Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, October 9, 2018

በዛሬው ዕለት ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ የነበሩ የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ታጣቂዎች የመኪና አደጋ እንዳጋጠማቸው ተዘገበ።


በዛሬው ዕለት ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ የነበሩ የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ታጣቂዎች የመኪና አደጋ እንዳጋጠማቸው ተዘገበ።
 ቢቢሲ እና አንዳንድ መገናኛ ብዙሀን የትግራይ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮን ዋቢ አድርገው እንደዘገቡት ፣የትህዴን አባላት ኤርትራ ከሚገኘው ቤዛቸው ተነስተው ወደ ዛላምበሳ እየተጓዙ ሳለ ሰገንቲ አካባቢ ሲደርሱ ነው አደጋው ያጋጠማቸው።
በአደጋው የተወሰኑ ወታደሮች ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተመልክቷል።
ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች እንዳመለከቱት ዛሬ ማለዳ ከኤርትራ የተነሱ ወደ 2000 የሚጠጉ የትህዴን ወታደሮች- የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጠው ወደ ዛላምበሳ ገብተዋል።
በትጥቅ ትግል ሲንቀሳቀሱ ከቆዩ የኢትዮጵያ ድርጅቶች መካከል አንዱ የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያ ንቅናቄ መሆኑ ይታወቃል።
እንደ አብዛኞቹ የትጥቅ ድርጅቶች ውስጥ መሰረቱን በኤርትራ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የቆየው ትህዴን፣በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ሰላም መፈጠሩን ተከትሎ ከኢትዮጵያ መንግስት የቀረበውን የሰላም ጥሪ እንደሚቀበለው ማስታወቁ ይታወሳል።

Monday, October 8, 2018

አርበኞች ግንቦት7 በሃረር ከተማ ስብሰባ እንዳያካሂድ ተከለከለ


አርበኞች ግንቦት7 በሃረር ከተማ ስብሰባ እንዳያካሂድ ተከለከለ
(ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ክልሉ ለድርጅቱ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓም በጻፈው ደብዳቤ “ በጸጥታ ምክር ቤት ጉዳዩ ታይቶ በክልሉ ባለው ሃገራዊ ሁኔታ አንጻር ተገምግሞ የተጠየቀው ፍቃድ አለመፈቀዱን እንገልጻለን” ብሎአል።
ክልከላውን በማስመልከት ልክልሉ ም/ል ፕሬዚዳንት አቶ ጋቢሳ ተስፋዬና ለጸጥታ ክፍል ሃላፊው አቶ አበበ መብራቱ ስልክ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊመልሱልን አልቻሉም።
የአርበኞች ግንቦት7 የአመራር አባል የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ በሰጡን አስተያየት፣ ክልሉ የጣለው እገዳ የተጀመረውን ለውጥ የሚያጨልም ተደርጎ መታየት የለበትም ያሉ ሲሆን፣ አገሪቱ ሽግግር ላይ ስላለች አንዳንድ ቦታ ላይ ለውጡን ለመቀልበስ የሚፈልጉ ሃይሎች ሴራ መሆኑን በመረዳት ከክልሉ አስተዳደርና ከፌደራል መንግስቱ ጋር እየተነጋገርን አገር የማረጋጋት ስራ እንሰራለን ብለዋል።
ክልከላው በአርበኞች ግንቦት7 ላይ ብቻ ለምን ሆነ? ሌሎች ድርጅቶችስ ለምን አልተከለከሉም በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ “ድርጅቱ የሚከተለው የፖለቲካ አስተሳሰብ ባለፉት 27 አመታት ሲራመድ ከነበረው አስተሳሰብ ጋር የተለዬ በመሆኑ የተፈጠረ ድንጋጤ” ሊሆን ይችላል ብለዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 ቅዳሜ ጥር 3 በአዳማ የድጋፍና የውይይት ፕሮግራም እንደሚያካሂድ ታውቋል።

