Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, March 4, 2020

የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች (Corona virus) / Possible Symptoms

ዋና ምልክቶች (Major Indicators)
※ ትኩሳት (Fever)
※ ሳል (Cough)
የምግብ መፈጨት ችግር (Digestive Problem)
※ ማስመለስ (Vomiting)
※ ተቅማጥ (Diarrhea)
※ የምግብ ፍላጎት መቀነስ (Loss of Apetite)
የነርቭ ምልክት (Nerve Symptoms)
※ የራስ ህመም (Head Ache)
የእይታ ችግር (Vision Problems)
※ የአይን ማቃጠል ወይም መለብለብ ናቸው።
.Image result for coronavirus
የቫይረሱ መተላለፊያ መንገዶች፦
በቻይና የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ (Coronavirus) ወረርሽኝ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ወደ ጤነኛ ሰው በሚከተሉት መንገዶች ይተላለፋል፦
※ በበሽታው የተያዘ ሰው በሚያስልበት ወይም በሚያስነጥስበት ወቅት በአየር ይተላለፋል።
※ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ከተነካካን ወይም እጅ ለእጅ ከተጨባበጥን (ሰላምታ)።
※ ቫይረሱ ያለበትን ዕቃ ወይም ቁስ ከነካን በኋላ አፋችንን፣ አፍንጫችንን ወይም አይናችንን ከነካን በቫይረሱ በቀላሉ እንያዛለን።
ቫይረሱን ለመከላከል ምን ማድረግ አለብን?
ለኮሮና ቫይተስ የሚሆን ክትባት እስካሁን አልተሰራም፤ ለኮሮና ቫይረስ ኢንፌክሽንን ለመከላከል የሚረዳን ልክ ጉንፋን እንዳይዝዎት የሚያደርጉትን አይነት ጥንቃቄ ያድርጉ፦
※ እጅዎን ለብ ባለ ውሃ እና ሳሙና ይታጠቡ ወይም ከአልኮል የተሰሩ የእጅ ሳኒታይዘሮች (Hand Sanitizer) ይጠቀሙ።
※ ህዝብ በተጨናነቀባቸው ቦታዎች ላለመሄድ ይሞክሩ
※ በሽታው ቢኖርብዎትም ባይኖርብዎትም አፍና አፍንጫዎን የሚከልል ማስክ ያድርጉ
※ አፍዎን፣ አፍንጫዎንና አይንዎን በፍጽም በእጅዎ ወይም በጣትዎ አይንኩ።
※ በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ያለዎትን ቅርርብ (ንክኪ) ይቀንሱ።
አጠቃላይ መረጃ

አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር = 4,474
★ Total Confirmed Cases = 4,474
★ አጠቃላይ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች = 724★ Total Deaths = 107
★ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር = 63
★ Total Recovered = 63
.
በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ስርጭት በሃገር (Confirmed Cases by Country/Region)
※ ቻይና (Mainland China) = 4,409
※ ሆንግ ኮንግ (Hong Kong) = 8
※ ታይላንድ (Thailand) = 8
※ ማኩዋ (Macua) = 6
※ ማሊዢያ (Malaysia) = 4
※ አውስትራሊያ (Australia) = 5
※ ሲንጋፖር (Singapore) = 5
※ ታይዋን (Taiwan) = 5
※ ጃፓን (Japan) = 4
※ አሜሪካ (US) = 5
※ ፈረንሳይ (France) = 3
※ ደቡብ ኮሪያ (South Korea) = 4
※ ቬትናም (Vetnam) = 2
※ ካምቦዲያ (Cambodia) = 1
※ ካናዳ (Canada) = 1
※ ኔፓል (Nepal) = 1
※ ጀርመን (Germany) = 1
※ ኮትዲቫር (Ivory Coast) = 1
መልካም ጤንነት!! ለወዳጅ ዘመድ ሼር ማድረግ አይርሱ/

