other links

Saturday, August 13, 2016

5ቱን የአፍሪካ ውብና ደማቅ ከተሞች ይተዋወቁ




ከታምራት ሲሳይ


1. ሉዋንዳ


የአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ በአፍሪካ በነዳጅ ምርት፣ የባህር ወደብና የአስተዳደር ማዕከል ናት:: በአለፉት አስርት ዓመታት ከአፍሪካ አገራት የላቀ ዕድገት አሳይታለች::


በቻይና የኢንቨስትመንት ኮርፖሬሽን ግንባታ እንደ ምዕራባዊያን ከተሞች የመጠቀች ሆናለች::





2. አጋዲር


የሞሮኮ አንዷና ዋነኛ ከተማ ናት:: ከተማዋ በ1960 በርዕደ መሬት ከተመታች በኋላ እንደገና የተገነባች ናት:: አሁን የባህር ዳርቻ ያላት የጎብኝዎችን ቀልብ ከመላው ዓለም የምትስብ ተመራጭ ከተማ ከሥራ ቦታ በሚጠፉ ሰራተኞች የተዘጋው ሆናለች::





3. ናይሮቢ


የኬኒያ መዲና እና ትልቋ ከተማ ናት። ከምስራቅ አፍሪካ ከተሞች በህዝብ ብዛትም ቀዳሚ ናት:: ከአፍሪካ በፖለቲካም ሆነ በምጣኔ ሀብት ዕድገት ከመሪ ከተሞች ተርታ ተሰልፋለች:: የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚበዙባትና ዓለማቀፍ ተቋማት የከተሙባት በመሆኑ ደማቅ አድርጓታል።





4. ሌጐስ


በህዝብ ብዛቷ ከናይጀሪያ ቀዳሚ የአገሪቱ መዲናም ናት:: የሌጐስ ደሴት ከሰማይ ጠቀስ ፎቆችዋና በጅምላ ንግድ ማዕከልነቷ ትታወቃለች:: ከበርካታ ብሔሮቿ ውበት ጋር ተዳምሮ ከተማዋ ውብና ደማቅ መሆን አስችሏታል።





5. ካይሮ


የስልጣኔ መናኸሪያዋ፣ የግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ ከመካከለኛው ምስራቅ አገራት እና ከአፍሪካ ሁለተኛዋ ትልቋ ከተማ ናት:: ከተማዋ የ24 ሰዓት ከተማ ተብላም ትታወቃለች:: ካይሮ 24 ሰዓት ሙሉ ደምቃ ውላ ታነጋዋለች።

No comments:

Post a Comment