Ethiopia: Gov’t calls on OLF to disarm combatants


by Engidu Woldie
ESAT News (October 10, 2018)
Ethiopian government spokesperson called on the Oromo Liberation Front (OLF) to immediately disarm its combatants that were still carrying weapons.
The statement by the minister of government communication affairs, Kasahun Gofe, was made in response to a recent statement by the leader of OLF, Dawud Ibssa, who said they had not made any deal with the government regarding disarming his soldiers.
The OLF and a number of other armed opposition groups have returned to Ethiopia from their base in Eritrea after they had reached a peace deal with the government. The deal involves that the opposition lay down arms and their soldiers check into camps.
The ambiguous and controversial statement by Ibssa, who said disarming his soldiers was not part of the deal to return home, was taken by many as a refusal to disarm.
Gofe told reporters in Addis Ababa that the OLF had disarmed 1,300 of his soldiers before they crossed into Ethiopia, but said there were still soldiers that should be disarmed. It was not clear if the minister was implying that the OLF had armed combatants that were already inside the country.
The spokesperson said the question of disarming combatants is not up for negotiation. He warns that the government would take measures to disarm anyone to fulfill its duty to protect the peace of the citizenry.
Gofe said it would be tantamount to crossing the “red line” if any opposition group decides to keep arms.
The Prime Minister, Abiy Ahmed, also weighed in on the issue today saying opposition groups “do not need to be armed with weapons but ideas.”

Friday, October 5, 2018

የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዎች ታወቁ



 ይህ ሽልማት የ25 ዓመቷን ወጣት ወ/ሮ ናዲያ ሙራድን የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማትን በወጣትነቷ ያገኘኝ ሁለተኛዋ እንስት መሆን አስችሏታል። ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት የ17 ዓመቷ ፓኪስታኒያዊቷ ወጣት ማላላ ዩሳፊዛይ የ2017 እ.ኤ.አ. ሽልማትን ማግኘቷ ይታወሳል።
የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ተወላጅ የሆኑት የ63 ዓመቱ ዶ/ር ዴኒስ ሙክዌጌ በበኩላቸው ለበርካታ ዓመታት በእርስበእርስ ጦርነት በምትታመሰው አገራቸው በግዳጅ ተደፈሩው ለማኅጸን ሕመም ተጋላጭ የሆኑ ቁጥራቸው ከአስር ሽህ በላይ ለሚሆኑ ጉዳተኛ ዜጎች የህክምና እርዳታ በመስጠት ህይወታቸውን ታድገዋል።
ዶ/ር ዴኒስ ሙክዌጌ ከዚህ በፊትም የተለያዩ አህጉር እና ዓለምአቀፍ ሽልማቶችን ተሸልመዋል። በ2008 እ.ኤ.አ. በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ሽልማትን ጨምሮ በ2009 እ.ኤ.አ. የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ሰው ሽልማትን ማግኘታቸውን ቢቢሲ አክሎ ዘግቧል።

Sunday, September 30, 2018

Ethiopia: Assassination attempt on PM linked to OLF operatives as five charged with terrorism

Ethiopia: Assassination attempt on PM linked to OLF operatives as five charged with terrorism

by Engidu Woldie
ESAT News (September 28, 2018)
Ethiopian federal prosecutors today charged five individuals with planning, coordinating and executing an assassination attempt on the life of Prime Minister Abiy Ahmed at a rally on June 23, organized to show support for the reformist Premier.
Getu Girma, Birhanu Jafar, Tilahun Getachew, Bahiru Tolosa and Dessalegn Tesfaye were charged with terrorism, attempting to kill the Prime Minister. The charges allege that the defendants carried out the attempted murder on the PM with a belief that Abiy Ahmed was not popular among the Oromos and did not stand for the rights of the Oromo people. The charge says the defendants, who are linked to the Oromo Liberation Front (OLF), carried out the attempted murder with a conviction that the OLF was the rightful representative of the Oromo people, but not the Prime Minister. And that the OLF should replace the government of Abiy Ahmed.
The charge alleges that one of the masterminds of the attack was a woman by the name Genet Tamiru with an alias Toleshi Tamiru, who is based in Kenya.
It was not immediately clear if the Ethiopian government requested the extradition of the woman.
According to the charges, the defendants used two F1 bombs and a tear gas grenade. One of the defendants hurled a bomb in the direction of the podium where the Prime Minister and other dignitaries were sitting, killing two and injuring 165. The Prime Minister was swiftly escorted out unscathed.
The charges allege that the masterminds of the attack have agreed that the mission should be carried out by “operatives of the OLF who were capable of carrying out a bomb attack.”
One of the alleged coordinators of the attack, Tesfaye Urge, whom prosecutors presented as the lead mastermind of the attempted assassination in earlier court proceedings, was not mentioned in the charge filed at today’s court. Tesfaye Urge was ironically the anti-terrorism head with the Ethiopian National Intelligence and Security Service (NISS), the country’s spy agency.
Police earlier alleged that Tesfaye Urge had coordinated the attempted assassination on the PM in collusion with higher ups who were still at large.
Legal analysts say Tesfaye Urge might have been cooperating with authorities who want to get to the bottom of the operation and catch the big fish. Establishing the link between Urge and Genet Tamiru a.k.a Toleshi Tamiru, one of the alleged masterminds based in Kenya, would help in charging other key players of the assassination attempt, according to legal experts.

