ማለታቸው አይደንቅም። ኢውሮ ኒውስ ከአዲስ አበባ በቀጥታ ያሳይ የነበረው ትእይንት ዘግናኝ ነበር። አይሲስ በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸመውን የማይተናነስ ጭካኔ አሳዩን። ህጻን፤ ሴትና አዛውንት እንኳን ሳይለዩ ሁሉንም በጭካኔ ቀጠቀጡ። የህዝብ ወገን ቢሆኑ በወገን፤ ለዚያውም በሃዘን ላይ ያለ ህዝብ ላይ እንዲህ አይጨክኑም። በእውነቱ ባእዳንም እንዲህ ባዘነ ህዝብ ላይ አይጨክኑም። የ97ቱን ሰቆቃ አስታወሱን።
የታፈነው ህዝብ በአንድ ላይ ሆኖ ብሶቱን ሲገልጽ ሰማን። ሬድዋን ሁሴን እንደሚሉት ከዚህ ረብሽ ጀርባ ሰማያዊ ፓርቲ አለበት። ከጨርቆስ እስከ ፈረንሳይ ለጋሲዮን፣ ከቦሌ እስከ ኮልፌ፤ ከዘነበወርቅ እስከ ሽሮ ሜዳ … ያለ ህዝብ ሁሉ ሰማያዊ ፓርቲ ከሆነ ህዝብ ከናንተ ጋር አይደለምና ስልጣኑን ለሰማያዊ ፓርቲ ማስረከብ ነው ያለባቸው። አይገባቸው ይሆናል እንጂ በተዘዋዋሪ እየነገሩን ያሉት ህዝብ በሙሉ እንደጠላቸው ነው። ጥቂት ያሉትንም የህዝብ ቁጥር በምስል አየነው።
ይህ የህዝብ መልእክት ትምህርት ካልሆናቸው አምሯቸው የታወረ ነው። ክስተቱ እንደፈርዖን በባርነት የያዙት ህዝብ ምን ያህል እንደተከፋ ያሳየናል። 23 አመታት በጫንቃው ላይ የተቀመጠው ስርዓት ምን ያህል እንዳንገፈገፈው የሚያሳይ ባሮ ሜትር ነው።
ለመሆኑ እነዚያ ባለስልጣናት ሲሞት ደረት የሚመቱት ልማታዊ አርቲስቶች የት ጠፉ? “ታላቁ መሪ” ባረፉ ግዜ ማቅ ለብሰው እዩኝ-እዩኝ ይሉ የነበሩ አርቲስቶች ነብስ እየመረጡ ነው የሚያለቅሱት? በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ የተሰውት ወገኖች የሰብአዊ ፍጡራን አይደሉም እንዴ? ወይንስ ሃዘንም በትእዛዝ ሆነ? መቼም በዚህ ሰቆቃ ለማዘን የግድ ኢትዮጵያዊ መሆን አያስፈልግም። ለማዘን ሰው መሆን ብቻ ይበቃል። በዚህ የጨለማ ወቅት ከህዝብ ወገን ያልሆነ ሁሉ ለህሊናው ሳይሆን ለሆዱ የሚገዛ እንስሳ ብቻ ነው። መቼም የማያልፍ ነገር የለም ይህም ያልፍና ሁላችንንም ያስተዛዝበናል።