ቀነኒሳ የሞ ፋራህን የግማሽ ማራቶን ክብረ-ወሰን ሰበረ


በለንደን ከተማ በተካሄደው የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን፤ ቀነኒሳ በቀለ ክብረ-ወሰን በመስበር አሸንፏል።
የ5 ሺህ እና 10 ሺህ ሜትር ውድድሮች የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቱ ቀነኒሳ በዚህ ውድድር ሲሳተፍ የመጀመሪያው ነው።
1:00:22 በሆነ ሰዓት የገባው ቀነኒሳ፤ በእንግሊዛዊው ሯጭ ሞ ፋራህ የተያዘውን የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ክብረ-ወሰን ሰብሯል።
ከቀነኒሳ ጋር ይፋጠጣል ተብሎ የተጠበቀው ሞ ፋራህ ከጥቂት ቀናት በፊት በህመም ምክንያት እንዳይማሰተፍ አሳውቆ ነበር።
x
© The Vitality Big Half
የቢቢሲ አማርኛ

Thursday, February 13, 2020

Brandy and alchohols flew in india tap water


Alcohol has polluted the water supply for several residents in Kerala, India.
 Alcohol has polluted the water supply for several residents in Kerala, India. File/Getty Images
Drinks are on the house and there’s plenty of booze on tap in Chalakudy, a town in the Indian state of Kerala where alcohol has tainted the water supply for several homes.
Eighteen families reported “spiritual,” boozy-smelling tap water to local authorities on Monday, Manorama News reports. All of their homes were drawing water from the same neighbourhood well.
Apartment complex owner Joshy Maliyekkal says he noticed the alcohol smell when he switched on a motor to fill a water tank outside his home.
“All of a sudden, the pipe started to smell very bad,” he told the New Indian Express. “We were suspicious as to why such a smell was coming from the water drawn from an open well.”
He said locals have been using the well for years and have never had a problem.
Authorities looked into the matter and discovered that the well had been tainted by a dumping pit filled with 6,000 litres of illegal alcohol, which had been seized from a bar approximately six years ago. The seized spirits had apparently leaked into the water supply, the New Indian Express reports.
“The inspection proved the presence of alcohol in the water, and hence we called the excise officials and informed them of the matter,” V.G. Joji, a local ward councillor, told the New Indian Express.
“We will lend all support to the families affected,” said T.K. Sanu, deputy excise commissioner.
Sanu says it’s not unusual to dispose of alcohol in a pit, but those who dug this one should have taken more care to protect the environment and the public. It’s believed they uncorked 2,000 bottles and poured each one into the hole.
“They were unaware of the presence of an open well nearby, which is why this happened,” he said.
What is World Toilet Day?
 What is World Toilet Day?
Residents have filed a complaint with the municipal secretary and health department, Manorama News reports.
The bar linked to the booze has offered to supply water for the affected residents while the issue is sorted out.
STORY CONTINUES BELOW ADVERTISEMENT
In the meantime, the case has triggered plenty of laughter on social media.
“Stuff of dreams,” one user tweeted.
“I suppose this would be the adult version of Willy Wonka’s chocolate factory,” said another person.
A third person said: “‘God’s Own Country’ is where the spirit flows from the tap!”

