Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, September 14, 2016

የቱርክ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ባለንብረቶች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የባንክ ብድርና የታክስ ክፍያ ሳይከፍሉ ከሃገር መኮብለላቸው ተሰማ

የቱርክ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ባለንብረቶች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የባንክ ብድርና የታክስ ክፍያ ሳይከፍሉ ከሃገር መኮብለላቸው ተሰማ
ኢሳት (ታህሳስ 18 ፥ 2009)
ሁለት የቱርክ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ባለንብረቶች ከመንግስት የወሰዱትን ወደ አንድ ቢሊዮን ብር የባንክ ብድርና የታክስ ክፍያ ሳይከፍሉ ከሃገር መኮብለላቸው ተሰማ።
ለሁለት የቱርክ ባለሃብቶች ብድር ሰጥቶ የነበረው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ ግለሰቦቹ ከኢትዮጵያ እንዳይወጡ ጥያቄውን ለኢሚግሬሽን ቢሮ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ ጥያቄው በቶሎ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት ባለሃብቶች ወደ ሃገራቸው ቱርክ መሄዳቸው ታውቋል።
ሳይፈቲን እና ኢማም አልቲንባ የተሰኙት ሁለት የቱርክ የጨርቃጨርቅ ባለሃብቶች ከመንግስት በወሰዱት ብድር ያቋቋሙት ኤልስ አዲስ ኢንዱስትሪያል ዴቬሎፕመንት ሃላፊነቱ የግል ኩባንያ ከአምስት አመት በፊት ወደ ምርት ስራ መግባቱን በሃገር ውስጥ የሚታተሙ ጋዜጦች ዘግበዋል።
ይኸው በናዝሬት አዳማ ከተማ የሚገኘው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ባለፈው አመት ወደ 4 ሚሊዮን ብር የሚደርስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ ባለመክፈሉ የሃይል አቅርቦቱ ተቋጦበት እንደነበር ተመልክቷል።
የጨርቃጨርቅ ፋብሪካው ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከመንግስት የወሰደውን ብድር በአግባቡ መክፈል እንዳልጀመረ የሚገልጽ ማሳሰቢያ ሲሰጠው እንደነበረም የባንኩ ሃላፊዎች አስረድተዋል።
ፋብሪካው የማምረት አቅሙ 95 በመቶ አካባቢ ደርሶ የነበረ ቢሆንም፣ ምክንያቱ ባልታወቀ መንገድ ምርቱን ወደ ውጭ እንዳልላከ በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ኢንስቲትዩት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት አቶ ባንቲሁን ገሰሰ አዲስ ፎርቹን ለተሰኘው ጋዜጣ ተናግረዋል።
የፋብሪካው ባለንብረቶች በአጠቃላይ ከመንግስት 900 ሚሊዮን ብር አካባቢ ብድርና ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ እያለባቸው ከሃገር የኮበለሉ ሲሆን፣ የባለሃብቶቹ መሰወር ተከትሎ ለፋብሪካው የጥጥ ምርት በማቅረብ ላይ የነበሩ 10 ድርጅቶችም ያልተከፈላቸው 20 ሚሊዮን ብር አካባቢ መኖሩን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አስታውቀዋል።
እነዚሁ ጥጥ አቅራቢዎች የፋብሪካው ባለቤቶች በባንኮች ተቀባይነት የሌለው ቼክ ሲሰጧቸው እንደነበርም ለመንግስት ባቀረበቱት አቤቱታ ገልጸዋል።
የጨርቃጨርቅ ፋብሪካው ከመቋቋሙ ጊዜ ጀምሮ በአምስት ዙሮች ለእቃ ግዢዎችና ለስራ ማስኬጃዎች በማለት ብድሩን ሲወስድ የቆየ ሲሆን፣ የአንድ አመት ያልተከፈለ የግብር ዕዳው ብቻ 30 ሚሊዮን ብር አካባቢ መሆኑም ታውቋል።
ባለንብረቶቹ ከሃገር ከመውጣታቸው በፊት የፋብሪካው ማሽነሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ አበላሽተው የነበረ ቢሆንም፣ መንግስት የውጭ ባለሙያዎችን በማስመጣት ብልሽቱ መፍትሄ እንዲያገኝ ማድረጉንም ለመረዳት ተችሏል።
ለፋብሪካው ብድርን የሰጠው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፋብሪካውን በ729 ሚሊዮን ብር ለመሸጥ ጨረታን አውጥቶ የሚገኝ ሲሆን፣ ፋብሪካው ወደ 1ሺ የሚጠጉ ሰራተኞች እንዳሉት ታውቋል።
በጋምቤላ ክልል ተመሳሳይ ሁኔታ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ የተሰማሩ የህንድ ባለሃብቶች ከመንግስት የወሰዱትን ከፍተኛ ብድር ሳይመልሱ ከሃገር መኮብለላቸውን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን፣ የመንግስት ባለስልጣናት በህንድ ባለሃብቶች ያልተመለሰውን የብድር መጠን ከመግለፅ ተቆጥበዋል።
በክልሉ በጫት ቤቶች ሳይቀር የመሬት ይዞታ ካርታ ሲሰጥ መቆየቱን የገለጹት ባለስልጣናት ይህንኑ ህገወጥ ድርጊት ፈጽመዋል የተባሉ አምስት አመራሮችና ስምንት ባለሙያዎች ለእስር መዳረጋቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጋትሎዋክ ቱት ለመንግስት መገኛኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፣ በቅርቡ በጋምቤላ ክልል ከመሬት አሰጣጥ ጋር ተፈጽሟል ከተባለው የሙስና ድርጊት ጋር በተያያዘ 13 የክልሉ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል። ወደ 4.9 ቢሊዮን ብር ብድር በወሰዱት የትግራይ ባለሃብቶች በልማት ባንኩ ሃላፊዎች ላይ ግን የተወሰደ ርምጃ የለም።
በርካታ ባለሃብቶች በተመሳሳይ መሬት ላይ ብድርን በመውሰድ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ላይ በቢልዮን የሚቆጠር ኪሳራ ማድረሳቸውና በክልሉ በኢንቨስትመንት ስም የተካሄደው መሬት የመስጠት ዘመቻ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ መብለጡን 15 አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ጥናቱን ማቅረቡ ይታወሳል። የትግራይ ባለሃብቶች ቡድኑ የወሬኞችና የአሳባቂዎች ደጋፊ ሲሉ መዝለፋቸው ይታወሳል

