Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, January 1, 2019

ኢትዮጵያውያኑ ‘የይለፍ ፍቃድ የላችሁም’ በሚል በትግራይ በኩል ኤርትራ እንዳይገቡ ተከለከሉ

Image may contain: one or more people, sky and outdoor


ከዛሬ ጠዋት 12 ጀምሮ በዛላምበሳ በኩል ወደ ኤርትራ በመጓዝ ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ተጓዦች እንዳይገቡ ተከለከሉ፡፡
ዲደብሊውና ቢቢሲ እንደዘገቡት ክልከላው የተደረገው ፍቃድ የላችሁም በሚል ነው፡፡ የኢትዮጵያና ኤርትራ መንግስታት በደረሱት ስምምነት መሰረት ባሳለፍነው መስከረም ወር ድንበሮቻቸውን ከፍተው የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ካንዱ ወደ ሌላዉ ሲመላለሱ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
የዛላንበሳ ነዋሪዎች እንዳስታወቁት እስከ ዛሬ ድረስ የኤርትራም ሆነ የኢትዮጵያ መንግሥታት የይለፍ ፍቃድ አይጠይቁም ነበር፡፡ በዛሬው ዕለት ግን በኤርትራ በኩል የይለፍ ፍቃድ በመጠየቁ በርከት ያሉ መኪኖች በድንበሩ ቆመው እንደሚገኙ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉለመከዳ ኮምኒኬሽን ፅሕፈት ቤት የፕሬስ ባለሙያ አቶ የዕብዮ ሙልጌታ ለDW ተናግረዋል፡፡ የጉሎመኸዳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ገብረህይወት ገብረየሱስ በበኩላቸው የዛላምበሳ ድንበር ባልታወቀ ምክንያት ከፌደራልመንግሥት ፍቃድ ለሌላቸው ተጓዦች መከልከሉን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ድንበር በኩል “ከፌደራል መንግሥት ፈቃድ መያዝ አለባችሁ” የሚል ምላሽ እንተደተሰጣቸውና ከኤርትራ በኩል ደግሞ የይለፍ ወረቀት እየተዘጋጀ መሆኑን” ነዋሪዎች ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ያለ ይለፍ ወረቀት ከሁለቱም በኩል መንቀሳቀስ የማይቻል ሲሆን በተጨማሪም በኤርትራ በኩል ድንበር ጥበቃውን እንዲያጠናክሩ በድንበር ጥበቃ ላይ ለተሰማሩ ከላይ መመሪያ እንደተሰጣቸው እየተነገረ ነው፡፡

Monday, December 31, 2018

አርበኛ መሳፍንት ‹‹በወልቃይት ጠገዴ ያልተነገረና የኢትዮጵያ ህዝብ በውል ያላወቀው መጠን የለሽ በደል ተፈፅሟል›› አሉ

Image may contain: 1 person, standing and outdoor


አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ህወሀት በትጥቅ ትግሉ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ላይ ሲፈፅም የነበረውን ግፍ በመቃወም በረሃ ገብተው ህወሃትን ሲፋለሙ በትግራይ የጉድጓድ እስር ቤት ታስረው ከፍተኛ ስቃይ ደርሶባቸዋል፡፡ ይሁንና እስር ቤቱን ሰብረው በመውጣት እድሜያቸውን ሙሉ ሲፋለሙ የቆዩት እኚህ አርበኛ መንግስት ያቀረበውን ጥሪ ሰምተው በቅርቡ ከበረሀ ወጥተዋል፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግል ጓዶቻቸውን ይዘው ከመንግስት ጋር ለመነጋገር ወደጎንደርና ባህር ዳር መምጣታቸውን ከዚህ ቀደም በዘሃበሻ ዜናዎቻችን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ አርበኛ መሳፍንት ዛሬ ለንባብ ከበቃውና በጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ከሚዘጋጀው በረራ ጋዜጣ ጋር ቃለምልልስ አድርገው ነበር፡፡
በዚህ ቃለምልልስ ትግል ስለጀመሩበት ምክንያት ሲገልፁ ‹‹የህወሃት ሰዎች ለአካባቢው ህዝብ ያላቸው እይታ ገና ከጠዋቱ ጀምሮ በጥላቻ የተሞላ ነበር፡፡ በአማራ ላይ የነበራቸው ጥላቻ ጫፍ የደረሰ ስለነበር አንተ የመሳፍንት ዘር፣ የጨቋኝ ቤተሰብ ስለሆንክ ነው መሳፍንት የተባልከው እያሉ በጥላቻ ያዩኝ ነበር›› ካሉ በኋላ በዚህ መልኩ በእሳቸውና በአማራው ህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል ሲበዛ በ22 አመታቸው ወደትግል መውጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ በትግል ትንሽ ከቆዩ በኋላ በህወሀት እጅ ወድቀው የስቃይና የመከራ ጊዜ እንዳሳለፉ የተናገሩት አርበኛ መሳፍንት መስከረም 17 ቀን 1981 ከለሊቱ ስምንት ሰአት አምልጠው እንደወጡም ገልፀዋል፡፡
ከእስር አምልጠው ዳባት ርቀው እየኖሩ እያለ ህወሀቶች በ1983 አገሪቱን እንደተቆጣጠሩና መሳሪያቸውን እንዲያወርዱ ተስማምተው የግብርና ኑሯቸውን ጀምረው እንደነበር አስረድተዋል፡፡ ይሁንና ግብርና እንደጀመሩ የቢሮክራት ልጅ ተብለው እርሻቸው እንደተቀማባቸው የተናገሩት አርበኛው ይህን በደል ችለው በመኖር በ1997 ቅንጅትን ወክለው ምርጫ መወዳደራቸውንም ያወሳሉ፡፡ በምርጫው በዳባት ሙሉ በሙሉ ምርጫውን ማሸነፉን ተከትሎ አፈሙዝ ሲነሳባቸው በድጋሚ ለትግል ወደበረሃ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡ በረሃ ከገቡ በኋላም በህዳር ወር 1999 ህወሀት ሽፍታ በመላክ ልታስገድላቸው እንደሞከረችና በተአምር እንደተረፉ ያስረዱት አርበኛ መሳፍንት ሲናገሩ ‹‹ህዳር 19 ቀን 2009 ይፋዊ ውጊያ በህወሃት ተከፍቶብኝ ከእነሱም ከእኛም ወገን በርካታ ሰው ሞቷል፡፡ በዚያ ውጊያ የምወደው አባቴ ተታኩሶ በኋላም ተገድሎብኛል፡፡ እኔም ከብዙ ጡርነት ነው ያመለጥኩት›› ብለዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ህወሃት ዲሽቃና ከባድ መሳሪያ ሁሉ ተጠቅሞ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
አሁን በምን ስምምነት ከበረሃ ወጥተው ከተማ እንደገቡ ሲጠየቁ በሰጡት ምላሽ ደግሞ ‹‹መሬት የያዘ ነገር የለም፡፡›› ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል አመራሮች ከውጭ አገር እስኪመለሱ እየጠበቁ መሆኑን የተናገሩት አርበኛው ከበረሃ የመጣው ወጣት ሀይል እየተንገላታ በመሆኑም ቅሬታቸውን አሰምተው ‹‹ወደፊት በምን አይነት መልኩ ህዝብና አገር ሊጠቅም በሚችል ተግባር ላይ ልንሰማራ እንደምንችል በዝርዝር ተወያይተን ለህዝባችን እንገልፃለን›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በተለይ በወልቃይት ጠገዴ ህወሃት የፈፀመውን ሲገልፁ ደግሞ ‹‹በወልቃይት ጠገዴ አካባቢ ወጣቱን አጥፍተውታል፡፡ ነባሩን ህዝብ እያሰሩ፣ እያሳደዱና እየገደሉ ከርስቱ አፈናቅለው የራሳቸውን ህዝብ አስፍረውበታል፡፡ ያልተነገረና የኢትዮጵያ ህዝብ በውል ያላወቀው መጠን የለሽ በደል ተፈፅሟል›› ብለዋል፡፡

