Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, November 2, 2019

የኩዌት ባለስልጣናት የተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ሰዎችን እንደ 'ባሪያ' ሲሸጡ የነበር ያሏቸው ግለሰቦች ላይ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነ ገለጹ።

ኩዌት በድረገጽ ሰዎችን ሲሸጡ የነበሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረች

በበይነ መረብ የሚሸጡት ሴቶች

የቢቢሲ አረብኛ ክፍል የምርመራ ቡድን በዚህ ሳምንት ባስተላላፈው ዘገባ፤ እንደ ጉግል እና አፕልን የመሳሰሉ የበይነ መረብ መድረኮችን በመጠቀም ኩዌታውያን ከተለያዩ አገራት የመጡ ስደተኞችን እንደሚሸጡ ያሳያል። በፌስቡክ ስር በሚተዳረው በኢንስታግራም ጭምርም ሰዎች እንደሚሸጡ ዘገባው ያትታል።

ለሽያጭ የሚቀርቡት አብዛኛዎቹ ሴቶች ሲሆኑ፤ ለቤት ሠራተኝነት ነው የሚፈለጉት። ሻጮቹም እንደ #maids for transfer እና #maids for sale የመሳሰሉ ሀሽታጎችን በመጠቀም ሴቶቹን ለሽያጭ ያቀርቧቸዋል።
ይህንን መሰል ማስታወቂያዎችን በመጠቀም የቤት ሠራተኞችን ሲሸጡ የነበሩ ግለሰቦች ማስታወቂያቸውን እንዲያወርዱ መታዘዛቸውንም ባለስልጣናቱ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በዚህ ተግባር ተሰማርተው የሚገኙ ሰዎች በድጋሚ እንደማይፈጽሙት የሚገልጽ ሕጋዊ ወረቀት እንዲፈርሙና መጸጸታቸውን እንዲገልጹ ተደርገዋል በማለት ስለተወሰደው እርምጃ ገልጸዋል።
ኢንስታግራም በበኩሉ ቢቢሲ ጉዳዩን ካሳወቀው በኋላ እርምጃ እንደወሰደ አስታውቋል። አክሎም ኢንስታግራምና ፌስቡክን በመጠቀም ሰዎችን ለሽያጭ ለማቅረብ የተከፈቱ ገጾችን እንደሚከታተልና እንደሚያግድ ገልጿል።
ቢቢሲ የምርመራ ዘገባውን ሲሠራ በብዛት ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩት ገጾች በሙሉ በአሁኑ ሰአት እንቅስቃሴያቸው ቆሟል።

በኩዌት የሰው አቅርቦት ባለስልጣን የሆኑት ዶክተር ሙባራክ አል አዚሚ ደግሞ በምርመራ ዘገባው ላይ የታየችውን የ16 ዓመት ጊኒያዊ ታዳጊ ጉዳይን በቅርበት እንደሚከታተሉትና ጥቅም ላይ የዋለው 'ፋቱ' የተባለው መተግበሪያ ምርመራ እንደሚደረግበት ገልጸዋል።
በዘገባው የቀረበውና አንዲትን ሴት ለመሸጥ ሲስማማ የነበረው የፖሊስ አባልም ምርመራ እየተደረገበት ነው ተብሏል። ሌሎች ሰዎችም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን ተጎጂዎችም ካሳ ይከፈላቸዋል ብለዋል ባለስልጣኑ።