የኮንሶ መንደሮች የ987 ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸው በከባድ መሳሪያ አመድ በአመድ ሆኗል



የኮንሶ መንደሮች አይሎታ ዶካቱ እና ሉሊቶ ትግሬ-ወያኔዎች እና አሽከሮቻቸው ጋዩ:: ከፍጅቱ ማምለጥ የቻሉ ሲያመልጥ አቅመ ደካሞች እንዲሁም ሴቶችና ህፃናትን ጨምሮ ብዙዎች ተገለዋል። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብም በሽሽት ኮንሶ ካራት ከተማን አጥለቅልቋት በረሀብና በጥም እንየተንገላታ ነው።
የኮንሶ ህዝብ ማንኛውም ወገን ሰበዓዊ ድርጅቶች እርዳታ እንዲለግሱዋቸውም እየጠየቁ ነው።
ከ3000 በላይ ወታደር ከነሙሉ ትጥቁ ሰፍሮ ጥይት እያርከፈከፈ ህዝቡን እየፈጀው ነው።


በደቡብ ክልል አመራሮች ድጋፍ የሃገር መከላከያ ሰራዊት በኮንሶ ህዝብ ላያ በከፈቱት የዘረ ጭፍጨፋን ተከትሎ 65 ሰው ህይወት ስያልፍ 45 የሚሆኑትን በራሳቸው በሰራዊቱ መኪና ጭነው የት እንዳስገቡ አይታወቅም የ987 ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸው በከባድ መሳሪያ አመድ በአመድ ሆኗል። በሰአቱ አቅም ያለው ሲያመልጥ አቅም የሌላቸው ብዙ ህፃናት ቤት ውስጥ መቃጠላቸው መረጃዎች ሲጠቁሙ ከስምንት ቀበሌ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ወደ መዲና ከተማቸው ለማምለጥ ሲጥሩ መግቢያ መንገዶች ሁሉ በሰራዊት ታጥረው ከመፍራታቸው የተነሳ ወደ አረባምንጭ መስመር ሲጓዙ የነበሩ እናቶች ከነ ህፃናታቸው በረሀብና ጥማት እያለቁ ይገኛሉ።በኮንሶ በርካታ ዜጎች ተገደሉ : አካባቢው የጦርነት ቀጣና ሆኗል ተባለ።

የመከላከያ ሰራዊት እና የደቡብ ክልል የልዩ ሃይል አባላት በኮንሶ ህዝብ ላይ እየፈጸሙት ባለው ጥቃት በርካታ ዜጎች ተገድለዋል። እስካሁን ድረስ ባለው መረጃ ከ25 ያላነሱ ሰዎች ተገድለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ግን የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ይሆናል ይላሉ። ከተገደሉት መካከል አንድ አራስ ሴት በጥይት ተደብድባ ስትገደል፣ ህጻኑ በወታደሮች ተወስዷል በማለት የአገር ሽማግሌዎች ገልጸዋል።

ትናንት ብቻ ከ4 ሺ 50 በላይ ሰዎች የተሰደዱ ሲሆን፣ ዛሬም ስደቱ ቀጥሎአል በማለት የአገር ሽማግሌዎች ይናገራሉ።


ጭፍጨፋውና እልቂቱ ሊቀጥል እንደሚችል የአገር ሽማግሌዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።

Tuesday, September 13, 2016

Night shout protest in Addis ababa

የዩናይትድ ስቴትስ ምክርቤት አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ጋር በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ረቂቅ አቀረበ




በሪዮ ኦሎምፒክ ሁለት እጆቹን በማጣመር ተቃውሞ ያሳየው ኢትዮጵያዊ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ከዩናይትድ ስቴትስ የምክርቤት አባል ክሪስ ስሚዝ ጋር በካፒቶልሂል ፊት ለፊት

የዩናይትድ ስቴትስ ሕግ አውጪ ምክር ቤት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ የተነጣጠረ ረቂቅ ውሳኔ በዛሬው ዕለት ይፋ አደረገ።



ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

የዩናይትድ ስቴትስ ምክርቤት በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ረቂቅ አቀረበ(6:36)



http://amharic.voanews.com/a/usa-congressman-chris-smith-on-ethiopian-human-right/3505870.html


Ethiopian Paralympic athlete Tamiru Demisse in new finishing line protest against oppressive regime


Ethiopian Paralympic athlete Tamiru Demisse in new finishing line protest against oppressive regime


1500m runner echoes protest of fellow countryman Feyisa Lilesa, who has now fled to the US



Ethiopia's Tamiru Demisse (C) reacts after the final of men's 1500 m (T13) of the Rio 2016 Paralympic Games at the Olympic stadium in Rio de Janeiro on September 11, 2016 AFP/Getty Images


A runner has become the latest Ethiopian athlete to stage a political protest in Rio, after he crossed the finish line in a 1500m event at the Paralympics.

Tamiru Demisse, who was competing in the final of the T13 race for visually impaired runners, crossed his arms above his head as he crossed the line in second place, taking silver behind Algeria’s Abdellatif Baka.
ADVERTISING




The crossed-arms symbol is in reference to the political persecution of the Oromo ethnic group by the government back home, and echoed a similar gesture made by Feyisa Lilesa at the end of the marathon event in the Olympics.