Ethiopia: Mass arrest in Addis Ababa unlawful: rights watchdog says


by Engidu Woldie
ESAT News
The Human Rights Council says the mass arrest carried out by police in Addis Ababa last week was unlawful.
The Council said it was troubling that over 1,200 people were detained at a military camp without charges, while they should have been arraigned before the court in 24 hours of the arrest or set free.
The council said in a report that police had beaten the detainees while rounding them up from restaurants, bars and other public places while they have committed no crimes.
The Council has called for the unconditional release of the detainees.
Police in Addis Ababa arrested close to 1,500 people a week ago in what they said was to fight organized crime. Police raided bars, restaurants as well as hookah and gambling houses in the capital. The arrests mainly targeted the youth.
Supporters and members of opposition political parties, mainly that of Patriotic Ginbot 7, have been arrested leading to suspicion the city’s police and security were targeting political opponents.
Twenty eight people have been killed in deadly ethnic violence in several districts in Addis Ababa, according to the capital’s police commissioner. Those tolls were in addition to the 27 people killed in ethnic attack in Burayu, in the outskirts of the capital. Residents displaced after the attack told reporters that the Oromos had attacked the Dorzes and other ethnic group from Southern Ethiopia.

ሶስት ወር ብቻ ለቀረው የምህረት አዋጅ ለመጠቀ በኦንላይን መመዝገብ እንደሚቻል ተገልጿል


 መንግስት በቅርቡ ባጸደቀው የምህረት አዋጅ የመጠቀሚያ ጊዜ ሶስት ወር ብቻ እንደቀረው ተገለጸ።
እስካሁን በዚህ እድል የተጠቀሙና የምህረት ሰርተፍኬት የወሰዱ ሰዎች ቁጥርም 495 ብቻ መሆኑ ታውቋል።
በተለያዩ ወንጀሎች የተከሰሱና የሚፈለጉ ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውጪ ከሆኑ በኦንላይን በመመዝገብ በወጣው የምህረት አዋጅ መጠቀም እንደሚችሉም ተመልክቷል።
በምሕረት አዋጁ መሰረት በማረሚያ ቤት የሚገኙና ከማረሚያ ቤት ውጭ የሆኑ፣ከግንቦት 30 ጀምሮ የምህረት ሰርተፍኬት እየተሰጣቸው መሆኑ ተገልጿል።
እስከ ህዳር 30/2011 ይህው እንደሚቀጥልም ተገልጿል፣በውጭ ሃገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በጠቅላይ አቃቤ ሕግ ድረ ገጽ www.Fag.gov.et እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።
በሐገር ክህደት፣በሽብር፣ሕገ መንግስታዊውን ስርአት በሃይል በመናድ፣የጦር መሳሪያ ይዞ ማመጽ በሚል የተከሰሱ ሰዎች በዚህ አዋጅ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ተመልክቷል።
በኩብለላ ወንጀል የተከሰሱና የሚፈለጉ ወታደሮች፣በስለላ ወንጀል የተጠረጠሩና የሚፈለጉ ዜጎች፣ የሐሰት ወሬ በማውራት ሕዝብን አነሳስታችኋል በሚል የተከሰሱና የሚፈለጉ ጋዜጠኞችና ሌሎች ዜጎችም በምህረት አዋጁ መሰረት ከክሳቸው ነጻ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
በዚህና መሰል ክሶች የተከሰሱና የሚፈለጉ ሁሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጋር በአካል በመቅረብ ወይንም በኦንላይን በማመልከት ከክሳቸው ነጻ መሆናቸው የሚያረጋጝጥ ሰርተፍኬይ ይሰጣቸዋል ተብሏል።
ከግንቦት 30/2010 ጀምሮ ተግባራዊ የሆነው ይህ አዋጅ የሚቆየው ለሶስት ወር ያህል ማለትም እስከ ህዳር 30/2011 ድረስ እንደሆነም መረዳት ተችሏል።