Friday, November 1, 2019

ከ300ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች ያሉት ቴክቫህ ኢትዮጵያ



የቴክቫ ገፅ
አሁን አሁን በኢትዮጵያ በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጩ የጥላቻ ንግግርንና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመቆጣጠር በግለሰብ፣ በተቋማት እና በመንግሥት ደረጃ ለመቆጣጠር የተለያዩ ጥረቶች ሲደረጉ ይስተዋላል።
ጉዳዩ ወጣቶችንም ሳያሳስብ አልቀረም ታዲያ። ለዚህም ነው ቴክቫህ ኢትዮጵያ የተጀመረው።
አቅሌሲያ ሲሳይ በመላ ሃገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች መረጃን በዋናነት የሚያገኙት ከማህበራዊ ሚዲያ መሆኑን ትናገራለች።
የኤሌክትሪካል ምህንድስና እና ኮምፒውተር ተማሪ የነበረችው አቅሌሲያ፤ "በዩኒቨርስቲ ውስጥ ሳለን የምናገኘውን መረጃ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አዳጋች ነበር" ትላለች።
በዚህ ሁሉም የራሱ የሆነ ገፅ ከፍቶ የተለያዩ መረጃዎች በሚያሠራጭበት ዘመን፤ በዩኒቨርስቲ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች ዐይናቸውን ለቴሌቪዥን ጆሯቸውን ለሬዲዮ ለመስጠት ጊዜ እንዳልነበራቸው ታስታውሳለች - አቅሌሲያ።
ሁሉም ሰው ሞባይሉ ላይ ተጥዶ በማህበራዊ ትስስር መድረኮች በኩል የሚያገኘውን መረጃ ይቃርማል።
እርሷ በዩኒቨርስቲ በነበረችባቸው የመጀመሪያ ዓመታት ፌስቡክ ለእነዚህ ተማሪዎች መረጃን በማቅረብ አልፋና ኦሜጋ ነበር።
በኋላ ግን ቴሌግራም መጥቶ የመረጃ ማቅረቡን መንበር ተቀላቀለ። ያኔ ነው የአቅሌሲያ ጓደኞች ስለቴሌግራም መነጋገር የጀመሩት።
አቅሌሲያም ስለ ቴክቫህ ኢትዮጵያ ሰማች፤ ቤተሰብም ሆነች።
ፀጋአብ ወልዴ ተወልዶ ያደገው ይርጋለም ነው። ሐዋሳ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን በጋዜጠኝነትና በተባባሪ አዘጋጅነት መስራቱን ይናገራል። አሁን ደግሞ የቴክቫህ ኢትዮጵያ መስራችና የቤተሰብ አባል ነኝ ብሎ ነው ራሱን የሚያስተዋውቀው።
ቴክቫህ ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ከ320 ሺህ በላይ የቤተሰብ አባላት ያሉት እና ቴሌግራም በተሰኘው የማህበራዊ ትስስር መድረክ ላይ መረጃ የሚያቀብል ገፅ ነው።
ገፁን የሚቀላቀሉት ሁሉ የቤተሰብ አባላት ተብለው እንደሚጠሩ የሚናገረው ፀጋአብ ቴሌግራምን በስልኩ ላይ ጭኖ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዚህ ገፅ አባል ያደረጋቸው ስልኩ ላይ የሚገኙ ከሃያ እስከ ሠላሳ ሰዎችን ብቻ መሆኑን ያስታውሳል።
እነዚህ ሰዎች በስልኩ ውስጥ ቁጥራቸው የሰፈረ ባልንጀሮቹ ይሁኑ እንጂ የቴሌግራም ተጠቃሚም አልነበሩም።
ቀስ በቀስ ግን አንዱ አንዱን እየሳበ፤ ሌላኛው ለጓደኛው እየተናገረ የገፁ ተከታዮች ቁጥር ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
እነዚህን የቤተሰብ አባላት አንድ የሚያደርጋቸው መረጃ መፈለግ ብቻ ነው? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላት የቴክቫህ ቤተሰብ አቅሌሲያ፤ ፈጠን ብላ "...ብቻ ሳይሆን ሰብዓዊነት ይቅደም የሚለውም አንድ ያደርገናል" ብላለች።
Image copyright
ቴክቫ የት ተጠነሰሰ?
ፀጋአብ በሐዋሳ ኤፍ ኤም 100. 9 ላይ፣ ከዚያ በኋላ ደግሞ የሐዋሳ ድምፅ ላይ ሲሠራ መረጃ አጠናቅሯል፤ አደራጅቷል። ፀጋአብ ዕድሜው ሃያዎቹን ያልዘለለ ወጣት ነው። በርካታ ወዳጆቹ እና የእድሜ አቻዎቹም የሚገኙት በትምህርት ቤት ውስጥ ነው።
ታዲያ በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት የተነሳ በዩኒቨርስቲዎችም ውስጥ ረብሻ፣ አመፅና ሞት ሁሌም ይሰማል። እነዚህን መረጃዎችን የሚያገኘው ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት መሆኑን ያስታውሳል። ነገር ግን ሁሌም አንድ ክፍተት ይታየዋል።
ይህ ለእርሱም ሆነ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ላሉ ጓደኞቹም የሚደርስ መረጃ፤ የብሔር ታፔላ አንጠልጥሎ፣ ስድብ አዝሎ፣ በቀል አንግቦ እንደሚንቀሳቀስ አስተዋለ።