Unlike Feyisa, who was reminded by officials that the International Olympic Committee frowns upon political gestures at the Games, Tamiru also repeated the gesture during the ceremony to receive his medal.

Last month, Feyisa explained that he he conducted his protest in response to the killing of the Oromo people, saying the government was “killing our people”.

He has now travelled to the US, after a crowd-funding campaign to support him and his family raised its target of $150,000. He said if he returned to Ethiopia “they will kill me… or if not kill me, they will put me in prison”.

READ MORE
Feyisa Lilesa fails to return to Ethiopia after Olympic protest


Sunday evening’s T13 1500m race was also remarkable for the fact that the top three runners, Algeria’s Baka, Tamiru and Kenya’s Henry Kirwa, all ran faster times than the 3:50:00 that won gold for the US’s Matthew Centrowitz Jr in the Olympic 1500m race.

The conflict between the government and the Oromo, the largest single ethnic group in Ethiopia, flared up last year over land and political rights.

Human Rights Watch estimates that more than 500 people have been killed since the government began a brutal crackdown on political protests. The government disputes that figure.

Angela Merkel stunned by massive protest against Ethiopian government (TPLF) in Berlin.

 – By Zerihun Shumete/ Germany



Ethiopians who live in Germany have held a huge protest against the 25 years dictatorial Ethiopian government ( TPLF) on 09 Sep 2016 . As the beating, killing and jailing of innocent Ethiopians by the ruling party EPDRF continues in various parts of the country ( https://www.youtube.com/watch?v=OadpfWUbMOY), the Ethiopian diaspora community in Germany went out on the streets of Berlin to condemn these barbaric acts and to voice their anger and protests. The Ethiopian civic organizations, which are found in Germany, has arranged and successfully launched this demonstration. This protest was held in front of Germany Foreign office bureau, embassies of United States and France. At last the demonstration ended in front of the official residence of the German federal chancellery, Angela Mackerel’s building.
The main objectives of the Berlin demonstrations were
1. supporting and standing in solidarity with the people of Ethiopia
2. warning the TPLF regime to stop committing crimes against the people of Ethiopia
3. putting pressure on the government to release journalists, political and religious leaders unconditionally
4. demanding the 25 years dictatorial government (EPRDF /TPLF) to step down and hand the power to the people
5. requesting the German government to stop supporting tyranny Ethiopian government financially and materially.
Ethiopians all over Germany have been opposing the ruthless ethnic-based dictatorial rule of the present regime in different ways. On 08 Sep. 2016 brave Ethiopians have barged into TPLF’s consulate in Frankfurt and expressed their anger and detest for the regime. They demanded the Woyane rule to stop killing Ethiopians and to hand over the power to the people peacefully otherwise the power will be taken by all means and given to the owners, who are the Ethiopian people. Various activities of pressuring the German government to stop supporting the Ethiopian regime have been also carried out by Ethiopian diaspora community. Demonstrations in Frankfurt on April 2016 , solidarity and memorial programs in Munich on September 2016 ( for those innocent and peaceful Ethiopians who are brutally killed by TPLF soldiers in Amhara and Oromia) and petitions programs were conducted successfully by Ethiopians in Germany.
The European union has announced its decision not to give Emergency trust fund money to TPLF regime on 07 September 2016 due to the recent killings, jailing and beating of innocent demonstrators and protesters by the government( in Amhara and Oromo regions) U.S has also raised a great concern on the ongoing people protests and on the use of military actions on peaceful demonstrators by the government. German media have been also covering the Ethiopian people protests ( in Amhara and Oromia ) and the brutal responses of the government. Among these are
-Die Zeit http://www.zeit.de/politik/ausland/2016-08/aethiopien-demonstrationen-tote-amnesty-international ,
-Zeit Online ( http://www.zeit.de/video/2016-08/5073642244001/aethiopien-proteste-in-addis-abeba)
-ZDF ( http://www.zdf.de/ZDFmediathek/beitrag/video/2810508/Aethiopien-Ein-Land-in-Aufruhr#/beitrag/video/2810508/Aethiopien-Ein-Land-in-Aufruhr) ,
-Die Tagesschau (https://www.tagesschau.de/ausland/aethiopien-105.html)
– Deutsch welle (http://www.dw.com/de/viele-tote-bei-protesten-in-%C3%A4thiopien/a-19458253)
By Zerihun Shumete
From Germany

በምስራቅ ሸዋ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት አለፈ


 በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦራ ወረዳ ዛሬ ሊነጋጋ ሲል በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ታህሳስ 16፣ 2009 ማለፉን ፖሊስ  አስታወቀ።
አደጋው የደረሰው ሾፌሩን ጨምሮ 14 ሰዎችን አሳፍሮ ከባቱ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሽ ተሽከርካሪ ቦራ ወረዳ ሶሪ ዶሌሳ ቀበሌ ሲደርስ ከቢሾፍቱ ከተማ ወደ ባቱ ከተማ ከሚጓዝ ሲኖ ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።
የዞኑ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ እንደገለፁት፥ በአደጋው በህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ሾፌሩን ጨምሮ በሙሉ ህይወታቸው አልፏል።
የሟቾች አስከሬን ወደ አዳማ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን፥ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ከፍጥነት በላይ እየተጓዘ እያለ ሲኖ ትራኩ መንገዱን ስቶ እንደገባበት ምክትል ኮማንደር አስቻለው ጠቁሟል።
ሆኖም ለተጨማሪ ምርመራ የሲኖ ትራኩ አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ እየተጣራ ነው ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ሌሊት እንዳይጓዙ የተከለከለ ቢሆንም ትርፍ
ሰው ለመጫን ሲሉ ተደብቀው በሚያደርጉት የሌሊት ጉዞ መንገደኛውን ለአደጋ እያጋለጡት በመሆኑ የትራፊክ ፖሊሶች የሌሊት ቁጥጥራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ምክትል ኮማንደሩ ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡም የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ከፖሊስ ጋር በመተባበር የቁጥጥሩን ስራ እንዲያግዝ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ አመልክተዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ

በጎጃምና በጎንደር በአብያተ ክርስቲያናት አቡነ ማቲያስ የሚመራውን ሲኖዶስና አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ እንደማይቀበሉት አስታወቁ።

በጎጃምና በጎንደር በአብያተ ክርስቲያናትና በገዳማት ውስጥ የሚገኙ ካህናትና መነኮሳት በአቡነ ማቲያስ የሚመራውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስና የቤተክርስቲያን አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ እንደማይቀበሉትና እንደማይተዳደሩ አስታወቁ።


”በመላው ሀገራችን ገዳማትና አድባራት የምትገኙ ካህናትና መነኮሳት የእኛን ፈለግ በመከተል የአባ ማትያስን አባትነት ባለመቀበል ቤተክርስቲያንና ትውልዱን እንድንታደገው በህያው እግዚያብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን ” ብለዋል የጎጃምና የጎንደር ካህናትና መነኮሳት።

ኢሳት

Monday, September 12, 2016

አዳዲስ መረጃዎች ….. የጉድ ዘመን መጣልን ጠበል መሸጥም ተጀመረልን -ዘመድኩን በቀለ




ዋጋው 15 ሊትሩ ጠበል 5 ብር ተተምኖለታል ። ድሆች እርማችንን እናውጣ ።

በቀጣይ መስቀል ለመሳለም ፣ ቅዳሴ ለማስቀደስም ክፍያ ሳይጠይቁ አይቀርም እየተባለም ነው ።

 ከዛሬ ጀምሮ በጎንደርና በጎጃም የሚገኙ አብያተክርስቲያናት በሙሉ ለማእከላዊው የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር አንገዛም ለአቡነ ማትያስም አንታዘዝም አሉ የሚል ዜና እየወጣ ነው ።

አሁን አሁን የቤተክርስቲያንን ክብር ዝቅ ያደረጉ የመሰላቸው ሰዎች በየሥፍራው ባላቸው መንግሥታዊ ስልጣን በመጠቀም በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ክብሯን ዝቅ ያደርጋል የሚሉትን ተግባራት በሙሉ ያለአንዳች ከልካይና ተቆጪ በነፃነት በመፈጸም ላይ ይገኛሉ ።

ታቦት መሸጥ ፣ ቅርሶቿን መዝረፍ ፣ ይዞታዎቿን መውረስ ፣ የመስቀል አደባባዮችና የጥምቀት ባህሮችን ለኢንቨስተር መሸጥ ዋና ሥራቸው ከሆነ ውሎ አድሯል ። ይህ የተለመደ ቢሆንም አሁን በውስጥ መስመር ከሚደርሱኝ ብዛት ያላቸው መረጃዎች መካከል አንዱን አሳፋሪ የጠበል ሽያጭን የተመለከተውን ዜና እነሆ ብያለሁ ።

በምስራቅ ሸዋ ዞን በቦሰት ወረዳ በቆምቤ ቀበሌ ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን ሰብስቦ ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር በማቋቋም በጥቃቅንና አነስተኛም በማደራጀት ፤ ፀበልን በሊትር እየሸጡ ይጠቀሙ ዘንድ የክልሉ መንግሥት የወረዳው ሰዎች ካርኒና ደረሰኝ አዘጋጅተው ለሥራ አጥ ወጣቶች በመስጠት የአከባቢው ወጣቶችን በጸበል ንግድ ላይ ላይ እንዲሰማሩ ማደረጉን ከሥፍራው የመጣ መረጃ ያመለክትናል።

ይህ ሁሉ ሲፈጸም እነ ፓትርያርክ አባ ማትያስና በየሀገረ ስብከቱ እየተሾሙ የሚላኩት ከአንድ ብሄር የሚውጣጡ ሹመኛ የቤተክህነቱ ባለስልጣናት ምንም አይነት ደንታም እንደማይሰጣቸው ተቃውሞም እንደማያሰሙ ይታወቃል ።

ዛሬ ጠበል በጠራራ ፀሐይ በደረሰኝ ከቤተክርስቲያን ቀኖና ውጪ መሸጥ ከተጀመረ ነገ እነዚህ ጉደኞች ምን ሊያመጡብን እንደሚችሉ ከወዲሁ መገመት አያቅተንም ።

እናም የተከበራችሁ የእምዬ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ አሁን መንግስት በሹመት ቤተክርሲትያን ላይ በግድ የጫነብንን የአቡነ ማትያስ አገዛዝ ከላይ እስከታች ገንዘብ ባለበት ሥፍራ ሁሉ የአንድ ብሄርና የአንድ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ሰግስጎ ሰግስጎ በማስቀመጥ እንደመዥገር የሚመጠምጧትን ነቀዞች ማስቆም የምንችለው በአሁን ሰዓት ለቤተክርስቲያን የምንሰጠውን ማንኛውንም አይነት ገንዘብ ለጊዜው ማቆም ስንችል ነው ።

አሁን አሁን የሚደርሱኝ መረጃዎች እንደሚያሳዩኝ ከሆነ በጎንደርና በጎጃም የሚገኙ አብያተክርስቲያናት የሚያስደነግጥ እርምጃ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ ።