Sunday, December 30, 2018

አቡነ መልከጼዴቅ ነገ ኢትዮጵያ ይገባሉ


ቅዱስ ሲኖዶስ ወደ አንድ ከመጠቃለሉ በፊት በውጭ በነበረው ሲኖዶስ በዋና ጸሐፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት አቡነ መልከጼዲቅ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ ተሸኝተዋል:: ነገ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል::

አጭር የሕይወት ታሪክ
አቡነ መልከጼዴቅ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብረታቦር አውራጃ  በፋርጣ ወረዳ፣ ልዩ ስሙ መገንታ ቁስቋም በተባለ ሥፍራ ከአባታቸው ከቄስ ወርቅነህ ትኩና ከእናታቸው ከወ/ሮ አንጓች አታሌ እንደ ኢትዮጵያ አቶጣጠር በ1916 ዓ/ም ተወለዱ። ገና የአስራ አንድ ዓመት ልጅ እያሉ በ1927 ዓ.ም ማዕረገ ድቁናን ከብፁዕ አቡነ አብርሃም ተቀበሉ፤ የአስራ አምስት ዓመት ወጣት ሳሉ ጣና በምትገኘው በክርስቶስ ሠምራ ገዳም መነኮሱ። በ1938 ዓ.ም ማዕረገ ቅስናን ከብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ተቀበሉ። ብፁዕ አባታችን ዘመናዊ ትምህርትን ከመንፈሳዊው ትምህርት ጋር አጠናክረው ለመማር በ1939 ዓ.ም ወደ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ገብተዋል። ከወዳጅ ቤተ ክርስቲያን በተገኘው ከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርት ዕድል ቆስጠንጢንያ በሚገኘው የግሪክ ኦርቶዶክስ ኢኩሚኒካል መንበረ ፓትርያርክ ተልከው ልዩ ስሙ ሐልኪ በሚባለው የሥነ መለኮት (የቲኦሎጂ) ኮሌጅ በዲግሪ ተመርቀዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የሥነ መለኮት (የቲኦሎጂ) ባለድግሪ ካህን በመሆንም በ1949 ዓ.ም. ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል።
ብፁዕ አባታችን መደበኛ ሥራቸውን የጀመሩት አዲስ አበባ በሚገኘው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በመምህርነት ተመድበው የተማሩትን በማስተማር ነበር። በ1950 ዓ.ም. የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ዳይሬክተርና መምህር ሆነው እንዲሠሩ ተመርጠውና ተሹመው ሙያቸውን በተግባር ገልጠዋል። በ1952 ዓ.ም. የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ልዩ ካቢኔ ሲቋቋም ለንጉሠ ነገሥቱ የሚቀርቡትን መንፈሳዊ ጉዳዮች ለማጣራት በኃላፊነት ተመርጠው የመንፈሳዊ ጉዳዮች መምርያ ዳያሬክተር ሆነው ተሹመዋል። ወዲያውም የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀሥልጣናት ሆነው ተሹመው ሁለቱንም ከፍተኛ ኃላፊነቶች በመሸከም እስከ 1966 ዓ.ም ድረስ ለ14 ዓመታት ከፍተኛ የሥራ ውጤት አሳይተዋል።
ብፁዕ አባታችን አቡነ መልከጼዴቅ ፈጣሪ በሰጣቸው እውቀትና ጥበብ እስከ ዛሬው ዕለት ድረስ 21 መጻሕፍትን በተለያዩ ቋንቋዎች ደርሰው ያሳተሙ ሲሆን 11 የሚሆኑ ያልታተሙና ለህትመት የተዘጋጁ መጻሕፍቶችን ደርሰዋል። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በ1983 ዓ.ም. ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ እጅ ጵጵስናን ተቀብለዋል።
ብፁዕ አባታችን አቡነ መልከጼዴቅ ላበረከቱት ከፍተኛ ሐይማኖታዊ፤ ሰብአዊና ሀገራዊ አገልግሎቶች ከሀገራችንና ከተለያዩ የውጪ ሀገራት በርካታ የክብር ሽልማቶችንና ልዩ የክብር አልባሳትን ተጎናጽፈዋል። ዋናዋናዎቹን ለመጥቀስ ያህል፦
– የኢትዮጵያ የክክብር ኮከብ ባለ አምበል 1ኛ ደረጃ
– የዳግማዊ ምኒልክ የክብር ኮከብ ባለ አምበል 1ኛ ደረጃ
– የቅድሥት ሥላሴ ኒሻን የኮማንደር ደረጃ ባለ ፕላኩ
– የቅድሥት ሥላሴ ኒሻን የኮማንደር ደረጃ ከነ ፕላኩ
ልዩ ሽልማት፦
ከግሪክ መንግሥት
ከግሪክ ቤተ ክርስቲያን
ከእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን (በግሪክ)
የላዝሩስ ኒሻን ከኦስትርያ(ቪዬና)
ጥቄር ካባ ባለራስ ማዕርግ በሙካሽ የተሠራ፤
ቀይ ከፋይ ላይ ወርቅ የተጠለፈበት ካባ እንዲሁም በሙካሽ የተሰራ ቀሚስ
ከወርቅ የተሰራ የእጅ መስቀል ናቸው።
ብፁዕ አባታችን አቡነ መልከጼዴቅ ከሚወዷት ሀገር የተሰደዱት በሥርዓት መጓደል፣ በቀኖና መፍረስ፣ የመንግሥት ቀጥታ በሐይማኖት ተቋም ውስጥ ጣልቃ መግባትና ፓትርያርክ በሕይዎት እያለ በሌላ እንዲተካ ከማድረግ ጀምሮ ከተራ ንፍቀ ዲያቆን እስከ መንበረ ፓርትያርክ ያለው የሥራ ቦታ እየተቀማ ከሥራቸው እያባረረ በምትካቸው ብቃት የሌላቸውንና ከሃይማኖቱ ጋር ቁርኝት ያልፈጠረባቸውን ካድሬዎችን በማስገባት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግ ተጥሶ፣ ደንቡ ፈርሶ፣ ቀኖናው ተዛብቶ፣ ስርዓቱ ደፍርሶ የግፉ ዋንጫ ሞልቶ ሰለፈሰሰ ነበር።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በስደት ዓለም በብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ፓርቲያሪክ መሪነት እሳቸው ዋና ጸሐፊ በመሆን ሕጋዊው ሲኖዶስ በስደቱ ዓለም እንዲጠናከርና እንዲስፋፋ ብርቱ ጥረት አድርገዋል። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የሕጋዊው ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የካሊፎርኒያ ግዛት ሊቀ ጳጳስ መደበኛ ጽሕፈት ቤታቸውን ካሊፎርንያ በርክሊይ በማድረግ እንደዘንግ እየተወረወሩ በመላው አሜሪካ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ መካከለኛው ምሥራቅ፣ የሩቅ ምሥራቅ፣ ኢሲያ፣ በመላው አውሮፓና በደቡብ አፍሪካ በመሄድ ወገኖቻቸውን አሰባሰቡ፤ አጽናኑ፣ አበረታቱ ገንዘብም ለምነው ቤተ ክርስቲያን አሳነጹ፣ በጸሎታቸውም ተጉ። እንደ ሐዋርያው ጳውሎስም ደጋግመው ጎበኟቸው። በፅኑ መሠረት ላይ የጸኑትን አብያተ ክርስቲያናት በሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ስር እንዲተዳደሩ አደረጉ።
ብጹዕ አቡነ መልከጼዴቅ አማርኛ፣ እንግሊዘኛ፣ ግዕዝ፣ ግርክኛ፣ ቱርከኛ፣ አረብኛና ትግሪኛ ቋንቋ የሚችሉ በመሆናቸው መጽሐፍትን ለማንበብ፣ እንግዶችን ለማነጋገር፣ እንዲሁም በየቤተ ክርስቲያኖቻቸው ተጋብዘው ሲሄዱ በቋንቋቸው በመናገር ብዙዎቹን ያስደመሙ የቋንቋ ባለጸጋ ናቸው።
ብጹዕነታቸው በካሊፎርኒያ ግዛትና በአለም አቀፍ ደረጃ ላደረጉት ከፍተኛ ሐይማኖታዊና ሰብአዊ እንቅስቃሴ ስደተኛው እምነቱን እንዲያጸና፣ ሐይማኖቱን እንዲጠብቅ፣ በጥሩ ሥነምግባር እንዲታነጽ፣ ብርቱና ጠንካራ ሠራተኛ እንዲሆን፤ እንዲሁም ወላጆች ልጆቻቸውን በትክክለኛው ጎዳና እንዲያሳድጉ፤ ልጆችም በሐይማኖታዊ ምግባር ታንጸው ጠንካራና መልካም ዜጋ እንዲሆኑ በማስተማር ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከአምስት የካሊፎርንያ ግዛት ከንቲባዎች፦ ከኦክላንድ ሊቢ ሼፍ፣ ካሳንፍራንሲስኮ ኤድዊን ሊ፣ ከሳን ሆዜ ሳም ሊካርዶ፣ ከበርክሊ ቶም ባትስ፣ እና ከሳንታ ክላራ ሊዛ ጊልሞር ፤ ከሶስት የሕዝብ ተወካዮች፦ ከናንሲ ፐሎሲ፣ ከባርብራ ሊ፣ እና ከማይክል ሆንዳ፤ ከሁለት የጉባኤ አባላት፦ ከዳያን ፊንስታይን እና ከካሜላ ሃረስ እንዲሁም ከካሊፎርንያ ግዛት የሸንጎ አባል ሮን ቦንታ የምስክር ወረቀትና የከፍተኛ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ እንዲሆኑ ወስነው የትውልዳቸው ቀን ጁላይ 19 በየአመቱ የአቡነ መልከጼዴቅ ቀን እንዲሆን ሰይመውላቸዋል። በዚህም የተነሳ ብጹዕነታቸው ከትውልድ ሀገራቸው ውጪ በስደት ዓለም ፈጣሪያቸውን፣ ተከታይ የመንፈስ ልጆቻቸውን፣ ሀገራቸውን ያስከበሩ ምሉዕ አባት ናቸው።