ታማኝ በየነ ከ8 መቶ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት የምስጋናና የአክብሮት የምሳ ግብዣ አደረገ

8 መቶ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት አንድ ላይ ሲገናኙ ።
አርቲስት እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነ ከተወዳጆ ባለቤቱ ፋንትሽ በቀለ ጋር በመሆን !!!
የቀድሞ የኢትዮጵያ የጦር ሰራዊት አባላት አሁን ኢትዮጵያን እያስተዳደረ ያለው መንግስት የተቀማነውን ስማችንንና ክብራችንን ያስመልስልን ሲሉ ጥያቄ አቀረቡ።
የሰራዊት አባላቱ ጥያቄያቸውን ያቀረቡት በአርቲስትና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ታማኝ በየነ አማካኝነት መሆኑም ታውቋል።
አርቲስትና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ታማኝ በየነ 800 ያህል ለሚሆኑ የሰራዊቱ አባላት የምስጋናና የአክብሮት የምሳ ግብዣ ማድረጉም ተመልክቷል።
ከ22 አመታት በኋላ ወደ ሃገሩ የተመለሰው አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ከተለያዩ የህብረትሰብ ክፍሎች ጋር በመገናነት ምስጋናና ክብር በመስጠት ግብዣ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ታማኝ በየነ ዛሬ ላይ ደግሞ የምስጋናና የአክብሮት የምሳ ግብዣ ስነስርአቱን ለቀድሞ የጦር ሰራዊት አባላት አድርጓል።
800 የሚሆኑ የሰራዊቱ አባላት ተገኝተዋል በተባለበት በዚህ ስነስርአት ላይ የቀድሞ የምድር ጦር፣የባህር ሃይል፣የአየር ሃይል፣የአየር ወለድና ሌሎች የሰራዊቱ አባላት ተገኝተዋል።
የጦር ሰራዊት አባላቱ በስነስርአቱ ላይ ለሃገራቸው የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል።
በተለይም እኛ የሃገራችንን ድንበር ለማስጠበቅ መስዋዕት ከፍለን እንጂ ሃገር ለመውረር አልዘመትንም ሲሉ ተናግረዋል የቀድሞ ጦር ሰራዊት አባላት።
ከተለያየ ክፍል የወጡ የሰራዊቱ አባላትም መፈክሮቻቸውን ያስተላለፉና ለሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ታማኝ በየነ ያላቸውን አክብሮት በመግለጽ በቀጣይም የተነጠቅነውን ስማችንና ክብራችንን አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ መንግስት እንዲያስመልስልን ሲሉ ጥያቄያቸውን በአርቲስት ታማኝ በየነ በኩል አቅርበዋል።
በስነስርአቱ ላይ የተገኙት የጦር ጉዳተኞችም የያዝነውንም ተነጥቀናል፣ጥያቄያችን ሊሰማና መፍትሄ ሊሰጠን ይገባል ሲሉ በታማኝ በየነ በኩል ለመንግስት አስተላልፈዋል።
በስነስርአቱ ላይ የቀድሞ ሰራዊት አባላት በክፍሎቻቸው አማካኝነት ለአርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ስጦታ አበርክተውለታል።

ትክክለኛው የቅድስት አርሴማ ስዕል እና ቅድስት አርሴማ ተብለው የሚሰራጩ የሌሎች ቅዱሳን አንስት ሥዕላት!