"በፌስቡክ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ ዜናዎችን አያለሁ። ይህንን ደግሞ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሉ ወጣቶችም ያዩታል" ይላል።
አቅሌሲያም ይህንኑ ታረጋግጣለች። ተመርቃ ከመውጣቷ በፊት በዩኒቨርስቲ ውስጥ የምትሰማቸው መረጃዎች፣ ተረጋግታ ትምህርቷን እንድትማር የሚያደርጉ ሳይሆኑ ስጋትን የሚያጭሩ፣ መከፋፈልን፣ አለመተማመንን የሚያነግሱ መሆናቸውን አትረሳም።
ጉዳዩ ያሳሰበው ፀጋአብ፤ ከዚህ የማህበራዊ ትስስር መድረክ የመረጃ ቋት ውስጥ ፍሬውን ከገለባ፣ እንክርዳዱን ከፍሬው ለይቶ ለማቅረብ ሁነኛ መፍትሄ ሆኖ ያገኘው ቴሌግራምን ነው።
እናም ሐምሌ 19 ቀን 2009 ዓ.ም ላይ ቴክቫህ ኢትዮጵያ ተመሰረተ።
ቴክቫህ ኢትዮጵያ የገፅ ስያሜ ነው። ቴክቫህ የሂብሩ ቃል ሲሆን ተስፋ ማለት ነው ሲል ያብራራል፤ ተስፋ ኢትዮጵያ ለማለት መፈለጉንም ይናገራል።
ቴክቫህ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እውነተኛ መረጃ ማድረስን ስንቁ አድርጎ ቢይዝም ከዚያ ባሻገር የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይም ወጣቱን ለማሳተፍ እንደሚሰራ ፀጋአብ ይናገራል።
ከዚህ ባለፈም ደግሞ በጥላቻና በሐሰተኛ ንግግሮች ዙሪያ በመነጋገር መማማር እንዲፈጠር የተለያዩ ዘመቻዎችን እንደሚያደርግ አቅሌሲያ ትናገራለች።
ቴክቫህ ከተለያዩ መገናኛ ብዙኀን የሚያገኛቸውን መረጃዎችን ከማቅረብ ባሻገር ተከታዮቹ ከያሉበት የሚልኳቸውን መረጃዎችንም ያቀርባል።
መረጃዎቹ ከየት መጡ፣ ማን ላከው የሚለውን በማጣራት ኃላፊነት እንዲሰማቸው በሚል ስማቸውን ጠቅሶ ያወጣል። ከተለያዩ መገናኛ ብዙኀን መረጃዎችንም ሲወስድ ያገኘበትን በመጥቀስ የገፁን ተዓማኒነት ለመጠበቅ ይጥራል።
ፀጋ አብ እንደሚለው ለየትኛውም አካል ወገንተኛ ሆኖ አይሰራም።
Image copyright
ለምን ቴሌግራምን መረጠ?
ኢትዮጵያ ውስጥ ይፋዊ ጥናት ባይኖርም የማህበራዊ ትስስር መድረክ ተጠቃሚዎች ፌስቡክ ቀዳሚ ምርጫቸው ይመስላል፤ ፌስቡክ ይቅርብኝ ያለ ትዊተር መንደር አይታጣም።
ፀጋአብ ግን የመረጠው ቴሌግራምን ነው። ለምን?
ፀጋአብ ፌስ ቡክ ብዙ ተከታዮች እንዳለው አልካደም። ነገር ግን በፌስቡክ ላይ የሚንሸራሸሩ የትኛውም ጉዳዮች ላይ [በጎም ይሁኑ መጥፎ] የሚሰጡ አስተያየቶች መከባበር የተሞላባቸው እና የተለያዩ ወገኖችን ስሜት ያገናዘቡ አይደሉም ይላል።
ሰዎች አስተያየት የመስጠት መብታቸው የተጠበቀ ቢሆንም የጥላቻ ንግግሮች፣ በስፋት የሚታዮበት መድረክ እንደሆነ ለመናገር አላመነታም።
"ፌስ ቡክ ላይ ምንም አይነት ገፅ የለንም" የሚለው ፀጋአብ ገፃችንን ፌስ ቡክ ላይ አድርገነው ቢሆን ኖሮ አንባቢያችን እኛን ብቻ አይቶን ሳይሆን በዙሪያችን የሚርመሰመሱ ሌሎች የመረጃ አቅራቢዎች ጋር ጎራ ብሎ በዚያው መረጃ ሊወሰድ የሚችልበት እድል ሰፊ እንደሚሆን ይናገራል።
በቴሌግራም ላይ አንድ ሰው ፈልጎ የተቀላቀለው ካልሆነ በስተቀር ሌሎች ጉዳዮች ስለማይመጡ ተጠቃሚዎቻቸውን ቢያንስ ከስድብና ከጥላቻ ንግግር ለመጠበቅ እንደሚያስችላቸው በመግለፅ የቴሌግራምን ጠቀሜታ ያስረዳል።
ከዚህ ባሻገርም ቴሌ ግራም እንደ ፌስቡክ አስተያየት በመስጠት ስድብ የመወራወሪያ ዕድል ስለሌለው ራስን ከሐሰተኛ ዜናና ከጥላቻ ንግግር ለመጠበቅ ሁነኛ መላ ሆኖ እንደታየው ይገልጻል።
"በቴሌግራም ቢያንስ የተሻለ መደማመጥ የሚችል፣ የሌላውን ሐሳብ አክብሮ የእርሱን ሐሳብ የሚገልፅ ተጠቃሚ ፈጥረን ወደ ሌላዎቹ የማህበራዊ መድረኮች ወደፊት ልንሄድ እንችላለን፣ አሁን ግን ቴሌ ግራም ብቸኛ አማራጫችን ነው" ብሏል- ፀጋአብ።
ፀጋአብ ቴክቫህ ኢትዮጵያ በተመሠረተበት በዚህ ሁለት ዓመት ውስጥ አንድ ቀን ብቻ መረጃ ለቤተሰብ አባላቱ ሳያደርስ መቅረቱን ያስታውሳል።
ያ- ቀንም ሕመም ገጥሞት እርሱና ሞባይሉ ተራርቀው የነበረበት ነው።
በመላው ሀገሪቱ አልያም በትላልቅ ከተሞች ኢንተርኔት ድርግም ብሎ ሲጠፋ እንኳ እርሱ ዋይፋይ ወደሚያገኝበት ጎራ ብሎ መረጃዎቹን ለቤተሰብ አባላቱ እንደሚያደርስ ይናገራል።
ፀጋአብ መረጃዎቹ ለመቀበልም ሆነ ለማድረስ ሳምሰንግ ኖት 9ንና ሳምሰንግ ኤ70 ስልኮችን ይጠቀማል። የባትሪ እድሜያቸው ረዥም ስለሆነ ነው የመረጥኳቸው ሲል ያክላል።