ብጹዕ ሊቀጳጳስ አቡነ መልከጼዴቅ ለክርስቶስ ራሳቸውን የሰጡ፣ የጳውሎስን አረአያ የተከተሉ፣ እንደ አቡነ ጴጥሮስ የተጋደሉ፣ የእግዚአብሔር ፍጡር የሆነ የሰው ልጅ ምንም ዓይነት በደል እንዲደርስበት የማይፈልጉ፤ ኃጢያትን የሚጠየፉ፣ ከምንም በላይ ክርስቲያኖች እርስ በእርሳቸው ተከባብረው፣ ተፈቃቅረው፣ እራሳቸውን በመፅሐፍ ቅዱስ ቃል አንጸው፣ በፈጣሪ እምነት ጸንተው፣ እንዲቆዩ ያስተማሩ አባት ናቸው። በሕይወት ዘመናቸው ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጸኦ ባይመጥንም ማስታወሻቸው ይሆን ዘንድ ይህንን ቤተ መጽሐፍት ወመዘክር የብጹዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሊቀጳጳስ ቤተ መጽሐፍት እንዲሆን በእሳቸው ስም የተቋቋመው የመልከጸዴቅ ፋውንዴሽንና የኦክላንድ መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በወሰነው ውሳኔ ግንቦት 4 ቀን 2010 ዓ.ም. (May 12, 2018) በብጹዕ አባታችን አቡነ መልከጼዴቅ ተመርቆ ተከፍቷል። መጻሕፍት ቤቱ ብጹዕ አባታችን ያነበቧቸውና የጻፏቸው መጻሕፍቶችና ማስታወሻዎች እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምትመራባቸውን ቀኖናዎች፣ ታሪኮች፣ የታተሙና ያልታተሙ መጻሕፍቶቿ የሚሰበሰቡበትና ለአንባቢ፣ ለአጥኝ፣ ለተመራማሪ እንዲመቻች ለመድረግ ነው። እንኳን ደስ ያላችሁ:
Condensed Biography of His Eminence Archbishop Abune Melketsedek
His Eminence Archbishop Abune Melketsedek was born in the locality of Megenta Kusquam, in the district of Debre Tabor, province of Gondar, Ethiopia, to his father Priest Workneh Teku and his mother Mrs. Anguach Atale on July 24, 1924. In 1935, at the tender age of eleven, His Eminence was ordained a deacon by Bishop Abune Abraham. Four years later, absolving himself of the secular life he never had much care for, he committed himself to the services of the Lord and became a monk at the age of 15 at the convent of Kristos Semra, near Lake Tana. He was ordained a priest in 1946 by His Eminence Abune Yishak.
In 1948, with the natural inclination to supplement his ecclesiastical training, His Eminence enrolled in Kidist Selassie Theological College. During his fourth year, under the auspices of the Greek Orthodox Ecumenical Patriarchate, he attended Holy Theological School of Halki, the Patriarchate’s main School of Theology in Turkey, and returned to his country in 1958 as the first Ethiopian theologian cleric.
His Eminence joined the workforce as an instructor at the Theological College of the Holy Trinity Cathedral in Addis Ababa, Ethiopia, where he was later appointed Director of Sewasew Berhan St. Paul School of Theology in 1958. In 1960, His Eminence was chosen to serve on Emperor Haile Selassie’s Crown Council as Director of Religious Affairs, overseeing the vetting of all religious matters that come before the Emperor. Immediately following this appointment, he was also appointed Arch-hierarch of Menbere Tsebaot Kidist Selassie Cathedral. He simultaneously filled both positions until 1974.
His Eminence is a prolific writer and a scholar who made a significant contribution to the Ethiopian Orthodox church by publishing canonical books that are fundamental to the Ethiopian Orthodox faith. He has authored 32 books, 21 of which were published, and 11 remain in manuscript form. In 1983, with His Holiness Patriarch Abune Merkoriwos officiating, His Emminence Abune Melketsedek was enthroned as Archbishop. In recognition of his tireless efforts His Eminence has received the following honorary awards and vestments from his country and different foreign countries over his lifetime.
The Order of the Star of Ethiopia (1st grade/Grand Cross)
The Order of Emperor Menelik II (1st grade/Knight Grand Cross)
The Order of the Holy Trinity (Commander Grade)
Honorary Awards from:
The Greek government
Church of Greece
Church of Alexandria in Greece
Lazarus Medal from Austria
Vestments including,
Gold-embroidered black velvet cloak
Gold-embroidered red velvet cloak and cassock
Gold blessing cross
His Eminence was exiled from his beloved country in 1992 after bearing witness to the upheaval that was brought on the church by the government; its interference with church governance, the enthronement of a new patriarchate while the incumbent patriarch was still alive, its replacement of clergy with unqualified persons and its egregious violation of the cardinal tenets of the Ethiopian Orthodox church. He openly criticized the government and produced writings of opposition along with other church leaders, which resulted in the government’s pursuit of him. Consequently, he fled the country on October 20th, 1992 taking refuge in the United States.
Along with a group of other exiled leaders including Abuna Zenamarkos, Abuna Elias and Abuna Gorgoriyos, with the partnership of Abuna Yishak, Archbishop of the Ethiopian Orthodox Churches in North America and Europe, and the leadership of the exiled Patriarch who was living in Kenya at the time, His Eminence ensured the continuation and expansion of the Ethiopian Orthodox Holy Synod despite its displacement from its home. Under the leadership of His Eminence as General Secretary, the Synod sought to console the distraught Christians in Ethiopia while seizing the opportunity to gather the multitude of Ethiopians who had migrated to North America and Europe since the 1970s.
As General Secretary of The Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahdo Church-In-Exile, His Eminence established his secretariat in Berkeley, CA, but traveled far, in the manner of the missionary journeys of the Apostle St. Paul, to Canada, Australia, the Middle East, Asia, Europe and South Africa to organize and nurture the ardent Ethiopian Christians, tirelessly soliciting for funds to build them church buildings.
In addition to his native Amharic, His Eminence speaks Geez (the ancient classical and liturgical language of Ethiopia), Tigrigna, English, Greek, Turkish, and Arabic, which has enabled him to read, interact with visitors and easily communicate whenever he is invited for a visit to places where these languages are spoken.
For his exceptional stewardship over his jurisdiction in California, the tremendous religious and social strides he made in providing spiritual guidance to the faithful Ethiopian immigrants at large and his invaluable services to the Ethiopian Orthodox Church, His Eminence is a recipient of certificates of recognition from United States Congressman Michael M Honda, United States Congresswoman Barbara Lee, 13th congressional district, United States Congresswoman Nancy Pelosi, 12th congressional district, United States senator from California, Kamala Harris, United States senator from California, Dianne Feinstein, Assemblyman Rob Bonta and The California Legislature Assembly. In addition, His Eminence also received certificates of declaration, proclaiming July 19th, his date of birth, Archbishop Melketsedek Workneh day, from Mayor Edwin Lee for City and County of San Francisco, Mayor Libby Schaaf for the City of Oakland, Sam Liccardo for the City of San Jose, Tom Bates for the City of Berkeley and Lisa M Gillmor for the City of Santa Clara.
His Eminence Abune Melketsedek devoted his life to Christ, advocated equal rights for all and tirelessly taught the paramount importance of Christians respecting and loving one another and modeling themselves after the gospel. Concerning the social and political challenges of his country, he preached intensely and tirelessly against religious and racial divide and urged all Ethiopians to live in peace and harmony with the understanding of their lineage to the holy land that is Ethiopia. He supplicated for the brutally murdered, the unjustly imprisoned, the impoverished and the sick, while persistently speaking out against perpetrators of evil.
Although not befitting his outstanding contributions, Mekane Selam Medhanealem Cathedral and Melketsedek foundation designate this museum library Archbishop Abune Melketsedek Library & Museum in commemoration of His Eminence’s legacy. It will serve as a repository of primary source materials on His Eminence, such as his written bodies of work, his personal library of books and memorabilia, among other archives. It is inaugurated with his benediction on this day May 12, 2018.