ህንድ፡ አልኮል በቧንቸው የመጣላቸው ነዋሪዎች በድንጋጤ ላይ ናቸው Alchohol via water pipeline

በመጠጥ የተሞላው ቧንቧ

Image copyrightJOSHY MALIYEKKAL
በህንዷ ግዛት ኬራላ ሰሞኑን አንድ አስደናቂ ጉዳይ ተከስቷል።
በአንድ የጋራ መኖሪያ ህንፃ የሚኖሩ ነዋሪዎች የቤታቸውን ቧንቧ በሚከፍቱበት ወቅት ቢራ፣ ብራንዲና ሌሎች መጠጦች ጋር የተቀላቀለ የአልኮል መጠጥ መፍሰስ ጀመረ።
የሚሰነፍጥ ሽታ ያለው ቅልቅሉ ቡናማ ቀለም ያለው ሲሆን በህንፃው ማዕድ ቤቶች ባለው ቧንቧ በኩልም ነው የመጣው ተብሏል።
በዚህ ሁኔታ የተደናገጡት ነዋሪዎች የአካባቢውን ባለስልጣናት ስለ ሁኔታው ያሳወቁ ሲሆን፤ ውሃቸውም በድንገት ከአልኮል ጋር መቀላቀሉን ተረድተዋል።
እንዴት ሊቀላቀል ቻለ? ነገሩ እንዲህ ነው
ስድስት ሺ ሊትር የሚሆን ህገ ወጥ የአልኮል መጠጥ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ በጋራ መኖሪያ ቤቱ አካባቢ በሚገኝ ጉድጓድ ተቀምጦ ነበር።
በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋለው መጠጥ በመሬትም ስር ፈሶ ለትሪሱር ግዛት የመጠጥ ውሃ የሚያቀርበው የውሃ ጉድጓድ ላይ መቀላቀሉ ታውቋል።
በዚህም የውሃ መጠጥ ጉድጓድም አስራ ስምንት የጋራ መኖሪያ ቤቶችም ይጠቀሙበታል ተብሏል።
"በጣም ነው የደነገጥነው" በማለት ጆሺ ማልይካል የተባለ ነዋሪ ለቢቢሲ ሂንዲ ተናግሯል።

እንደ እድል ሆኖ በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰነፍጠው የአልኮል መጠጥ ከመጠጣት ቢያግዳቸውም፤ ለመጠጥም ሆነ ለመታጠቢያ የሚሆን ውሃ ተቸግረዋል።
"በውሃ ችግር ምክንያት ልጆች ትምህርት ቤት መሄድ አልቻሉም፤ ከስራም ቀርተናል" ብሏል ጆሺ ማልይካል
በውሃ ፋንታ በአልኮል መጠጦች የተሞላው ቧንቧImage copyrightJOSHY MALIYEKKAL
ነዋሪዎቹ ሁኔታውን ካስረዱ በኋላ ባለስልጣናቱ ስህተታቸውን ለማስተካከል ሞክረዋል።
ነገር ግን የውሃ ጉድጓዱን በደንብ ለማፅዳት አንድ ወር እንደሚወስድ ነዋሪዎቹም ገልፀዋል፤ ይህም ሁኔታ ነዋሪውን ባለስልጣናቱ እየቀዱ በሚያመጡት ውሃ እንዲወሰኑ አስገድዷቸዋል።
"በየቀኑ አምስት ሺ ሊትር የሚሆን ውሃ እየቀዱ ቢያመጡም በህንፃዎቹ ለሚኖሩ ቤተሰቦች በሙሉ በቂ ሆኖ አላገኘነውም" ብለዋል ጆሺ ማልይካል
የአካባቢው ባለስልጣናት ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምንም አይነት ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
የኬራላ ግዛት በአገሪቱ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ አልኮልን በሚወስዱ ነዋሪዎቿ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

Tuesday, January 28, 2020

የታገቱት ተማሪዎች፡ የቤተሰብ ሰቀቀን፤ የማሕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጩኸት፤ የመንግሥት ዝምታ