የቴክቫህ የቤተሰብ አባላት በዋናነት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ወጣቶች ናቸው። እነዚህ ወጣቶች ደግሞ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡና የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ ናቸው።
Image copyright-ETH
ፀጋአብ ይህ ጉዳይ በሚገባ ያሳስበዋል። ለዚህም በዚህ ዓመት ቴክቫህን በኦሮምኛ ቋንቋ ጀምሮ እየሞከረ እንዳለ ይናገራል። በሌሎች ቋንቋዎችም ለመጀመር እቅድ ይዟል። በማለት ነገሮች ካሰበው ፍጥነት በላይ በመሄዳቸው ሌሎች ተጓዳኝ ተግባራትን ለማከናወን አዳጋች እንደሆነበት ያስታውሳል።
በሁለት ዓመት ውስጥ ከ300ሺህ በላይ ተጠቃሚዎችን እደርሳለሁ ብሎ አለማሰቡን የሚናገረው ፀጋአብ ሌሎች በርካታ ሀሳቦች እንዳሉትም አጫውቶናል።
ፀጋአብ እንደሚለው በርካታ ሰው የሚያውቀው ወቅታዊ መረጃዎችና ዜናዎች የሚቀርቡበትን ቴክቫህ ኢትዮጵያን ብቻ ነው። ይሁን እንጂ የታመሙ ሰዎች የሚያሳክሙበት፣ የተቸገሩ ድጋፍ እንዲያገኙ የሚያደርጉበት 4ሺህ ተከታዮች ያሉት ቴክቫህ ኤይድ የሚባል ገፅ እንዳላቸው ይናገራል።
ይህ ብቻም ሳይሆን ተማሪዎች ኦሮምኛ፣ትግርኛና ግዕዝን በቀላሉ በስልካቸው መማር እንዲችሉ የሚያገለግል 24ሺህ ተከታዮች ያሉት ቴክቫህ ኢዱ የተሰኘ ገፅም አለው። እርሱ እንደሚለው ይህ ገፅ በበጎ ፍቃደኞች የቤተሰብ አባላት የተደራጀ ነው።
"ወደፊት የቤተሰብ አባላቶቻችንን እያየንና እነርሱ ሊያገለግሉ በሚችሉበት መስክና ቋንቋ መረጃዎችን ለማድረስ መሞከራችን አይቀርም" ይላል -ፀጋአብ።
የቴክቫ ኢትዮጵያ ዘመቻዎች
Image copyrightTIKVAH-ETH
በተቋማት ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በማህበራዊ መገናኛ ብዙኀን ጥላቻዎች ተሰብከዋል፤ በዩኒቨርስቲ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች ልዩነት እንዲሰፋ የሚሰሩ መልዕክቶች በሰፊው ይሠራጫሉ የሚለው ፀጋአብ በማህበራዊ ትስስር መድረክ ላይ የጥላቻ ንግግርን የሚቃወሙ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ መቆታቸውን ይናገራል።
የቴክቫህ ቤተሰብ አባላት ግን ይህንን የጥላቻ ዘመቻ ተገዳድሮ የሚቆም የሰላም፣ የመቻቻል መልዕክትን ማስተላለፍ እንደሚቻል ለማሳየት መንቀሳቀሳቸውን ይገልጣል።
ባለፈው ዓመት የቴክቫህ የቤተሰብ አባላት በ11 ዩኒቨርስቲዎች በመንቀሳቀስ የጥላቻ ንግግሮችን በተመለከተ ከተቋማቱ ተማሪዎች ጋር ተወያይተዋል።
በዚህ ጉዟቸው ከመቀሌ እስከ አርባ ምንጭ፤ ከወልቂጤ እስከ ደብረብርሀን፤ ከዋቻሞ እስከ ወሎ፤ ከሐሮማያ እስከ ወላይታ ዩኒቨርስቲዎች ድረስ ተጉዘዋል።
በሄዱበት ሁሉ ተማሪዎች እርስ በእርሳቸው እንዲደጋገፉ፣ አንዱ አንዱን እንዲያውቅ የበኩላቸውን ጥረት ማድረጋቸውን ይናገራል።
"በአንዳንድ ተቋማት ይህንን መልዕክት ይዞ መሄድ አስቸጋሪ ቢሆንም እኛ ግን ሀሳባችንን ደግፎ የሚቆም አንድ ሰው እንኳን ቢገኝ በማለት ሄደናል፤ በመሄዳችንም ውጤታማ ሆነናል።" ይላል።
ከተማሪዎቹ ጋር በሚኖር ውይይት በአርባ ምንጭ የሀገር ሽማግሌዎች እንደነበሩ የሚያስታውሰው ፀጋአብ በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ግን በወጣቶች መካከል ብቻ ውይይት መደረጉን፣ በየዩኒቨርስቲዎቹ ባሳለፉትም ሁለት ሁለት ቀን አብዛኛዎቹን ወጪዎች የቴክቫህ ቤተሰብ አባላት መሸፈናቸውን ይናገራል።
ሰው በሰውነቱ እንዲከበር ከዚያም ስለሌሎች ጉዳዩች ለመነጋገር የጥላቻ መልዕክቶችን ማስወገድ ተገቢ መሆኑን የምትናገረዋ አቅሌሲያ በሚቀጥለው ዓመትም ተመሳሳይ መልዕክትን በማንገብ እንደሚጓዙ ነግራናለች።
ቴክቫህ የቴሌግራም ገፅ አሁን ወጪውን የሚሸፍነው ከሚያስተላልፋቸው ማስታወቂያዎች መሆኑን ፀጋአብ ይናገራል።
ቴክቫህ ወደፊት የጥላቻ ንግግሮችን ለማስቀረት፣ ሐሰተኛ ዜናዎችን ለመዋጋት በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የመጓዝ፣ በበጎ አድራጎት በሰፊው ለመሰማራትና ተፅዕኖ መፍጠር የሚችል የመገናኛ ብዙኀን ለማቋቋም ሀሳብ እንዳለው ፀጋአብ ገልፀፆልናል።