Saturday, December 29, 2018

የሻሸመኔ አሳዛኙ ክስተትና የደረሱኝ መረጃዎች | ከአህመዲን ጀበል



ዛሬ ጠዋት ላይ በፌስቡክ ወጣቶች አዛዉንቶችን ሲደበድቡ የሚያሳይ ቪዲዮ ተመለከትኩ፡፡ አንዳንዶች አዛዉንቶቹ የእገሌ ብሄር(ዘር) ስለሆኑ ነው የሚደበድቧቸው እያሉ ሲጽፉ ሌሎች ደግሞ የተደብዳቢዎችን ማንነት ትተው ሽማግሌዎች መሆናቸውን ብቻ እየጠቀሱ አዝነው የጻፉትን አነበብኩ፡፡ ልክ ነው ያሳዝናል፡፡ በሀገራችን ባህል ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን በእድሜ ከፍ ያለን ሰው ያውንም ወጣቶች እንኳንስ እያሳደዱ መደብደብ አይደለም አጓጉል ቃላት እንኳ መሰንዘር ነውር ነው፡፡ ከዚህ በፊት በሻሸመኔ በአንድ ኢትዮጵያዊ ወገናችን ላይ የተፈጸመውን አሳዛኝና አስደንጋጭ የደቦ ፍርድና እርምጃ አስታዉሶኝ ጉደዩ አስደነገጠኝ፡፡ ችግር ቢኖር እንኳ ለህግ ማቅረብ እየተቻለ ስለምን የደቦ ፍርድ እዚያም እዚህም ይሰፍናል? ብዩ አዘንኩ፡፡ ቪዲዮውን በጥሞና ሳየው ደብዳቢዎቹም ተደብዳቢዎቹም ኦሮምኛ ቋንቋ እየተናገሩ እንደሆነ አስተዋልኩ፡፡