ትክክለኛው የቅድስት አርሴማ ስዕል እና ቅድስት አርሴማ ተብለው የሚሰራጩ የሌሎች ቅዱሳን አንስት ሥዕላት!
በሀገራችን በሀበሾች በስፋት የቅድስት አርሴማ እየተባለ የሚሰራጨው ሥዕል የቅድስት ሉሲያና የቅድስት ባርባራ ናቸው፡፡
አንዳንዶች «አንዴ በልቦናችን ተስሏል» ብለው በዛው መቀጠልን የሚመርጡ ሰዎች አሉ:: በእርግጥ የሚያስረዳ ሰው ጠፍቶ ባለመረዳት ቢሆን ኩነኔ አይሆንም ብዬ አስባለሁ፡፡ ከተረዳን በኋላ ግን የቅድስት ሉሲያን ቅድስት ሉሲያ፤ የቅድስት አርሴማን ደግሞ ቅድስት አርሴማ ብለን ቢቻል ስለሁሉም ቅዱሳን ተምረን ከሁሉም በረከት መቀበል ይሻላል ወይስ ተረድተንም እንዳልተረዳ ሰው የቅድስት ሉሲያንና የሌሎችን ስዕላት ሁሉም ቅድስት አርሴማ እንደሆኑ አድርጎ መቀጠል?
"ጌታችን በወንጌሉ እውነትን እውነት፤ ሐሰትን ሐሰት ብለን እንድንናገር ያስተምረናል፡፡ በመሆኑም እውነተኛውን የቅድስት አርሴማን ወካይ የሆነውን ሥዕሏን እንድንጠቀም ለማሳሰብ እፈልጋለሁ፡፡ ከዚያም ሲቀጥል በሥዕሉ ላይ የተወከሉት ሌሎች ስለክርስቶስ ሲሉ ሰማእትነት የተቀበሉትን ቅዱሳንን እንድናከብር ያስፈልጋል፡፡"
ትክክለኛው የቅድስት አርሴማ ስዕል ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እዚህ አስረድቷል፤ ከፍታችሁ ማየት ትችላላችሁ፦ http://www.danielkibret.com/2014/10/blog-post_8.html?m=1q


Saturday, September 29, 2018

በመስቀል አደባባይ ሰኔ 16/2010 የተሰነዘረው የቦምብ ጥቃት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል ነው ተባለ

በመስቀል አደባባይ የተሰነዘረው የቦምብ ጥቃት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል ነው ተባለ