Wednesday, October 30, 2019

የባልደራስ፣ የአብን አባላትና የብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት ተፈቱ

የተፈቱት የባልደራስ አባላትImage copyrightFACEBOOK
የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት፣ የአብን ፓርቲ አባላት እንዲሁም የብርጋዴል ጄነራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት በዛሬው ዕለት ተፈተዋል
ግለሰቦቹ የተታሰሩት ከሰኔ 15 ግድያ ጋር በተያየያዘ በሽብር ተጠርጥረው ሲሆን አቃቤ ሕግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ ቢሰጠውም ክስ ሳይመሰርት መለቀቃቸውን በዛሬው ዕለት ከእስር የተፈቱት አቶ ስንታየሁ ቸኮል ለቢቢሲ በስልክ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት (ባልደራስ) አባላት ጠበቃ የሆኑት አቶ ሔኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ላለፉት አራት ወራት በእስር ላይ ያሳለፉት ደንበኞቻቸው የተለቀቁት በመታወቂያ ዋስ መሆኑን ተናግረው ምንም ዓይነት ክስ ሳይመሰረት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፈታታቸውን ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት ህዝብ ግንኙነት ከሆኑት አቶ ስንታየሁ ቸኮል በተጨማሪ የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት አባላት የሆኑት አቶ መርከቡ ኃይሌ፣ ኤሊያስ ገብሩ እንዲሁም አዳም ጂራ መፈታታቸውን አቶ ሔኖክ ገልጸዋል።
በተለምዶ ሶስተኛ የሚባለው አዲስ አበባ ፓሊስ ጣቢያ ለወራት ታስረው የነበሩት አቶ ስንታየሁ እንደሚፈቱ የሰሙት ዛሬ ከሰዓት እንደነበር ተናግረዋል።
"ፖሊስ የምርመራ ጊዜ ወስዶ ቢመረመርም ያገኘብን መረጃ ስለሌለ በነጻ ተለቀናል" ያሉት አቶ ስንታየሁ " እኛ ሳንሆን እውነት ነው ያሸነፈው" ብለዋል።
አቶ ስንታየሁ አክለውም መጀመሪያም "የህሊና እስረኞች ነበርን በነጻ ተለቅቀናል፤ ዛሬ ተፈታን ብለን ነገ ከትግል የምንሸሽበት መንገድ የለም አሸናፊ ሆነን ነው የወጣነው" ብለዋል።
የእስር ቆይታቸው ፈታኝ እንደነበር የሚናገሩት አቶ ስንታየሁ በጨለማ ቤት ውስጥ ከሁለት ወር በላይ ማሳለፋቸውን ለቢቢሲ አስረድታዋል።