ከዚም ጉዳዮን አጣርቼ ለማወቅ ጥረት ጀመርኩ፡፡ የተለያዩ ሰዎች ጋር ደዋወልኩ፡፡ እንደተባለው ግጭቱ በሻሸመኔ እንደሆነና ስፍራው በሻሸመኔ ከተማ ቀበሌ 10 አሌሉ የሚባል ሰፈር ባለው የምዕራብ አርሲ ዞን የእስልምና ጉዳይ ጽ/ቤት (መጅሊስ) ቅጥር ጊቢ መሆኑን ተረዳሁ፡፡ የተደበደቡት ሰዎች ጀማል መሀመድ፣ሁሴን አብዱልቃድር፣ ዑስማን፣ሙሀመድ አየለ (አልይ) እና አንድ ስማቸውን ማወቅ ያልቻልኳቸው እንደሆኑ ተረዳሁኝ፡፡ ክስተቱም ከ41 ቀናት በፊት በ6/3/2011 እንደተፈጠረ ሰማሁ፡፡ ጉዳዩም ከመጅሊስ ጋር ተያይዞ እንደተፈጠረና ከአንድ ወር በፊት የተደበዱ ሰዎች ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች አቤቶታ እንዳቀረቡም ሰማሁ፡፡ በሀገሪቷ በአንንዳንድ አከባቢዎች እየታየ ስላለው ግጭት የመፍጠር አዝማሚያ ከአንድ ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለዉጥ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ የፌደራል መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሀጅ ሙሐመድ አሚን ጀማል በሻሸመኔ መጅሊስ ግጭት ተከስቶ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንደቀረበ የጠቀሱት ኋላ ላይ ትዝ አለኝ፡፡ ወደ ፌደራል መጅሊስ ደዉዩ እንዳረጋገጥኩ የሻሸመኔው ችግር ከ41 ቀናት በፊት የተከሰተው ራሱ መሆኑን አረጋገጥኩ፡፡ ወደ ሻሸመኔም ደውዩ ጠያየቅሁ ከመረጃ ምንጮቼ የተረዳሁትን ከጉዳዮ መነሻና የእለቱ ችግር እንዴት እንደተከሰተ ጭምር እንደሚከተለው በዝርዝር አብራራለሁ፡፡
የሻሸመኔ ከተማ ህዝብ በከተማዋ በስልጣን ላይ የነበሩት የመጅሊስ አመመራሮችን አትወክሉንም ብሎ ይቃወም ነበር፡፡ በኋላ ላይ የህዝቡ ጫና ሲበዛባቸው በመጅሊስ መሪነት የነበሩ ሰዎች ከሕዝቡ ከምንጣላ ብለው በ15/10/2011 ከሥልጣን ለቀው የቢሮውን ቁልፍ ለሀገር ሽማግሌዎች አስረከቡ፡፡ ሽማግሌዎችና ዓሊሞች በጉዳዩ ላይ እየመከሩ ሳለ በሰኔ 26 ቀን 2010 የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አሸማጋይነት ተቋቋመ፡፡ የመጅሊሱን ቢሮ ቁልፍ የተረከቡት ሽማግሌዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት ለዉጥ እስኪመጣ እንጠብቅ በሚል የሻሸመኔ ከተማና የምዕራብ አርሲ ዞን መጅሊስ ቢሮ ታሽጎ እንዲቆይ ይወስናሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ከአምስት ወራት በፊት የኦሮሚያ ክልል መጅሊስ ደብዳቤ በመጻፍ እነእገሌን በመጅሊስ መሪነት ሾሜያለሁ ብሎ ደብዳቤ አስይዞ ይልካል፡፡ የተላኩት ሰዎችም በተይም በረብሻው ስፍራ ቆሞ ለህዝቡ የሚናገረው ጀማል መሀመድ የተሾሙበትን ፖስታ ይዞው ለዞኑና የከተማው አስተዳደሮች ፖሊስና የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ጋር ይሄዳል፡፡ ከአከባቢው ያገኘሁት መረጃ እንደሚለው ናደው የሚባለው የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊ ጉዳዩ የህዝበ ሙስሊሙ እንጂ የኛ አይደለም፡፡ ሕዝቡን ጠይቅ እኛን አይመለከትም ይለዋል፡፡
ቀጥሎም በከተማዋ ታዋቂ የሆኑ ዓሊሞችን እነ ሼህ ሀጅ አደም፣ሼህ አሊ ቡታንና ሼህ መሀመድ በዳሶ ያናግራል፡፡ አግዙኝ ይላል፡፡ እነርሱም ‹‹ችግር ልትፈጥር ካለሆነ በቀር አርፈህ ተቀመጥ›› ይሉታል፡፡ የዚህ በዚህን ጊዜ የከተማው አስተዳደር ፖሊስና የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ችግር እንዳይፈጠር አርፈው እንዲቀመጡና ከህዝቡ ጋር እንዳትጋጩ ብለው ይመክሯቸዋል፡፡ የሻሸመኔ ከተማ የእስልምና ጉዳይ ጽ/ቤትን ከፍተው ለመግባት ስፍራው ከተማ መሃል ስለሆነና ቁልፉም በሀገር ሽማግሌዎች እጅ ስለሆነ ችግር ይፈጥርብናል ብለው ይሰጋሉ፡፡ ቀጥሎም የሻሸመኔ ከተማ መጅሊስ ቢሮ ተዘግቶ እያለ አዲሱን የሻሸመኔ መጅሊስን ቢሮ ወደ ምዕራብ አርሲ ዞን መጅሊስ ቢሮ ቅጥር ጊቢ አዙረናል፡፡ እኛም ተመርጠናል ብለው በከተማዋ መስጊዶች ማስታወቂያ ይለጥፋሉ፡፡
የተወሰኑ የሀገር ሽማግሌዎች ከዚህ በፊት በመጅሊስ ምርጫ ጊዜ በሳዑዲ አረቢያ ጅዳ ነበረ የተባለው ጀማል መሁመድን ከዚህ በፊት በማንኛውም መልኩ የመጅሊስ አባል ሳትሆን እንዴት በመጅሊስ መሪነት ተመረጥኩ ትላለህ ብለው ያናግሩታል፡፡ ይኸው የኦሮሚያ መጅሊስ መርጦ ላከኝ ያለበትን ደብዳቤ ብሎ ያሳያቸዋል፡፡ ሽማግሌዎቹ ‹‹እውነት የኦሮሚያ መጅሊስ መርጦህ ቢሆን እንኳ ከህዝቡ ሁሉ ጋር ተጋፍጠህ አትችልም፤ ደብዳቤን ደብቀህ ኑሮህ ኑር›› ይሉታል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ እርሱም አሻፈረኝ ብሎ በመጅሊስ መሪነት ተሾመ የተባለው ጀማል መሀመድም በ02/3/2010 ደብዳቤ በመጻፍ (በኦሮምኛ የተጻፈው ይህ ደብዳቤ በእጄ ገብቷል) የሻሸመኔ ከሕዝበ ሙስሊም ስብሰባ ይጠራል፡፡ በዚህን ጊዜ የከተማው ሽማግሌዎችና ዓሊሞች በስብሰባው ቢገኙ ላልመረጧቸው የመጅሊስ መሪዎች እርቅና መስጠት ይሆናል ብለው ቀሩ፡፡ ሰዉም እንዲቀር ሲሉ በየመስጊዱ ለሕዝቡ አስተላለፉ፡፡ በዚህ ጊዜ የተወሰኑ ወጣቶች በስፍራው ተገኝተው ‹‹ማንናችሁ? በምን ስልጣን ጠራችሁን?›› ብለው እየጠየቁ ግርግሩና ድብደባው ተከሰተ፡፡ ይህንኑ የሚያሳየዉን ቀጣዩን ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡ ኦሮምኛ ለማትሰሙት ደግሞ በዚህ ቪዲዮ ላይ የሚተላለፈውን ንግግር እንደሚከተለው ተርጉሜ አቅርቤያለሁ፡፡
– ተናጋሪ (በበረንዳው መድረክ ላይ የቆመው)፡- …መምጣት ስላልቻሉ…(ብሎ ቪዲዮው ይጀምራል)
– ከሰዉ መካከል፡- ማነው የጠራን?
– ተናጋሪ፡- እኔ ነኝ፡፡
– ከሰዉ መካከል፡- ለምን ጠራኸን? አንተ ማንነተህ?
– ተናጋሪ፡- እኔ ጀማል መሀመድ ጃርሶ እባላለሁ፤
– ከሰዉ መካከል፡- የሥራህ ድርሻ ምንድነው? ሚናህ ምንድነው? ለምን ጠራኸን?
– ከከመድረክ ተናጋው ጎን የቆሙት ሽማግሌ(በመጅሊስ መሪነት ተሸሙ የተባሉትና ኃላ ላይ ከተደበደቡት መካከል አንዱ ናቸው) ፡- ችግር የለውም ተራ በተራ ተናገሩ፡፡
– ከዉ መካከል፡- አንተ አያገባህም እንደፈለግነው እንጠይቃለን፡፡ ንግግራችን ከርሱ ጋር ነው፤ካንተ ጋር አልተነጋገርንም፡፡
– እንደፈለግነው እንጠይቃለን አያገባህም፡፡
– ከሰዉ መካከል፡- አንተ ሽማግሌ እርሱ እኔ ነኝ የጠረኻችሁ ብሏል አንተ ምንም አያገባህም ዝም በል፡፡
– ከመድረክ፡- ጌታችሁን ፍሩ
– ከሰዉ መካከል፤-አንተ ራስህ ጌታህን ፍራና ዉረድልን፡፡
– ከሰዉ መካከል፡- አንድ ሰው ሲጠይቅ ሌሎቻችሁ ዝም በሉ፡፡
– ከሰዉ መካከል፡- ዝም በል አፍህን አትክፈት፡፡
– ከሰዉ መካል፡- ምን ልትሆን ፈለግክ?
– ከሰዉ መካከል፡- አንተ ሕዝቡን የጠራህበትን ተናገር፡፡ ማን እውቅና እንደሰጠህ ተናገር፤ በህገወጥ መንገድ እዚህ ጊቢ ማን እንድትገባ እንደፈቀደልህ ተናገር፡፡ ይህ ጊቢ የሙስሊሙ ሕዝብ ነው፡፡ ከሌቦች እጅ ወስደን ቆልፈናል፡፡ ማን እንድትከፍት እንዳደረገህ ተናገር-ንገረን፡፡
– በዚህ ጊዜ በበረንዳው መድረክ ከጀርባ የቆመው ወጣት በመድረክ ላይ የቆመውን ተናጋሪ ከጀርባ ገፍቶ አስወረደው
– ከሰዉ መካከል፡ ተዉ ተዉ
– ምን ልትሆን ነው?
– ግርግሩና ድብደባ ተጀመረ፡፡
በዚህ መለኩ ግጭቱ ተፈጠረ፡፡ የቆሰሉ ሰዎችም ነበሩ፡፡ ጉዳዩን የሀገር ሽማግሌ የሆኑት ሼህ ተማም፣ሼህ አሊ ቡታ፣ ዉሽታና ዳንሱሬ በመያዝ በእርቅ እየፈቱት ነው፡፡ የተጎዱ ሰዎች ለመታከሚያ 200 ሺህ ብር ያስፈልገናል ሲሉ የሀገር ሽማግሌዎቹ 10ሺህ ብር እንዲሰጥ ወስነዋል፡፡ ለአሁን የደርስኩበት መረጃ ይህን ይመስላል፡፡ እዚህ ላይ በግልጽ መጥቀስ የምፈልገው በአሁኑ ሰዓት ልክ በብሄርና ጎሳ ግጭት እየተፈጠረ እንዳለው በሃይማኖትም ግጭት ለመፍጠር አንዳንድ ሙከራዎች እንዳሉ እንደኮሚቴ በግልጽ ከመንግስት ጋር ተወያይተናል፡፡ መልኩን እየቀያየረ ቢመጣም ግጭት በተለይ በዚህ የሽግግር ወቅት ለማን እንደሚጠቅም ግልጽ ነው፡፡ ይህንን በመረዳት ኮሚቴው ከእስካሁኑ በተለየ መልኩና በፍጥነት መጓዝ እንደሚገባ ከሚመለከተው አካል ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ በተከታታይ ኮሚቴው ይፋ የሚያደርጋቸው ጉዳዮች አሉ፡፡ ይህን በመረዳት እያንዳንዱ ዜጋ ምንም ያክል ስሜት የሚነካ ነገር ቢከሰት የመፍትሄው እንጂ የችግሩ አካል እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባል፡፡
የሻሸመኔው ጉዳይ ላይም ምክንያት የሆኑ ሁሉ ከየትኛውም ወገን ይሁኑ ተለይተው ለህግ ማቅረብ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም እንደ ሙስሊምነታችን የሻሸመኔው ችግር በሙስሊሞች መካከል ያውንም አንድ ቋንቋ ተናጋሪ በሆኑ ወጣቶች በአባቶች ላይ መከሰቱ አሳፋሪና ብዙ የሚያስተምረን ሊሆን ግድ ይላል፡፡ የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖር የሰውነት ክብር፣ የኢትዮጵያዊነት ባህልና የጋራ ማንነት ሉጋም ሆኖ ካልያዘን ከባድ ጊዜ ከፊታችን እንዳለ ያሳየናል፡፡ ይህ ደግሞ የሚያሰጋን በመሆኑ ስሜት ዉስጥ ገብተን ችግሩን ከማራገብ ቆም ብለን ዘላቂና ሀገር ዐቀፍ መፍትሄ እንድንሻ ሊገፋፋን ይገባል፡፡