One year after arrest Zone 9 bloggers remain imprisoned as trial drags on

Zone-9-founders-in-December-2012-Tadias-Magazine-coverIt will be one year this weekend since six bloggers were arrested in Addis Ababa, just days after the group announced on Facebook that their Zone 9 blog would resume publishing after seven months of inactivity. As the anniversary of the arrests approaches on Saturday, Soleyana S. Gebremichale, one of the Zone 9 founders who was charged in absentia, told me the situation was not hopeless.
“International advocacy is important not only to pressure the Ethiopian government but also to show solidarity for people in prison,” Soleyana, who is currently based in Washington, D.C., said. “The words and support that we show them are their strength in prison.”
The six Zone 9 bloggers, arrested along with three journalists not connected to the blog, were held in detention until mid-July when a court in Addis Ababa chargedall those being held, and Soleyana, with terrorism. Working with human rights organizations and participating in an email encryption training session were among the activities that led to the charges, according to reports. Their charge sheet, translated into English from Amharic, can be found here in full.
The Zone 9 bloggers–Befekadu Hailu, Atnaf Berhane, Natnail Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabella–and three journalists–Edom Kassaye, Tesfalem Waldyes, and Asmamaw Hailegeorgis–have now spent a full year in prison.
Among them is a lawyer and lecturer, an economist, and an IT specialist. One of them is a data expert in Ethiopia’s Ministry of Health, another is an engineer for Ethiopian Airlines. They are writers, advocates, and activists, but the Zone 9 bloggers are not terrorists.
According to reports, these young professionals from a range of backgrounds were united by a desire for a more just, transparent, and democratic Ethiopia. The Zone 9 bloggers used their blog, which is still running,as a platform to write about social justice, democracy, and human rights. They spoke out about censorship and challenged corruption.
“Zone 9 existed because we had a hope that we could contribute for the public discourse,” Soleyana told me.
The trial has been adjourned 26 times, most recently on April 8, according to a site that tracks its progress. The proceedings are scheduled to resume on May 26.According to the Trial Tracker Blog, which publishes news reports and details of campaigns about Zone 9, police continue to search for evidence to support the charges and failed to provide the defense with access to evidence they allegedly have. A request by the defense for the removal of judge, who the bloggers’ lawyer said had been “unfair” throughout the trial, was rejected.
According to the same site, in some instances family and friends were allegedly prevented from entering the courtroom. The nongovernmental organizationEthiopia Human Rights Project reported that “Female detainees could not be visited by friends and relatives” and that when visits were permitted, they were limited to six people only, for a maximum of 20 minutes a day.
Ethiopian officials have repeatedly rejected external criticism of their handling of the Zone 9 case, according to news reports including this piece by The Washington Post. According to the Post, the government denied the bloggers were imprisoned for their writing, and said they were on trial for attempting to sabotage the state. This sentiment was echoed by Communication Affairs Minister Redwan Hussein who, at a press conferencein May last year, said of the Zone 9 bloggers, “Most of them are not journalists but activists … if someone engaged in criminal activities, he will face prosecution regardless of his profession.”
Ethiopia, ranked fourth on CPJ’s list of the 10 Most Censored Countries, has consistently demonstrated itself to be hostile to the idea of a free press, using charges of terrorism to justify long jail sentences of journalists. In a series of trials documented by CPJ over the past four years, deputy editor of Awramba Times,Woubshet Taye was sentenced to 14 years, freelance writer Eskinder Nega to 18 years, and Feteh journalist Reeyot Alemu to 14 years, reduced to five on appeal. Prison authorities were accused of denying adequate medical attention to Reeyotand Temesghen Desalegn, the owner of Feteh magazine. And in two reports released by Citizen Lab, based at the University of Toronto, researchers said Ethiopia appeared to have used malware and surveillance tools to try to monitor Ethiopian journalists around the world.
Soleyana welcomed international attention to her colleagues’ plight. “Though it seems like the impact is slow and sometimes invisible I believe that the international pressure would contribute to change the decision of the Ethiopian government,” she said.
Despite international criticism, Ethiopia has been defending its anti-terror laws for years. Speaking to the BBC in 2014, Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn defended them as being similar to that of the UK terror laws. In 2012, the then Prime Minister Meles Zenawi defended the laws in Parliament. In response to a critical op-ed by Nicholas Kristof in The New York Times, the country’s Foreign Ministry argued that Ethiopia did respect press freedom, according to reports.
From Al-Shabab’s attack at Garissa in Kenya this month and Boko Haram’srelentless violence against Nigerians, to the senseless acts of groups such as al-Qaeda in the Islamic Maghreb, you don’t have to look far to find examples of terrorism across the African continent.
But as former High Commissioner for Human Rights Navi Pillay stressed in May last year, in response to Ethiopia’s crackdown on the press, “The fight against terrorism cannot serve as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, human rights activists and members of civil society organizations.”
In a statement this week, the U.N. Special Rapporteur on the promotion and protection of human rights and fundamental freedoms while countering terrorism, Ben Emmerson, and the UN Special Rapporteur on religious freedom, Heiner Bielefeldt, said: “By actively promoting and protecting human rights, states contribute to preventing terrorism in an effort to address its root causes and risk factors.”
At a time when national leaders should be protecting rights and providing reassurance from very real threats like these, many governments choose instead to crush those voices most in need of being heard. This has certainly been true in Ethiopia.
  • Support jailed journalists in Ethiopia and other countries by joining CPJ’s “Press Uncuffed” campaign.

wanted officials