 በአዲስ አበባ ከተማ ሰኔ 16/2010 በመስቀል አደባባይ የተሰነዘረው የቦምብ ጥቃት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድን ለመግደል የተቀነባበረ መሆኑን አቃቤ ሕግ ገለጸ።
ድርጊቱን የፈጸሙትም የኦሮሞ ነጻነት ግንባር/ኦነግ/ ደጋፊዎች መሆናቸውም ተመልክቷል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ ዛሬ በይፋ ክስ መመስረቱም ታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከሱሉልታ ተነስተው ጥቃቱን መፈጸማቸውም ተመልክቷል።
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ላይ ግድያ ለመፈጸም የተንቀሳቀሱት ግለሰቦች ኬንያ ላይ የተቀነባበረውን ርምጃ ሱሉልታ ላይ መክረው አዲስ አበባ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ መንቀሳቀሳቸውን ከጠቅላይ አቃቤ ሕግ ሪፖርት መረዳት ተችሏል።
ጌቱ ግርማ፣ብርሃኑ ጃፋር፣ጥላሁን ጌታቸው፣ባህሩ ቶላና ደሳለኝ ተስፋዬ የተባሉት ግለሰቦች ዛሬ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል በተቀነባበረው ሒደት ውስጥ በተለያየ ደረጃ ተሳታፊ ሆነው በመገኘታቸው ነው ተብሏል።
ሰኔ 16/2010 በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የተቃጣውን ግድያ ያቀነባበረችው ኬንያ የምትገኝ ገነት ታምሩ በቅጽል ስሟ ቶሎ ሺ ታምሩ የምትባል እንደሆነችም በክሱ ተመልክቷል።
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ላይ ግድያ በመፈጸም በሃገሪቱ በመታየት ላይ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ ተንቀሳቀሱ የተባሉት ሰዎች “ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሰልፍ መካሄድ የለበትም፣ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢሕአዴግ ነው፣ሰልፉ በአሜሪካ ኮንግረስ የጸደቀውን ኤች አር 128 ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል”የሚሉ መነሻዎችን ይዘው መንቀሳቀሳቸውን አቃቤ ሕግ ገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሌላቸውና እንደማይፈለጉ አድርጎ ለማሳየትም ጥቃቱ መቀነባበሩ ተመልክቷል።
በዚህም መነሻነት አንደኛው ተከሳሽ ጌቱ ግራም ኬንያ ከምትገኘው ገነት ታምሩ ጋር በመገናኘት ሰልፉ እንዳይካሄድና እንዲበተን መሞከራቸውን አቃቤ ሕግ ገልጿል።
ጌቱ ግርማ ከገነት ታምሩ መመሪያውን ከተቀበለ በኋላ ከ2ተኛው ተከሳሽ ብርሃኑ ጃፋር ጋር ሱሉልታ ላይ ስለተልዕኮው አፈጻጸም መምከራቸው ተገልጿል።
በዚህም ብርሃኑ ጃፋር ቦምብ እንዲያዘጋጅና ቦምቡንም የሚወረውር ሰው እንዲያፈላልግ በተሰጠው መመሪያ መሰረት ሶስተኛውን ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸውን ሒደቱ ውስጥ ማስገባቱን አቃቤ ሕግ ገልጿል።
2ኛው ተከሳሽ ብርሃኑ ጃፋር ሁለት ኤፍ ዋን አንድ የጭስ ቦምቦችን በማዘጋጀት በአንደኛው ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ቤት ማስቀመጣቸው ተገልጿል።
በሰልፉም ዕለት ተከሳሶቹ ከሱሉልታ በመነሳት በጌቱ ግርማ አማካኝነት የቦምብ ጥቃቱን መፈጸማቸው ተዘርዝሯል።
እነዚህ ግለሰቦች ሐገሪቱ መመራት ያለባት በኦሮሞ ነጻነት ግንባር/ኦነግ/ነው በሚል አላማ መንቀሳቀሳቸውም ተመልክቷል።
በኢትዮጵያ የተያዙት ቦምብ ወርዋሪዎችም ሆኑ በኬንያ ያለችው አቀነባባሪ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ጋር ግንኙነት ይኑራቸው አይኑራቸው በክሱ ውስጥ የተጠቀሰ ነገር የለም።
በጥቃቱ 2 ሰዎች ሲገደሉ ከ150 በላይ መቁሰላቸው ይታወሳል።
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ከዚህ የቦምብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መታሰራቸው የተገለጸ ቢሆንም በዚህኛው ክስ ውስጥ ግን አልተካተቱም።
አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ድርጊቱን ያቀነባበሩት ካልተያዙ የበላይ አለቆቻቸውና ከሌሎች ግለሰቦች ጋር መሆኑን ፖሊስ ፣መግለጹ ይታወሳል።
አቃቤ ሕግ በእኚህ የቀድሞ ባለስልጣንና በኬንያ በምትገኘው ገነት ታምሩና በሌሎች መካከል ያለውን ግንኙነት መሰረት አድርጎ በቀጣይ ክስ ሊመሰርት እንደሚችልም የህግ ባለሙያዎች ይገልጻሉ።
አቶ ተስፋዬ ኡርጌ የወንጀል ሒደቱን በዝርዝር አጋልጠው ከተናዘዙ በተያዙና ባልተያዙ ግለሰቦች ላይ በአቃቤ ሕግ ምስክርነት ከቀረቡ ከክሱ ሊወጡ እንደሚችሉ የሕግ ባለሙያዎቹ ይናገራሉ።

Four local officials from Benishangul killed in Wollega


by Engidu Woldie
ESAT News (September 27, 2018)
Four local officials from Benishangul Gumuz region in Western Ethiopia were killed in an ambush in Wellega, Oromo region.
The officials were on their way back to Kemash Zone from a security meeting in Wellega when they were attacked by unidentified gunmen in Gimbi, West Wellega, the report by the Ethiopian Television said.
The report quoted the regional police commissioner, Seyfedin Harun, as saying that the four officials of Kemash Zone were in Wellega for a joint regional security meeting with their counterparts from the Oromo region on Tuesday and were ambushed and killed on Wednesday as they were returning to Kemash.
The commissioner said a search is underway to catch the gunmen.
Tensions remain high in Kemash town following news of the killings and businesses and local government offices are closed.
The commissioner said there are elements in the region that were bent on inciting violence between the people in Oromo and Benishangul regions.

wanted officials