ኢትዮጵያና ሱዳን በሶስት ሳምንት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተገናኙ



የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በተቃውሞ እየታመሰች ባለችው ሱዳን ዛሬ ቆይታ አድርገዋል፡፡ በካርቱም ቆይታቸውም ከሱዳኑ የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚነስትር ዶ/ር አል ድሪር ሞሃመድ ጋር መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ገልጿል።
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በውይይቱ ወቅት ሱዳን በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ውስጥ ቅድሚያ የሚሰጣት አገር ናት መሆኗን ጠቁመው ሁለቱ አገሮች ለሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች ፍላጎት መሳካት ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩና የሁለቱ አገሮች ህዝቦች መፃኢ ዕድልም ተመሳሳይ መሆኑን ገልፀዋል።
ጨምረውም ‹‹በሁለቱ አገሮች መካከል በከፍተኛ ደረጃ የተደረጉ የፖለቲካ ምክክሮች ሁለቱ ወገኖች ከፊት ለፊታቸው ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና ለህዝባቸው ጥቅሞች በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ማሳያ ነው›› ብለዋል። የሱዳን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ዶ/ር አል ድሪር ሙሀመድ በበኩላቸው ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሚመራው አዲስ አመራር ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ በኢትዮጵያ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ለውጥ ሱዳን ታደንቃለች›› ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በግንቦት ወር 2010 ዓ.ም በሱዳን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ፕሬዝዳንት ኦማር ሃሰን አልበሽር በቅርቡ በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
እንዲሁም ባለፈው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በሱዳን ጉብኝት ማድረጋቸው የሁለቱን አገሮች ወንድማማች ህዝቦች ፍላጎት ለማሳካት በጋራና በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡
ሕወሓት ሱዳንን በሰላማዊ ሰልፍ ጭምር አጋሩ መሆኗን ከገለጸ በኋላ በሁለት ሳምንት ውስጥ የኢትዮጵያ ባለስልጣን ሱዳንን ሲጎበኝ ይህ ሁለተኛው መሆኑ ነው:: አልበሽር አዲስ አበባ መጥተዋል”” ከሳምንት በፊት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ለሁለት ቀናት ሱዳን ሄደው የነበru ሲሆን ዛሬ ደግሞ ዶ/ር ወርቅነህ እዛ ናቸው:::
ኢትዮጵያና ሱዳን በሶስት ሳምንት ውስጥ ሶስት ጊዜ ተገናኝተዋል ማለት ነው::

Thursday, December 27, 2018

በኢትዮጵያ ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ ታወጀ



የሀይማኖት አባቶች በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አማኞች በሙሉ እንደየእምነታቸው ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ እንዲያደርጉ አወጁ፡፡ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ አባቶች እና የኢትዮጵያ የሀገር ሽማግሌዎች አሁን በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው እለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤው ሁሉም ወገን ቅድሚያ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰብአዊ ክብርና ሰላም በመትጋት የወገኖቻችን ሞት፣ መፈናቀልና ጉዳት በአፋጣኝ ማቆም ይገባዋል ሲል የተማጽዕኖ ጥሪም አቅርቧል፡፡ ከዚህ በኋላ በሀገሪቱ በየትኛውም አካባቢ ምንም አይነት ግጭት እና የሚተኮስ ጥይት ሊኖር እንደማይገባ አሳሰበው ጉባኤው ለመላው ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ባለአስር ነጥብ የሰላም መልዕክት እና የተማጽዕኖ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ግጭቱ ተወግዶ የታሰበው ሰላም እውን እንዲሆንም በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አማኞች በሙሉ እንደየ ዕምነታቸው ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም ጸሎትና ምሕላ ታውጇል ብሏል ጉባኤው፡፡

Wednesday, December 26, 2018

በኢትዮጵያ የታገቱትን 4 ህንዳዊያን ለማስለቀቅ 12.4 ሚሊዮን ብር ተጠየቀ



ከታገቱ በርካታ ቀናትን ያስቆጠሩት አራት ህንዳዊያን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ የተደረገው ድርድር ያለውጤት ተበተነ፡፡ ድርድሩ የተደረገው ባለፈው አርብ ሲሆን በዚህ ድርድር ወቅት የህንድ ኤምባሲና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ተወካዮች ቢገኙም ምንም መስማማት ሊደረስ አልቻለም፡፡ ህናዳዊያኑ ሊታገቱ የቻሉት የሚሰሩበት የህንዱ የኮንስትራክሽን ድርጅት ለሰራተኞቹ ደመወዝ ሳይከፍል ወራትን በማስቆጠሩ ነበር፡፡