በተለይ በጎጃም እና በጎንደር በኦሮምያም በሙሉ የፓትርያርክ አባ ማትያስ የሰፈር ልጆች በወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት ጭፍጨፋ ፓትርያርኩና ሲኖዶሳቸው ዝምታን በመምረጥ ለሟቾች እና ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን እንኳን ባለመመኘታቸው ፤ በተለይ በጎንደርና በጎጃም የሚገኙ አድባራትና ገዳማት ከዛሬ ጀምሮ ለዋናው መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ባለመታዘዝ ስባሪ ሳንቲም እንደማይልኩ በይፋ የማወጃቸው ዜናም በመላው ዓለም እየናኘ ይገኛል።

ይሄ ለዘረኛው ቤተክህነት በተለይ በአንድ ብሄር ተደራጅተው ከአለቃ እስከ ዘበኛ ድረስ ቤተክርስቲያኒቱን ለሚግጡት ነውረኞች ወደ መቃብር ለመውረዳቸው ትልቅ ምልክት ነው ።

በዚሁ መልኩ በለፉት 25 ዓመታት ከሳውዲ አረብያ የነዳጅ ጉድጓዶች በበለጠ የገዢው ፓርቲ ትጥቅና ስንቅ መግዣ የሚሆን ገንዘብ ሲሰበሰብበት የነበረውን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የዋና ሥራ አስኪያጅነት ሥፍራ ከትግራይ ተወላጆች ውጪ ሌላ ሰው እንዲይዘው አይደረግም ።

ለምሳሌ በቅርቡ እንኳን በሚልየን የሚቆጠር ብር ለልጁ ማሳከሚያ የሚሆን ገንዘብ ኮሚቴ በማዋቀር ጭምር ዘርፏል ተብሎ በብዙ ጩኸት ከአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሥራአስኪያጅነት በተባረረው የኢቴቪ የትግርኛ ዜና አንባቢ በሆነው በአቶ የማነ ምትክ ጭራሽ አማርኛ እንኳን በቅጡ መናገር የማይችል ጎይቶም የተባለ ሰው በቦራው ሾመውበት በነጻነት ለአማራና ኦሮሞ ልጆች መግደያ የሚሆነውን ጥይት መግዣ የሚያገኙበትን ሥፍራ በቁጥጥር ስር እንዲውል አድርገውታል ።

እናም የተከበራችሁ ምእመናን ይህን ዐይን ያወጣ ዘረፋና ሌብነት ማስቆም የምንችለው በወርሀ ጳጉሜ የጀመርነውንና እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ለ3 ወር ያህል የሚቆየውን የሙዳይ ምጽዋትና የአስራት በኩራት እቀባው አጠናክረን ስንቀጥል ነው ።

 ማሳሰቢያ ለምእመናን በሙሉ

1ኛ፦ አስራት በኩራት የምታወጡም ሆነ ለሙዳየምጽዋት የምትሰጡት ገንዘብ ለእግዚአብሔር የምንሰጠውና አምላካዊ ትእዛዝ መሆኑን እንዳትዘነጉ ።ስለዚህም ምእመናን ይህ ለእግዚአብሔር የምናወጣው የራሱ የእግዚአብሔርን ገንዘብ ለግል ጥቅማችሁ ማዋል ስለሌለባችሁ በቤተሰብ ደረጃ ተመካክራችሁ አስፈላጊውንም ዘዴ ቀይሳችሁ የእግዚአብሔርን ገንዘብ ለይታችሁ ለብቻው አስቀምጡ ። ይህ የአደራ ማሳሰቢያዬ ነው ።

2ኛ፦ እንደሚታወቀው ይህ እርምጃችን ውጤታማ እስኪሆን ድረስ ከላይ በሙስና የተቀመጠት በዝባዦች ለጊዜው ምንም ላይጎዱ ይችላሉ ። ሆኖም በዚህ እቀባ ምክንያት የሚጎዱት ምስኪን ካህናትና ዲያቆናት መሆናቸውም ይታ ቃል ። እናም ምእመናንና የንስሐ ልጆች የሆናችሁ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች በሙሉ አባቶችና ወንድሞችን በመደጎም ውጤታማ ሥራ እንድንሠራ ይሁን ።

3ኛ፦ እነሱ ከላይ እስከታች በዘረኝነት ተተብትበው እና ተጠምቀው ሳለ እኛ ለምን ብለን መጠየቅ ስንጀምር ለማሸማቀቅ ዘረኞች ፣ ጠባቦች ፣ ትምክህተኞች በሚሉ ራሳቸው በፈጠሩልን የማሸማቀቂያ ገመድ አንጠለፍም ። ዘረኝነትን መቃወም ፖለቲከኛም አያስብልም ። አለቀ አራት ነጥብ ።

አሁን በኢትዮጵያም ሆነ በቅድስት ቤተክርስቲያን እየተፈጸመ ስላለው ግፍና መከራ ለመናገር እውነት እውነት እላችኋለሁ ሰባኪም ፣ ፖለቲከኛም ፣ አትሌትም ፣ ሆነ ግንበኛ ፣ መሆንን አይጠይቅም ። ” ጉዳዩን ለመቃወም ሰው መሆን ብቻውን በቂ ነው ” ።

 ጉዞው እስከ ቀራንዮ ነው ፣ ድል ለእምዬ ተዋህዶ !!! ወድቀት ለዘረኞች ።

ይህንንም ራሴው ዘመድኩን በቀለ ጻፍኩት ።ለማንኛውም በነጻነት እንወያይ ፤ ከስድብና ከዛቻ በራቀ መልኩ እንነጋገር ። +251911608054 የቫይበር ስልኬ ነው ። በተለይ ይህን መልእክቴን በተመለከተ ደግሞComent መስጠትናShare ማድረግ በእጅጉ ይበረታተል ።

ሻሎም ! ሰላም !