የተጋች ቤተሰብ
ከሚማሩበት የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለደህንነታቸው በመስጋት ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ሳለ ማንነታቸው ባልታወቀ ወጣቶች የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ አሁንም ምላሽ አላገኘም።
ተማሪዎቹ ከታገቱ 50 ቀናት አልፏቸዋል። ወላጆች ልጆቻቸው መታገታቸውን ከሰሙ አንስቶ ለሚመለከታቸው አካላት ልጆቻቸውን እንዲመለሱላቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ መንግሥት በጉዳዩ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ አልሰጠም።
የተማሪዎችን መታገት ተከትሎ ከቀናት በፊት ወደ አዲስ ዘመን ያቀናው የቢቢሲ ዘጋቢ ከተማዋ ሃዘን እንዳጠላባት ይናገራል።
የታጋች ቤተሰቦች ፊታቸው ጠቁሮ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆነው ነው ያገኘኋቸው የሚለው ዘጋቢያችን ቤተሰቦችን ማነጋገር እጅግ አሳዛኝ እንደነበር ያስረዳል።
መሪጌታ የኔነህ አዱኛ
አጭር የምስል መግለጫመሪጌታ የኔነህ አዱኛ
መሪጌታ የኔነህ አዱኛ የተማሪ ግርማሽ የኔነህ አባት ናቸው።
መሪጌታ የኔነህ ''በጥር 2 ተለቀዋል ስንባል ደስ ብሎን ነበር፤ ነገር ግን እስካሁን ከልጆቻችን ጋር አልተገናኘንም። መንግሥትም ያለን ነገር የለም። ገድለውብን ይሆናል ብለን እየፈራን ነው። በዚያ ላይ ልጆቹ አይተውት የማያውቁትን ነገር ሲያዩ ይደነግጣሉ ብለን እናስባለን። ሞተውም ከሆነ እውነቱን ነግረውን ቤተሰብ ጋር ተሰባስበን አልቅሰን እርማችንን ብናወጣ ይሻለናል፤ እንዲህ በየቀኑ ምን ሆነው ይሆን እያልን በሰቆቃ ከምንኖር" ይላሉ።
መሪጌታ እንደሚሉት የልጃቻቸው መታገት በቤተሰባቸው ላይ ከፍተኛ ጭንቀት ማሳደሩን ይናገራሉ። "ባለቤቴ ጨንቅላቷ ተጨንቆ ጸበል ወስጄ ነው ያከረምኳት" በማለት ይናገራሉ።
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
አጭር የምስል መግለጫወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ ናቸው።
ወ/ሮ ማሬ የእጅ ስልክ ስለሌላቸው በላይነሽን በስልክ ካገኙ ሰነባባተዋል። "ስልክ ስለሌለኝ የሆነው ሁሉ የምሰማው ከሰው ነው" ይላሉ።
''እህል አልበላ። ሌተ ተቀነ አይ ጉድ እያልኩ ነው። እግዜር ቢሰማን፤ መንግሥትም ቢራራልን፣ ልጆቻችን ቢሰዱልን እያልን ነው . . . አሳድጌ አሳድጌ ልጅ የለኝም ማለት ነው?" ሲሉም መልሰው ይጠይቃሉ።
ተማሪዎቹን መንግሥት እንዳስለቀቃቸው ሲሰሙ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቷቸው እንደነበረ የሚያስታውሱት ወ/ሮ ማሬ፤ "ወሬ ሆኖ ቀረ እንጂ" በማለት ተማሪዎቹ ተለቀዋል ቢባልም ከልጃቸው ጋር ሳይገናኙ እንደቀሩ ያስረዳሉ።
አቶ ሃብቴ እማኙ
አጭር የምስል መግለጫአቶ ሃብቴ እማኙ የተማሪ ግርማ ሃብቴ ወላጅ አባት
አቶ ሃብቴ እማኙ የተማሪ ግርማ ሃብቴ ወላጅ አባት ናቸው።
ልጃቸው ግርማ ከታገተ በሶስተኛው ቀን በአጋቾቹ ስልክ ደውሎላቸው እንደነበረ ያስታውሳሉ። "የነበረበትን አልነገረኝም። ብቻ ደህና ነኝ ነው ያለኝ።"
"ተስፋዬ የነበረው እሱ ነው" የሚሉት አቶ ሃብቴ፤ "እናቱ ቤተ-ክርስቲያን እየተንፏቀቀች እኔም የምሰራው ቅጡ ጠፋኝ። ልጄ የሚያውቀው ነገር የለም፤ የቤት ልጅ ነው። እንኳን የሰው አገር የራሱንም አያውቀው። . . . እናቱም የእሱን ሁኔታ አይታ በቤት ውስጥ የሉትን ልጆች ልትመራልኝ አልቻለችም" ይላሉ።
አቶ ሃብቴ "የማደርገው ጠፋኝ፤ ከፍ ብል ሰማይ ዝቅ ብል መሬት ሆኖብኝ፤ የእሱን መከራ ሳላይ ብሞት አይነደኝም ነበር" ይላሉ።
Presentational grey line
የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ላቀ አያሌው ከታገቱ ተማሪዎች ወላጆች መካከል የተወሰኑትን አነጋግሬአለሁ ይላሉ። ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ፤ እንደ አገር ተማሪዎችን ለማስለቀቅ የሚደረገው ጥረት አናሳ በመሆኑ ፈጥኖ መፍትሔ ማግኘት አልቻለም ባይ ናቸው።
«በተለይም አካባቢውን የሚያስተዳድረው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና የፌዴራሉ መንግሥት ትኩረት መስጠትና ተማሪዎችን ማስለቀቅ አለባቸው» በማለት ለክልሉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።