የህንዱ ቢዝነስ ላይን ጋዜጣ እንደዘገበው እነዚህን ህንዶች ለመልቀቅ የድርጅቱ ሰራተኞች 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር ጠይቀዋል፡፡ ከታገቱት ውስጥ አንዱ የሆነው ቻይታነያ ሀሪ ሲናገር ‹‹የህንድ ኤምባሲ በህይወት እንደምንቆይ ብቻ ማረጋገጫ ሰጥቶናል፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንም  እንደማንገደል ነግሮናል›› ብሏል፡፡ እነዚህ ሁለት አካላት የታገቱበትን ካምፕ ደህንነት ከማረጋገጥ ውጭ እነሱን ለማስለቀቅ የሚያስችል ምንም አቅም እንደሌላቸውም አስረድቷል፡፡

ጉዳዩ ከአቅም በላይ በመሆኑም የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጣልቃ እንዲገባም ታጋቹ ጠይቋል፡፡ የተጠቀሰው ገንዘብ እስካልተከፈለ ድረስ የመለቀቃቸው ነገር የማይታሰብ እንደሆነም ለዜና ምንጩ ተናግሯል፡፡ የህንዱ አይኤል ኤንድ ኤፍ ኤስ ኩባንያ የመንገድ ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረ ሲሆን ደመወዝ ያልከፈለው በመክሰሩ እንደሆነ ከዚህ ቀደም ዘግበን ነበር፡፡

Saturday, December 22, 2018

የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ጸደቀ


 በኢትዮጵያ ከወሰንና ከማንነት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚል የተዘጋጀው ረቂቃአዋጅ ዛሬ በፓርላማ ጸደቀ።
          በ33 ተቃውሞ የጸደቀው ይህ አዋጅ እንዳይጸድቅ 10 የሕወሃት የፓርላማ አባላት በፊርማ አስቀድመው ጥያቄ አቅርበዋል።
          ጥያቄያቸውም አዋጁ ሕገ መንግስቱን ይጻረራል የሚል ሲሆን የሕግ ባለሙያዎች እንደሚሉት ኮሚሽኑ የማማከር እንጂ የመወሰን ስልጣን ስለሌለው ሕገ መንግስት አይጻረርም በማለት ሞግተዋል።
          “የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ” በሚል ዛሬ ለፓርላማው የቀረበው አዋጅ ኮሚሽኑ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥናቱንና ምክረ ሃሳቡን እንደሚያቀርብ ያስረዳል።
          ኮሚሽኑ ከማንነት ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጥያቄዎችን የክልል፣የዞንና የወረዳ የአስተዳደር ጥያቄዎችን ሳይንሳዊ በሆነ ጥናት የሚመለከታቸውን ሁሉ በማሳተፍ ሞክረ ሃሳብ እንዲያቀርብ ስልጣን ተሰጥቶታል።
          ይህ ኮሚሽን የስልጣን ዘመኑ 3 አመት ሲሆን ዋናው ኮሚሽነርና ምክትሉ በፓርላማ እንደሚሰየምም ተደንግጓል።

Thursday, December 20, 2018

ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ከ33 አመታት በኋላ ኢትዮጵያ ገቡ


 የእርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ከ33 አመታት በኋላ ኢትዮጵያ ገቡ።
          የደርግንመንግስት በመቃወም ስርአቱን ከከዱ ከፍተኛ ባለስልጣናት የመጀምሪያው የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በ1981 በኮለኔል መንግስቱሃይለማርያም ላይ የተካሄደው የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ላይ ከውጭ ሆነው ተሳታፊ እንደነበሩም መረዳት ተችሏል።
          ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ትላንት ከናሚቢያ ዊንዲሆክ አዲስ አበባ ሲደርሱ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው እንደተቀበሏቸው ከመረጃው ለማወቅ ተችሏል።
          በአቀባበል ስነስርአቱ ላይ የቀድሞ መንግስት ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ኮለኔል ፍስሃ ደስታም መገኘታቸው ታውቋል።
          በአሜሪካ ኒዮርክ ከሚገኘው ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ 2ኛ ዲግሪያቸውን አግኝተው ወደ ኢትዮጵያ እንደተመለሱ በደርግ መንግስት ውስጥ በተለያዩ የሃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በ1979 ስርአቱን ጥለው በመውጣት፣በፕሪንስተን ዩኒቨርስቲ ውስጥ ሆነው የደም እንባ የተባለ መጽሃፍ በመጻፍ የስርአቱ ጉድፍ ያሉትን አጋልጠዋል።
          በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ በቋሚ ተጠሪነት የኤርትራ ክፍለ ሃገር አስተዳዳሪነትና በእርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ኮሚሽነርነት በደርግ ስርአት ውስጥ ማገልገላቸው ታውቋል።
          ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በ1981 የኮለኔል መንግስቱን መንግስት ለመገልበጥ በተደረገው ሙከራ ከውጭ ሆነው ተሳታፊ እንደነበሩም መረዳት ተችሏል።
          የኢትዮጵያ ወታደሮች ነጻ ንቅናቄን በመመስረት በግልበጣው ሒደት ተሳታፊ የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ መንግስት ከተገለበጠ በኋላ በሚደረገው ሒደት ውስጥ ሻዕቢያና ሕወሃት ተሳታፊ በሚሆኑበት መንገድ ላይ ከአቶ ኢሳያስ አፈወርቄና ከሕወሃት መሪዎች ጋር በወቅቱ መነጋገራቸውንም ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቆይታ መናገራቸው ይታወሳል።
          ለረጅም አመታት በተባበሩት መንግስታት ውስጥ በተለያየ የሃላፊነት ቦታ ያገለገሉት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ የሰላምና የጸጥታ ምርምር ተቋም የሚል ድርጅት ከሌሎች ባለሙያዎች ጋር በመመስረት በዋና ስራ አስፈጻሚነት እየመሩት እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።
          መቀመጫቸውን በአሁኑ ወቅት በናሚቢያ ዊንድሆክ ያደረጉት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ከ33 አመታት በኋላ ትላንት ማምሻውን ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል።
          ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ትላንት ከናሚቢያ ዊንዲሆክ አዲስ አበባ ሲደርሱ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ተቀብለዋቸዋል።
          በአቀባበል ስነስርአቱ ላይ የቀድሞ መንግስት ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ኮለኔል ፍስሃ ደስታም መገኘታቸው ታውቋል።

በሱዳን የገዢው ፖርቲ ጽሕፈት ቤት ተቃጠለ


ኢሳት
 ሱዳን ውስጥ ለተቃውሞ አደባባይየወጡ ወጣቶች የገዢውን ፖርቲ ጽሕፈት ቤት አቃጠሉ።
የተቃውሞው መነሻ በነዳጅ እና በዳቦ ዋጋ ላይ የተደረገው ጭማሪ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ተቃውሞው የተነሳውና የተቀጣጠለው ከርዕሰ መዲናዋ ካርቱም 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አትባራ በተባለው ከተማ ሲሆን በተቃውሞው የሱዳኑ ገዢ ፓርቲ ናሽናል ኮንግረስ ጽሕፈት ቤት ከመቃጠሉ ባሻገር በጎዳናዎችም ላይ እሳት እያነደደ መገኘቱን አልጀዚራ ዘግቧል።
አንድ የሱዳን ፓውንድ ይሸጥ የነበረው ዳቦ ወደ 3 ፖውንድ ከፍ ማለቱና በተመሳሳይ የነዳጅ ዋጋ እየጨመረ መገኘቱ ለተቃውሞው መነሻ እንደሆነም ተመልክቷል።
ተቃውሞው ከአትባራ ወደ ሬድ ሲት ስቴት መሸጋገሩ የተገለጸ ሲሆን ተቃውሞው የአልባሽር መንግስት ከስልጣን ይውረድ ወደሚል ተሸጋግሯል።
ተቃውሞው በተጠናከረበት አትባራ ከተማና በአጠቃላይ በናይል ሪቨር ስቴት የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን የሰዓት ዕላፊም ተደንግጓል።
ከሰዓት 12 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ እንደማይቻልም ተደንግጓል።
የ74 ዓመቱ ፕሬዝዳንት ጄኔራል ኦማር አልበሽር በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙ የፊታችን ሰኔ 30 ዓመት ይሆናቸዋል።