ዘመድኩን በቀለ ነኝ
መስከረም/2/2009 ዓም

ሙዳየ ምጽዋትና አስራት በኩራት ለወያኔ ቤተክርስቲያን ያለመስጠቱ አድማ በስኬት እየተካሄደ ነው።

የምስራች ለተዋህዶ ልጆች በሙሉ – ቦይኮቱ በሚገባ እየተሳካ ነው | ዘመድኩን በቀለ


✔# የሙዳይምጽዋቱና ✔# የአስራትበኩራት እቀባውም እየተሳካና መስመሩን ይዞ እየሄደ ነው ።
✔በውስጥ መስመር እየደረሱኝ የሚገኙት መልእክቶች እጅግ ደስ የሚያሰኙና ከስኬት ጫፍ የሚያደርሱን መሆናቸውን እያየሁ ነው ። በተለይ በየከተማው የምትገኙ የጽዋ ማኅበራት አጀማመራችሁ መልካም ነውና በዚሁ ቀጥሉበት ።
✔ ወጣቶች ከቤተሰብ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ በደንብ ምከሩበት ። ለወላጆችም በቤት ውስጥ ሁሉን አስረዷቸው ።
✔ ባለ ጊዜዎች ሆይ! በቫይበርና በስልክ እኔን መወትወቱና መለመኑ ዋጋ የለውም ።እስትንፋሴ እስክትቆም ድረስ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከዘር ፖለቲካም እስክትጸዳ ድረስ እሟገታችኋለሁ ። ወላዲተ አምላክ ምስክሬ ናት አንላቀቅም ።
በአዲስ አበባና በሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የምንገኝ ምእመናን ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት ሙዳየምጽዋትና አስራት በኩራታችንን በእጃችን ላይ በማቆየት እነዚህን በእኛው ገንዘብ እንደ ሐረር ሰንጋ እየደለቡ የወገናቸው ሞት የማይሰማቸውን የሃይማኖት ሳይሆን የፖለቲካ ሹመኞች የገቢ ምንጫቸውን ልናደርቅ ይገባል ። 