የማሕበራዊ ሚድያ ጩኸት

የተማሪዎች መታገት ከተሰማ ወዲህ ጀምሮ በማሕበራዊ ሚድያዎች በተለይም በፌስቡክና ትዊተር አለፍ ገደም ያሉ ዘመቻዎች መካሄድ ጀምረው ነበር። ከጥቂት ቀናት በፊት ጀምሮ ግን የማሕበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ጩኸታቸውን በሰፊው ማሰማት ጀምረዋል።
ታዋቂ ኢትዮጵያዊያን የማሕበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችም ዘመቻውን ተቀላቅለዋል። በተለይ ትዊተር በተሰኘው ማሕበራዊ መድረክ ላይ #Bringourgirlsback #Bringourstudentsback #WhereAreTheStudents? #ተማሪዎችየትገቡ? የተሰኙ ዘመቻዎች በመካሄድ ላይ ናቸው።

ስለታገቱት ተማሪዎች የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች በአማራ ክልል፡ ተካሄዱ


በባህር ዳር
አጭር የምስል መግለጫባህር ዳር
ሁለት ወር ለሚጠጋ ጊዜ የደረሱበት ያልታወቀ የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደህንነት ያሳሰባቸው በተለያዩ የአማራ ክልል ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች ድርጊቱን የሚቃወሙ ሰልፎች አካሄዱ።
በዩኒቨርስቲው ያጋጠመን አለመረጋጋት ሸሽተው ወደ መጡበት ሲመለሱ ባልታወቁ ወገኖች ተይዘው ደብዛቸው የጠፋው ተማሪዎች ጉዳይ ከመገናኛ ብዙሃን ርዕስነት አልፎ ለሰልፎቹ መካሄድ ምክንያት ሆኗል።
በዛሬው ዕለት በአማራ ክልል ርዕሰ ከተማ በተካሄደው የተማሪዎቹን መታገት በሚያወግዘው ሰልፍ ላይ በርካታ ቁጥር ያለው የከተማው ነዋሪ ተሳታፊ ሆኗል። በዚህም ምክንያት የተለያዩ የመንግሥትትና የግል ተቋማት ተዘግተው እንደነበር ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የሰላምና የህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ በክልሉ የተካሄዱት ሰልፎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን አስታውቋል።
ቢሮው ይህን ይበል እንጂ በባህር ዳር በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የክልሉ ባለስልጣናት በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለተገኘው ህዝብ መልዕክት ለማስተላለፍ ሲሞክሩ የተቃውሞ ድምጽ ተሰምቶ ዝግጅቱም መቋረጡን ሪፖርተራችን ከስፍራው ዘግቧል።
ከክቡር ትሪቡን አቅጣጫ ደንጋይ የተወረወረ ሲሆን ከስታዲየም ውጪም የተኩስ ድምጽ ሲሰማ ነበር።
በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር ከተማ በርካታ ጸጥታ አስከባሪዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ እና ከተማዋም ወደ የተረጋጋ እንቅስቃሴ መመለሷን ሪፖርተራችን ታዝቧል።