ከፊል አውቶማቲክ የሆኑ የጦር መሳሪያዎችን ግለሰቦችና የግል ኩባንያዎች እንዳይጠቅሙ ህግ ወጣ


ከፊል አውቶማቲክ የሆኑ የጦር መሳሪያዎችን ግለሰቦችና የግል ኩባንያዎች እንዳይጠቅሙ የሚከለክል መመሪያ የአሜሪካ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አወጣ።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከመጋቢት23/2018 ጀምሮ መሳሪያዎቹን መጠቀም የተከለከለ በመሆኑ ግለሰቦችም ሆኑ አምራቾች እንዲያወድሙ አሊያም ለሚመለከተው አካል እንዲያስረክቡትላንት መመሪያ ወጥቷል።
ከአውቶማቲክ መሳሪያዎች ውጭ ከፊል አውቶማቲክና አውቶማቲክ ያልሆኑ መሳሪያዎችን ገዝቶ መታጠቅ በማይፈቀድባት አሜሪካ የአሰቃቂ ግድያዎች እየጨመሩ መምጣት ብርቱ ተቃውሞን ሲያስከትል ቆይቷል።
በተለይም ከአንድ ዓመት በፊት የአሜሪካ የቁማርና የመዝናኛ ማዕከል በሆነችው ላስቬጋስ ከተማ በአንድ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የነበሩ 57 ሰዎች መገደል በጦር መሳሪያ መጠቀም መብት ዙሪያ ከፍተኛ ውይይት ቀስቅሷል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በጥቅምት ወር 2017 ስቴፈን ፓዶክ የተባለ የ64 ዓመት ሰው ላስቬጋስ ከተማ ከሚገኘው ማንዳሊ ቤይ ሆቴል 32ኛ ፎቅ ላይ ከያዘው መኝታው ክፍል ቁልቁል 22ሺህ ሰው በታደመበት የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ በከፈተው ተኩስ 58 ሰዎች ሲገደሉ 489 የሚሆኑት ቆስለዋል።
ፖሊስ ከመድረሱ በፊትም ግለሰቡ ራሱን ያጠፋ ሲሆን በመኝታ ክፍሉ ውስጥም 23 የጦር መሳሪያዎች መገኘታቸው ይታወሳል።
ይህንና መሰል ግድያዎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአሜሪካ ጠቅላይ አቃቤ ህግ መመሪያውን ትናንት እንደወጣ መረዳት ተችሏል።
ተጠባባቂ ጠቅላይ አቃቤ ህጉ- ማቲው ዋይታከር መመሪያውን የፈረሙ ሲሆን እንደ አውሮፓውያኑ ከመጋቢት 23/2018 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
ቀደም ሲልም አውቶማቲክም ሆነ ማሽንጋን መሳሪያዎችን ግለሰቦች እንዳይጠቀሙ ህግ ይከለክላል።
በአዲሱ መመሪያ ከፊል አውቶማቲክ መሳሪያዎችም በዕገዳው ዝርዝር ውስጥ ገብተዋል።
ሆኖም ሽጉጥና አውቶማቲክ ያልሆኑ መሳሪያዎችን ገዝቶ መጠቀም አልተከለከለም።
አዲሱን ዕገዳ ለማስቀልበስ እንቅስቃሴ እንደሚኖር ከወዲሁ የተገመተ ሲሆን የመመሪያው አውጪዎች መመሪያው የሃገሪቱን ህግ መሰረት ያደረገ ስለሆነ እንሞግታለን ብለዋል።
ክልከላው በመላው አሜሪና ተፈጻሚ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሶስት ሰዎች ተገደሉ


(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 11/2011) በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ብር ጭኖ በሚጓዙ  የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተሽከርካሪዎች  ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጨምሮ ሶስት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ።
ባልታወቁ ታጣቂዎች በተፈጸመውጥቃት አንደኛው ተሽከርካሪ ሙሉ በሙሉ መውደሙን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ተሽከርካሪዎቹ 6 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ይዘው ሻኪሶ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ለማድረስ እያመሩ እንደነበረ ታውቋል።
ሻኪሶ ከተማ ለመድረስ 20 ኪሎሜትር ሲቀራቸው ጥቃቱ መፈጸሙ የተገለጸ ሲሆን ብሩን የጫነው አንደኛው ተሽከርካሪ አምልጦ ሻኪሶ በመግባት ገንዘቡን ማስረከቡን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲላ ቅርንጫፍ የኦፕሬሽን ክፍል ሃላፊ አቶ አብዱልፈታህ አብራር ለኢሳት እንደገለጹት ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት ነው።
ከዲላ ቅርንጫፍ ብር ጭነው ወደ ጉጂ ዞን ሃያዲማ ቅርንጫፍ ያመሩት የባንኩ ሰራተኞች በማግስቱ ከሃያዲማ ወደ ሻኪሶ የሚያደርሱት ገንዘብ እንደነበር ነው ሃላፊው የሚገልጹት።
6 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ጭነው በ10 ወታደሮች ታጅበው ከሃያዲማ ወደ ሻኪሶ እያመሩ በነበሩት የባንኩ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃቱ የተፈጸመው ሻኪሶ ለመድረስ 20 ኪሎ ሜትር ሲቀራቸው እንደነበርም ሃላፊው ገልጸዋል።
ማንነታቸው ያልታወቁ ባሏቸው ታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ከወታደሮቹ ሁለቱ ሲገደሉ የሁለተኛው ተሽከርካሪ ሹፌሩም ህይወቱ ማለፉ ታውቋል።
ታጣቂዎቹ ከሃያዲማ ቅርንጫፍ ወደሻኪሶ ገንዘብ ጭኖ የሚሄደውን ተሽከርካሪ በጥይት መትተው ጎማውን ቢያተነፍሱትም ሹፌሩ በወሰደው ቆራጥ ርምጃ ጎማ የሌለው መኪና እያሽከረከረ ሻኪሶ መግባቱንና ገንዘቡን ከዘረፋ ማስመለጡንም የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
ይህን ተግባር የፈጸመው ሹፌር በተተኮሰበት ጥይት የተመታ ሲሆን ገንዘቡን ካስረከበ በኋላ ወደ ሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ለህክምና መግባቱንም ለማወቅ ተችሏል።
የታጣቂዎቹን ማንነት በተመለከተ ኢሳት ባደረገው ማጣራት በኦነግ ስም የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች የሚያሳዩ መረጃዎች ደረሰውታል።
ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ የሻኪሶ ንግድ ባንክ ሰራተኛ የኦነግ እንቅስቃሴ ጎልቶ የሚታይበት አካባቢ በመሆኑ በባንኩ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት የሰነዘሩትም የኦነግ ታጣቂች ናቸው ሲል ለኢሳት ገልጿል።
ጉዳዩን በተመለከተ የኦነግ አመራሮች ምላሽ እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
ከሁለት ወራት በፊት በተመሳሳይ የኦነግ ታጣቂዎች ጉጂና አማሮ በሚዋሰኑበት አከባቢ ሶስት የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የገደሉበትን ጥቃት መፈጸማቸው የሚታወስ ነው።

wanted officials