"መንፈሳችንን ለመስበር ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም፤ የሕዝብ ጥያቄ በመያዛችን ከትግል የምናቆምበት ነገር የለም" ሲሉ ከተፈቱ በኋላ ተናግረዋል።
አክለውም "እስር ቤት ውስጥ ሆነን አልተጎዳንም ፤ሕዝቡ እየመጣ እያጽናን ነው የነበረው። በመታሰር ውስጥም አሸንፈናል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ቀጣይ ብዙ ትግል አለ የሚሉት አቶ ስንታየሁ "እኔ ብፈታም ጥያቄያችን አልተፈታም" በማለት የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት የያዘው ጥያቄ መፈታት እንዳለበትም አስረድተዋል።
በሌላ በኩል አስራ አራት የአብን አመራሮችና ደጋፊዎች በዛሬው እለት መፈታታቸውን ጠበቃቸው አቶ አበረ መንግሥቴ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ክስ ካልቀረበ ይፈቱ በሚል ውሳኔ ካገኙት ውስጥ አምስት ሰዎች ለጊዜው እንዳልተፈረመላቸው ጠቅሰው ክስ ይመስረት አይመስረት የሚለው ጉዳይም ግልፅ አይደለም ብለዋል።
የፓርቲው አባላት ከመታወቂያ ጀምሮ፣ አምስት ሺ፣ ሰባት ሺና አስር ሺ ብር ዋስ መፈታታቸውን ጠበቃቸው ጨምረው አስረድተዋል።
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም ቀርበው የአስራ አምስት ቀን የክስ መመስረቻ የተጠየቀባቸው ሲሆን በመጪው አርብም ይጠናቀቃል።
እስከ አርብ ባለው ጊዜም ውስጥ ክስ ካልተመሰረተ የዋስትና መብታቸውንም ማቅረብ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል።
የዋስ መብታቸው ተጠብቆ በዛ አግባብ ነው የተፈቱት ስለ አፈታታቸው ሁኔታም እስካሁን ባለው እንደማይታወቅና ክስ የሚያስመሰርት ሁኔታ ይኑር አይኑር እንዲሁም ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎች በመጪው ቀናት እንደሚታወቁም ተናግረዋል።
አቶ ክርስቲያንን ጨምሮ ዘጠኝ አባላት እንዳልተፈቱም አቶ አበረ አስረድተዋል።
የብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት ወ/ሮ ደስታ አሰፋ በዛሬው ዕለት መፈታታቸውንም ጠበቃቸው ነግረውናል።

Wednesday, October 2, 2019

ፌስቡክ 'የላይክ' ቁጥርን ማሳየት ሊያቆም ነው


የፌስቡክ 'ላይክ' ምልክት
Image copyrightGETTY IMAGES
ፌስቡክ ኢንስታግራም ላይ የወሰደውን እርምጃ ተከትሎ በእያንዳንዱ የፌስ ቡክ የተጠቃሚዎች መልዕክት ስር የተሰጡ የመውደድ (ላይክ) ቁጥሮችን አለማሳየት ሙከራ እርምጃውን አውስትራሊያ ውስጥ መጀመሩን አስታወቀ።
ከዛሬ አርብ ጀምሮ አውስትራሊያ ውስጥ ያሉ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በሌሎች መልዕክት ላይ የተሰጡ የላይክ እንዲሁም የሌሎች ምላሽ ቁጥሮችን መመልከት አይችሉም።
አወዛጋቢ የሆነው ይህ ውሳኔ የፌስቡክ ተዛማጅ ማኅበራዊ መድረክ በሆነው ኢንስታግራም ላይ ከሐምሌ ወር ጀምሮ በበርካታ ሃገራት ውስጥ ተግባረዊ ተደርጓል።
ፌስቡክ ለአንድ መልዕክት የሚሰጡ የላይክ ቁጥሮችን ከባለቤቶቹ ውጪ ሌሎች እንዳያዩ የሚያደርገውን እርምጃውን ለመውሰድ የወሰነው በተጠቃሚዎች ላይ የሚደርሰውን ማኅበራዊ ጫና ለመቀነስ በማሰብ ነው ተብሏል።

ኩባንያው እንዳለው የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በራሳቸው መልዕክቶች ስር የሚሰጡ 'የመውደድ' ምላሾችን መመልከት ግን ይችላሉ።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ሚያ ጋርሊክ ለአውስትራሊያ አሶሺየትድ ፕሬስ እንዳሉት "የቁጥርን ነገር ከጉዳዩ ስናወጣ፤ ተጣቃሚው ዋና ትኩረትን በተሰጡ የላይክና የሌሎች ምላሾች ብዛት ላይ ሳይሆን በሚደረጉ ምልልሶችና በቀረቡ መረጃዎች ጥራት ላይ ብቻ ያደርጋል" ብለዋል።
ቃል አቀባዩ አክለውም ድርጅታቸው ይህንን ለውጥ ከማድረጉ በፊት የሥነ አእምሮ ባለሙያዎችንና ማንጓጠጥ እንዲሁም ማስፈራራትን የሚከላከሉ ቡድኖችን ማማከሩን ገልጸዋል።
በማኅበራዊ መገናኛ መድረኮች ላይ ከፍተኛ ተሰሚነት ያላቸው አንዳንድ ሰዎች ግን በአንድ መልዕክት ላይ የሚታይ የመውደድ አሃዝ ለሚያገኙት ገቢ ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ እርምጃውንተቃውመውታል።