ከባህር ዳር ከተማ ውጪ ደብረማርቆስ፣ ወልዲያ፣ ቆቦ፣ዋድላ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ዱር ቤቴ፣ ዳንግላ፣ ደብረ ብርሃን፣ ፍኖተ ሰላም፣ እና በሬ የተቃውሞ ሰልፎቹ የተካሄዱባቸው ከተሞች ናቸው።
በተቃውሞ ሰልፎቹ የተሳተፉ ሰዎች መንግሥት የታገቱትን ተማሪዎች ጉዳይ ችላ ማለቱንና ተገቢውን መረጃ ባለመስጠቱ ወቀሳ ከማቅረባቸው በተጨማሪ፤ ታጋቾቹ ተለቀዋል ተብሎ የተሰጠው መግለጫን "ሐሰተኛ" በማለት ምላሽ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል።
ድርጊቱን ለማውገዝ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉት ሰዎች መንግሥት ስለታገቱት ተማሪዎች ተገቢውን መረጃ እንዲሰጥ፣ ተማሪዎቹ እንዲለቀቁ፣ መንግሥት በአጋቾች ላይ እርምጃ እንዲወሰድና በጉዳዩ ውስጥ እጃቸው አለበት የሚባሉ አካላትም በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።
ሰልፈኞች በባህር ዳርImage copyrightAMMA
በሁሉም ቦታዎች በተካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች ላይ በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ የነበሩና ለወራት የደረሱበት ያልታወቁት ተማሪዎች ያሉበት ሁኔታ እንዲገለጽ እንዲሁም በቶሎ ተለቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ በአጽንኦት ተጠይቋል።
ታግተዋል የተባሉት ተማሪዎች ቁጥር 17 እንደሆነ የተነገረ ሲሆን ከመካከላቸው 13ቱ ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል። በዚህም መሰረት ባለፉት ሳምንታት በማሕበራዊ የመገናኛ መድረኮች ላይ "እህቶቻችንን መልሱ" በሚል ርዕስ ዘመቻዎች ሲካሄዱ ቆይተዋል።
ቢቢሲ እስካሁን ባገኘው መረጃ ሰላማዊ ሰልፎቹ በባሕር ዳር፣ በወልዲያ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በደብረ ብርሃን፣ በዱርቤቴ፣ ፍኖተሰላም፣ በራያ ቆቦ፣ በሸዋ ሮቢት፣ በዳንግላና በሌሎች ቦታዎች ተካሂደዋል።
ሰልፈኞቹ፤ "የታገቱት ተማሪዎች የት አሉ?"፣ "ደብተርና ስክርቢቶ የያዙ ተማሪዎችን ማገት ጀግንነት አይደለም"፣ "ለታገቱ ተማሪዎች መጮህ ፖለቲካ ሳይሆን ሰብዓዊነት ነው"፣ "መንግሥት ተለቀቁ ያላቸው ተማሪዎች የት አሉ?" የሚሉ ጥያቄዎችና መልዕክቶችን ማስተጋባታቸውን የቢቢሲ ዘጋቢ ከስፍራው ገልጿል።
በባህር ዳር በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ 6 የታጋች ተማሪ ወላጆች ተሳታፉ መሆናቸውን ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አንዱ አቶ መታገስ ገ/ሚካኤል ለቢቢሲ ተናግረዋል።

wanted officials