“ልጆቻችሁ አርፈው እንዲቀመጡ አድርጉ ። ያለበለዚያ ግን ወጋችሁን ነው የምንሰጣችሁ ” አይነት ንግግር በመናገር ልባችንን ያደሙትን ፓትርያርክ አባ ማትያስን አዲስ አበባ ቁጭ አድርገን የምንቀልበው እኛው ነን ። ንቡረእድ ኤልያስን ከመሬት ተነስቶ ባለፎቅ ያደረግነው እኛው ነን ። ትናንት ባዶ እግራቸውን ያለምንም ሳንቲም ባዶ እጃቸውን ሲዞሩ የምናውቃቸውን ዛሬ ግን ያለምንም የሙያ መስፈርት የአንድ ብሄርና የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ በመሆናቸው ብቻ ወደ ኢንቨስተርነት የተለወጡትን ፣ አስመጪና ላኪም የሆኑ የደብር አለቆች ፣ ጸሐፊ ፣ ቁጥጥርና ፣ ሒሳብ ሹም ፣ ወዘተ በአንድ ቋንቋ እያወሩ ከደሃው ህዝብ ተሰብስቦ በሚገባው ገንዘብ ዓለማቸውን በሚቀጩ ዘራፊዎች ላይ እቀባው ተጠናክሮ ይቀጥላል ።
እመኑኝ በአሁኑ ጊዜ የአስራት ገንዘቡን ዘወትር በማኅሌትና በሰዓታት በኪዳን ጸሎትና በቅዳሴ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የሚያመሰግነው ምስኪኑ ካህን ፍርፋሪ አይደርሰውም ። ቤሳ ቤስቲን አልኳችሁ ምንም አይደርሰውም ። በተለይ ካህናቱና ዲያቆናቱ አማራ ፣ ኦሮሞ ፣ ጉራጌና የደቡብ ተወላጅ ከሆኑ ዋጋ የላቸውም ። እጣፈንታቸው የቀጭን ጌቶቹን ጫማ በመሸከም እንደውሻ እግራቸው ስር ከመለጥመጥ በቀር አንዳች ማድረግ አይቻላቸውም ።
የሚገርመው አንድም ቀን በማኅሌቱ ላይ ሳይታዩ ቅዳሴም ሳይገቡ ቤተክርስቲያንም ሳይደርሱ እቤታቸው ቁጭ ብለው ከሁለትና ከሦስት አብያተክርስቲያናት ደሞዝ የሚበሉ ደፋሮች አሉ ። ምክንያቱም ” ምርጥ ዘርና ባለጊዜዎች ” ነን ብለው ለራሳቸው ልዩ ያልተጻፈ ህግ አውጥተው ስለሚኖሩ ።
እነዚህ አለቆች አብዛኛዎቹ የትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ታጋይ ወታደሮችም ጭምር ስለሆኑ ፖሊስን ያዛሉ ፣ አግአዚን ይጠራሉ ፣ ሰንበት ትምህርትቤቶችን እንደፈለጉ ይዘጋሉ ሲፈልጉ ያሳስራሉ ይበትናሉ ። ምክንያቱም እነሱ ካድሬና የፓርቲ አባል አይነኬ አይጠጌ ስለሆኑ ማለት ነው ።
እናም እነዚህ ሰዎች አፍ አውጥተው መንግሥትን ህዝቡን አትግደል ፣ በእስር ቤት አጉረህ በእሳት አቃጥለህ አትጨፍጭፍ አይሉትም ። ምክንያቱም እነሱም የፓርቲው አባላት ስለሆኑ ፓርቲያቸውን ከመታደግ አንጻር ምህላና ጸሎት ያዛሉ ተብሎም አይጠበቅም ። እንዲያውም እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን ቀይረው ማታ ማታ በየ መሸታ ቤቱ እንደሚንዘላዘሉት የፖሊስ ልብስ ለብሰው ሰላማዊ ሰልፈኞችን በመግደሉ በኩል ተሳታፊ አይሆኑም ብዬ ላለማመን አልሞክርም ።
እናም ወገኖቼ እነዚህን ደም መጣጮች፣ መዥገሮችና የቤተክርስቲያን ነቀርሳዎችን ከቤተክርስቲያን ትከሻ ላይ አራግፈን የመጣያው ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው ።
ለእነዚህ ዘረኞች የሆኑ ምድብ ፖለቲከኛና በስመ የሃይማኖት አባትነት በቅድስት ቤተክርስቲያን ተሰግስገው ለተቀመጡ ሰዎች የአስራት ገንዘቡን ገታ አድርገን ካልያዝነው ለእነሱ ለክ እንደ አባይ ወንዝ ያለ ነው ። ልክ እንደ ሳውዲ አረቢያ የነዳጅ ጉድጓድ ያለ ነው ። ከአሜሪካ ዶላሩ ፣ ከእንጊሊዝ ፓውንዱ ፣ ከአውሮጳ ዩሮው ፣ ከእስራኤል ሸክሉ ፣ ከስዊዝ ፍራንኩ ፣ ከአረቢያ ምድር በየሰው ቤት በእሳት ተቃጥለው የሚልኩት ሪያል የእነዚህ ማደለቢያ ነው ።
እና አስራቱን ምን እናድርግ ?
ለሱ መፍትሄው ቀላል ነው ።
1ኛ፦ ምስኪን ካህናትና ተንከራታች ደጅ ጠኚም ሆነው ረሃብ የሚያሰቃያቸውን አባቶችን እስከ ጊዜው ድረስ እነሱንም ቤተሰባቸውንም መርዳት ። በተለይ በተለይ ቤተሰብ ያላቸውንና በቤትኪራይ ውስጥ የሚኖሩትን ፣ ልጆቻቸውን የሚያስተምሩ ካህናትን በንስሐ ልጆቻቸው በኩል መርዳት ።
2ኛ፦ የቤተክርስቲያን ተተኪ የሚያፈሩትን የአብነት ትምህርት ቤት መምህራንን እና ተማሪዎችን በመርዳት ጉባኤ ቤቶች እንዳይፈቱ ማድረግ ።
3ኛ፦ እንደ ዋልድባ ያሉትን በችግር ላይ የወደቁና ሊበተኑ የደረሱ ስመጥር ገዳማትን የሚያስፈልጋቸውን በማቀረብ ገዳማቱ ሳይፈቱ እና ገዳማውያኑም ሳይበተኑ በአስራት ገነረዘቡ መርዳት ።
4ኛ፦ እንደ ደጆችሽ አይዘጉ አይነት የሚታይና የሚዳሰስ አሳማኝ ሥራ የሚሠሩ ማኅበራትን በሚገባ በተጠናከረ መንገድ መርዳትና መደገፍ ።
5ኛ፦ እንደ መቄዶንያ የአእምሮና የህሙማን መርጃ ማእከል ያሉትን ፣ ጌርጌሶኖን ፣ የወደቀ አንሱ የመሳሰሉት በየጎዳናው በረሃብ የሚሰቃዩትን አረጋውያን እና ህጻናትን እርዱበት ።
ይሄን በማድረግ በዝባዦችን እንቅጣ ።
ይህን እቀባ በመቃወም በዚህ በእኔ ፔጅ ላይ ፒሪሪም ፓራራም ታራራራም እያሉ የሚያላዝኑ እነ ገብረምናምንን ፈጽሞ አልሰማችሁም ።
አሁን በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ስላለው ግፍና መከራ ለመናገር እውነት እውነት እላችኋለሁ ሰባኪም ፣ ፖለቲከኛም ፣ አትሌትም ፣ ሆነ ግንበኛ ፣ መሆንን አይጠይቅም ። ” ጉዳዩን ለመቃወም ሰው መሆን ብቻውን በቂ ነው ” ።
እኔን የየሚደንቀኝ ይህን መልእክት እንኳ እያዩ እየተመለከቱ ሼርና ኮመንት ለመስጠት እንኳ በፍርሀት ቆፈን መታሠራቸው ነው ።
ጉዞው እስከ ቀራንዮ ነው ፣ ድል ለእምዬ ተዋህዶ !!! ወድቀት ለዘረኞች ።
ይህንንም ራሴው ዘመድኩን በቀለ ጻፍኩት ።ለማንኛውም በነጻነት እንወያይ ከስድብና ከዛቻ በራቀ መልኩ እንነጋገር ። +251911608054 የቫይበር ስልኬ ነው ። በተለይ ይህን መልእክቴን በተመለከተ ደግሞ ✔Coment መስጠትና
✔Share ማድረግ በእጅጉ ይበረታተል ።
ሻሎም ! ሰላም !
ዘመድኩን በቀለ ነኝ
ጷግሜን 4 /13/2008 ዓም
ኮሎኝ – ጀርመን