Monday, September 23, 2019

ውሃ ውስጥ ለፍቅረኛው የአግቢኝ ጥያቄ ያቀረበው ግለሰብ ሰጥሞ ሞተ



ስቲቨን ዌበርImage copyrightKENESHA ANTOINE
አንድ አሜሪካዊ ጎብኚ ታንዛኒያ ውስጥ ለፍቅር ጓደኛው የጋብቻ ጥያቄ ለማቅረብ ወደ ውሃ ውስጥ ገብቶ ሳይመለስ መቅረቱ ተሰምቷል።
ስቲቨን ዌበር የተባለው ግለሰብ እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በታንዛኒያ ፔምባ ደሴት ላይ በሚገኝ ማንታ በተባለ ሪዞርት ነበር ያረፉት። ስቲቨን ለፍቀረኛው ታገቢኛለሽ ወይ የሚለውን መልዕክቱን በወረቀት ላይ ጽፎ ነበር ወደ ውሃ ውስጥ የገባው።
ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በፌስቡክ ገጿ ላይ ባስተላለፈችው ምልዕክት ጥልቅ ወደሆነው ባህር አካባቢ የሄደው ስቲቨን መመለስ ሳይችል መቅረቱን አረጋግጣለች።
የማንታ ሪዞርት አስተዳደር ለቢቢሲ እንደገለጸው ስቲቨን ዌበር ውሃ ጠለቃ በሚደረግበት አካባቢ ገብቶ ህይወቱ ያለፈችው ባሳለፍነው ሐሙስ ከሰዓት ላይ ነበር።
''ባሳለፍነው ሐሙስ በሪዞርታችን በተፈጠረው ክስተት እጅግ ማዘናችንን መግለጽ እንፈልጋለን'' ብሏል ድርጅቱ በመግለጫ።
የሪዞርቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ማቲው ሳውስ እንዳሉት መላው የማንታ ሪዞርት ሰራተኛ በተፈጠረው አደጋ ተደናግጠዋል።
አጭር የምስል መግለጫስቲቨን ዌበር እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን
ስቲቨን ዌበር እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በሪዞርቱ የውሃ ጠለቃ በሚደረግበት የባህሩ ክፍል ለአራት ቀናት ለመቆየት ቀድመው ቦታ አስይዘው የነበረ ሲሆን ቦታው ከባህር ዳርቻ በግምት በ250 ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።

ለቀናት በአካባቢው ሲዝናኑ የቆዩት ጥንዶች በሶስተኛው ቀን ተያይዘው ጥልቀት ወዳለው የባህሩ ክፍል ያመራሉ። ስቲቨን ፍቅረኛው ሳታየው የታገቢኛለሽ ጥያቄውን ለማቅረብ ተዘጋጅቶ ነበር።
የውሃ ውስጥ መነጽሩን እንዳደረገም ስቲቨን ለፍቅረኛ የጋብቻ ጥያቄውን ማቅረብ ጀመረ።
በላስቲክ በተሸፈነ ወረቀትም እንዲህ ሲል ጽፎ ነበር፤ ''የምወድልሽን ነገሮች ሁሉ እንዳልነግርሽ ለረጅም ጊዜ ትንፋሼን መያዝ አልችልም፤ ነገር ግን ስላቺ የምወዳቸውን ነገሮች በሙሉ በእያንዳንዱ ቀን ይበልጥ እወድልሻለው።''
ቀጥሎም የጋብቻ ቀለበቱን ለፍቅረኛው አቅርቦ ነበር።
ስለ አሟሟቱ ዝርዝር መረጃ ባይሰጥም፤ ኬኔሻ አንቱዋን እንደገለጸችው ''ለጥያቄው ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ህይወቱ በማለፉ በጣሙን አዝኛለሁ'' ብላለች።

Sunday, September 22, 2019

ከ34 ዓመት በፊት በአውሮፕላን ጠለፋ የተጠረጠረው በቁጥጥር ስር ዋለ

https://zethiopians.blogspot.com/2019/09/blog-post_68.htm

የተጠለፈው አውሮፕላን

Image copyrightALAIN NOGUES/GETTY
እ.አ.አ. 1985 በአሜሪካ አየር መንገድ ንብረት በሆነ አውሮፕላን ላይ በተፈጸመው ጠለፋ እጁ አለበት የተባለው የ65 ዓመት ሊባኖሳዊ ግሪክ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።
ስሙ ያልተጠቀሰው ተጠርጣሪ ባሳለፍነው ሐሙስ ነበር ሚይኮኖስ በተባለ ደሴት በቁጥጥር ሥር የዋለው። ተጠርጣሪው በጉዞ ላይ በነበረበት ወቅት ፓስፖርቱ ሲታይ ጀርመን ውስጥ ተፈላጊ እንደሆነ ተደርሶበታል።

'ቲደብልዩኤ' የበረራ ቁጥር 487 የነበረው አውሮፕላን መሳሪያ ታጥቀው በነበሩ ሂዝቦላህ የተባለው ኢስላማዊ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ሆኖ ነበር። ምንም እንኳን ሂዝቦላህ ድርጊቱን አለመፈጸሙን ቢክድም።
ተጠርጣሪው እ.አ.አ. በ1987 ፈጽሞታል በተባለው የጠለፋና ሰዎችን በማገት ወንጀል ነበር በጀርመን ባለስልጣናት ይፈለግ የነበረው። በአሁኑ ሰዓት ተጠርጣሪው ከፍተኛ ጥበቃ በሚደረግለት የግሪክ ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛል።
ወንጀሉን ፈጽሟል ከተባለ ከሁለት ዓመታት በኋላ ጀርምን ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ የነበረ ሲሆን ቤሩት ውስጥ ታግተው የነበሩ ሁለት ጀርመናውያንን ለማስቀቅ ወደ ሊባኖስ በነጻ ተለቆ ነበር።
እ.አ.አ. በ1985 የትራንስ ወርልድ አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን ከካይሮ ተነስቶ በአቴንስ፣ ሮም፣ ቦስተን እና ሎስ አንጀለስ አድርጎ ወደ ሳንዲዬጎ በመብረር ላይ ሳለ ነበር ከአቴንስ ሲነሳ ጠላፊዎቹ አስገድደው ቤሩት እንዲያርፍ ያደረጉት።
153 የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎችና ሰራተኞች ለ17 ቀናት በቆየው አጋች ታጋች ድራማ በአውሮፕላኑ ውስጥ ቆይተዋል። ጠላፊዎቹም በእስራኤል ተይዘው የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሊባኖች ዜጎች ይፈቱልን በማለት ታጋቾቹን በማሰርና በመደብደብ በኋላ እንደሚገድሏቸው ሲያስፈራሩ ነበር።
በእስራኤል የሚገኙት ታሳሪዎች ሳይለቀቁ ሲቀር በአውሮፕላኑ ውስጥ ተሳፋሪ የነበረ አንድ የ23 ዓመት አሜሪካዊ የውሃ ጠላቂ ወታደር ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ሬሳውም ወደ ውጪ ተወርውሮ ነበር።
በመጨረሻ ግን ጠላፊዎቹ ታጋቾቹን ለቀዋል።
እንደ ኤፍቢአይ ከሆነ አውሮፕላኑን በመጥለፍ ወንጀል ውስጥ ቢያንስ አራት ሰዎች ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበራቸው።
እአአ 1986 ላይ የተለቀቀው እና 'ዘ ዴልታ ፎርስ' (The Delta Force) የሚል ስያሜ የተሰጠው ፊልም ይህን የአውሮፕላን ጠለፋ ላይ መሰረት ተድርጎ የተሰራ ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለያዩ ከተሞች ሰልፍ እያካሄዱ ነው



በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍImage copyrightAMMA
አጭር የምስል መግለጫበደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍ
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ሰልፍ እያካሄዱ ነው።
የተቃውሞ ሰልፍ እየተካሄደ ከሚገኝባቸው ስፍራዎች መካከል፤ የአማራ ክልል መዲና በሆነችው ባህርዳር፣ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ወልዲያ እና ምሥራቅ ጎጃም ደብረ ማርቆስ ይጠቀሳሉ።

የሰልፉ ተሳታፊዎች በቤተክርስቲያኗ፣ በኃይማኖት አባቶች እና በምዕመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ይቁም የሚል መልዕክት ይዘው ወጥተዋል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ እየተሰሙ ካሉ ድምጾች መካከል፤ ''በቤተ-ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸሙት ጥቃቶች ይቁሙ፣ ጥፋተኞች ለሕግ ይቅረቡ'' የሚሉ ይገኙበታል።
በወልዲያ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍImage copyrightAMMA
አጭር የምስል መግለጫበወልዲያ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍ
በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ ያለውን ሰልፍ ከሚያስተባበሩት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ በሪሁ ተስፋዬ "እጅግ በርካታ ሰዎች እየተሳተፉ የሚገኙበት ሰልፍ ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው" ብለዋል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ እየተሰሙ ካሉ መፈክሮች መካከል ''የቅዱስ ሲኖዶስ ድምጽ ይሰማ'' እና ''የቤተክርሰቲያን እና የኦሮቶዶክሶዊያን መገደል ይቁም'' የሚሉት ጎልተው እንደሚሰሙ አቶ በሪሁ ተናግረዋል።

የዛሬ ሳምንት ዕሁድ በተመሳሳይ መልኩ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደው ነበር።
በደሴ፣ ደብረ ታቦር እና ጎንደር ከተማ በተካሄዱት እና በሰላም በተጠናቀቁት ሰላማዊ ሰልፎችም ''በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቤተ-ክርስቲያን ያቀጠሉ እና ምዕመናንን የገደሉ ለፍርድ ይቅረቡ፣ መንግሥት ቤተ-ክርስቲያንን ሊያከብር ይገባል'' የሚሉ ተመሳሳይ የተቃውሞ ድምጾች ነበር የተሰሙት።

wanted officials