በጃዊ ባለፈው ሳምንት 37 የሚሆኑ አጋዚ ወታደሮች ተገድለዋል





ባንኮች ከ10 ሺህ ብር በላይ ወጪ እንዳያደርጉ እቀባ ተጥሏል፤ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ 2.3 ቢሊዮን ብር ደንበኞች ከባንኮች አውጥተዋል
 ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረግ በረራ ሁሉ በመከላከያ እውቅና እንዲሆን ተደርጓል
ጎንደር፤ ዛሬ ጳጉሜ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ከጠዋቱ 1፡00 ጀምሮ የመብራት፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በጎንደር ከተማ በማቋረጥ ከአየር ማረፊያ ጀምሮ በሁሉም ቀበሌዎች የአጋዚ ጦር አባላት ቤት ለቤት በመግባት መሣሪያ በመፈተሸ ሲቀሙ ውለዋል፤ የመገናኛ ዘዴዎች ሁሉ በመቋረጣቸው ብሎም ወጣቶች መነጋገር ባለመቻላቸው የተነሳ ቁጥራቸው የማይታወቅ በርካታ ዐማሮች መታሰራቸው ተሰምቷል፤ የባጃጅና የታክሲ ትራንስፖርት በግዴታ እንዲቆም ተደርጎ መረጃ ቶሎ ቶሎ እንዳይደርስም ጥረት ተደርጓል፡፡
ጎንደር በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የመከላከያና የፖሊስ አባለት የተጥለቀለቀ ሲሆን ከፍተኛ የትግሬ ወታደራዊ መከነኖች ፍሎሪዳ ሆቴል ይህ ሪፖርት እስከ ተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ስብሰባ ላይ ነበሩ፡፡
በተያያዘ ዜና አራዳ የሚባለው የገበያ አካባቢ የዐማራ ወጣቶችና በአጋዚ ወታደሮች መካከል ፍጥጫ መኖሩን መረጃው ደርሶናል፡፡ የጎንደር ወጣቶች ወንድሞቻችን አሳልፈን አንሰጥም እያሉ ሲሆን ከባሕር ዳርና ከቻግኒ ወደ ብር ሸለቆ የተወሰዱ ወጣቶች ከፍተኛ ስቅይት እየደረሰባቸው እንደሆነም እየወጡ ያሉ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
ከጎንደር ከተማ ዛሬ ነው የወጣነው የሚሉ ሰዎች እንደነገሩን የመረጃ አውታሮችን ሙሉ በሙሉ በመቆለፍ የጎንደር ከተማን ዳግም ወደ ዕልቂት ለመውሰድ የታለመ ይመስላል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ጃዊ፤ በጃዊ ነዋሪውን በማሰርና በማንገላተት ላይ በነበሩ 37 የሚሆኑ የትግሬ መከላከያ ሠራዊት አባላት በሳምንቱ መጀመሪያ አካባቢ መገደላቸውን ተሰምቷል፡፡ ቁጥራቸው ያልታወቁ ወታደሮች ደግሞ ጃግኒ ሆስፒታል ለእርዳታ መምጣታቸው የታወቀ ሲሆን እስካሁን ድረስ በአካባቢው ይህ ነው የሚባል ሰላም የለም ብለዋል መረጃውን ያቀበሉን ምንጮቻችን፡፡
አጠቃላይ፤ በአገሪቱ ያሉ ባንኮች አንድ ደንበኛ በቀን ከ10 ሺህ ብር በላይ እንዳያወጣ በአገዛዙ ታዘዋል፡፡ ባለፉት ጥቂት ቀናት ብቻ ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ከንግድ ባንኮች ደንበኞች ገንዘባቸውን ወጪ አድርገዋል፡፡ ይህም በጥቂት ቀናት ብቻ የባንኮች ካዝና ባዶ ይሆናል በሚል ስጋት አገዛዙ ደንበኞች በቀን የሚያወጡትን የገንዘብ መጠን እንዲወስ እንዳስገደደው ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በአዲስ አበባና በአንዳንድ ትልልቅ ከተሞች 10 ሺህ ብር ይባል እንጅ በብዙ የወረዳና የዞን ከተሞች ከአንድ ሺህ ብር በላይ ገንዘብ እንዳያወጡ ታግደዋል፡፡
በባሕር ዳር ያሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ለደንበኞቻቸው ለመክፈል ከግል ባንኮች እየተበደሩ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል፡፡
በተያያዘ መረጃ ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደርገውን በረራ ሙሉ በሙሉ በመከላከያ ሚንስትር እውቅና እንዲሆን ተወስኗል፡፡ አንድ የመንገደኞች አውሮፕለን ከመነሳቱ በፊት በየአካባቢው ያሉ የትግሬ መከላከያ ክፍለ ጦሮች እውቅና ከተሰጠ በኋላ ነው ተብሏል፡፡ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቬየሽን መሥሪያ ቤት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ተጠልፈው ድንበር የሚሻገሩ የአውሮፕላን አብራሪዎችን በመፍራት የሲቪል አቬሽን መስሪያ ቤት ምንም ሥራ በመከላከያ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

Two Ethiopia opposition leaders arrested



Addis Ababa – Two Ethiopian opposition leaders have been arrested and held in detention for the last two weeks, their party said on Monday, as the country grapples with rare anti-government unrest.

The authorities detained Agaw Democratic Party leader Andualem Tilahun and another senior party member, Beyilu Teshale, on August 29, but the information was only made public on Monday.

The party represents the Agaw people, an ethnic group numbering around two million based in the northern Amhara region, who have largely kept out of the trouble that has flared in Ethiopia this year.

“Andualem Tilahun was charged on allegedly public incitation against the government, which is not true,” Tesera Be, a party advisor who is currently in the United States, said.



“The charge is politically motivated to eliminate the opposition party in the region.”

The spokesperson for the regional government could not be reached for comment.

Ethiopia – regarded as among Africa’s most repressive states – has been hit by anti-government protests, starting in the central Oromo region in November last year and spreading in July to Amhara.

The government has cracked down hard on the dissent, and Human Rights Watch estimates that more than 400 people involved in the protests have been killed by security forces since November.

Be insisted the party officials were “never involved in any incitement to demonstrate against the government”, adding: “Their only objective is to obtain a regional state for the Agaw, like the Oromo or the Amhara.”

A few days before his arrest Tilahun was contacted by AFP to confirm that security forces were going from house to house in his village to persuade people not to take part in anti-government demonstrations.

source:- AFP

wanted officials