Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, April 13, 2019

BREAKING: Ethiopia arrests terror suspects with links to al-Shabaab




An Ethiopian official said the country’s intelligence and security agents have arrested suspects who were plotting to carry out terror attacks on public gatherings and other targets.
The country’s Attorney General, Berhanu Tsegaye told a gaggle of reporters in Addis Ababa that the National Intelligence and Security Services has successfully carried out arrests on suspected individuals.
The Attorney General did not say how many suspects were arrested in connection with the said planned terror attack on the country.
“The suspects have links to international terrorist networks. Photos, IDs, passports and other items that were in use in their preparation to carry out attacks were also seized,” Berhanu Tsegaye told reporters.
Asked to name the suspects’ international link, the Attorney General mentioned al-Shabaab as the main link to the suspects. He added that investigations were underway to find if the suspects have other international links.
The arrests were made in the last two weeks, according to the official.
“The investigations are not over yet. There are other suspects in the country and abroad who are yet to be arrested,” Tsegaye said.
A jihadist fundamentalist group based in Somalia, al-Shabaab was founded in 2006 and has claimed responsibility for several deadly attacks inside Somalia. It pledged allegiance to al-Qaeda in 2012 but some of its leaders had severed their relations with the terrorist group.
The United States has been increasing airstrikes against al-Shabaab after President Donald Trump authorized precision airstrikes against the group in March 2017.
Hundreds of al-Shabaab militants and some of its leaders have been killed in the last two years of airstrikes by the United States.

Tuesday, April 2, 2019

ኢትዮጵያ አንድ የመረጃ አገልግሎት የሚሰጥ ሳተላይት ልታመጥቅ ነው


ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ አንድ የመረጃ አገልግሎት የሚሰጥ ሳተላይት እንደምታመጥቅ ተገለጸ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ  ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት ሲያቀርቡ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ አንድ ሳተላይት ከሌላ ሀገር  ወደ ህዋ ለማምጠቅ ዝግጅት እያደረገች ትገኛለች።

የኮሚዩኒኬሽን ሳተላይት ወደ ህዋ የማምጠቅ ሙከራ ለማድረግ የሳተላይት ግብዓቶችን ከማሟላት ጀምሮ ፣ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን በመከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ለአገሪቱ የመጀመሪያው የሚሆነውን የመረጃ ሳተላይት ከሌላ ሀገር ለማምጠቅ የዝግጅት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሳተላይት የምታመጥቀው በአገር ውስጥ አለመሆኑ ቢገለጸም ሳተላይቱን ዲዛይን የማድረግና የመገንባት ሥራ ከሞላ ጎደል በኢትዮጵያውያን የተከናወነ ነው ተብሏል።
በርካታ የውጭ አገር ዩኒቨርስቲዎች የዕውቀት ሽግግሩን በከፍተኛ ደረጃ መደገፋቸውን፣ በአሁኑ ወቅትም ከሃምሳ በላይ ወጣት ኢትዮጵያውያን በህዋ ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ የብቃት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የመጀመሪያውን ሳተላይት ለማምጠቅ ከስምንት ሚሊዮን ዶላር ባላይ ወጪ መደረጉንም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመጪው ዓመት እስከ ህ   ዳር ወር ድረስ ይመጥቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ የመረጃ ሳተላይት፣ በዋናነት ለመሬት ምልከታ ሥራ ላይ እንደሚውል ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የሳተላይት ማምጠቅ ሥራው በስኬት ከተጠናቀቀ መንግሥት ለግብርና፣ ለውኃ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለማዕድን ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል የሚሆኑ መረጃዎችን በቀላሉ ከሳተላይቱ ማግኘት እንደሚያስችለውም ነው የገለጹት።
በራስ አቅም የተጀመረውን የህዋ ምርምርና ተጨማሪ ሳተላይት የመገንባት አቅም የበለጠ ለማጎልበት፣ የሳተላይት ግንባታ ፋብሪካ ለማቋቋም ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑን ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ገልጸዋል፡፡
ለሳተላይት ፋብሪካ ግንባታ ከሚደረገው ዝግጅት በተጨማሪ፣ የመገጣጠሚያና የፍተሻ ማዕከል ለመገንባትም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ተጨማሪ የሳተላይት መረጃ መቀበያ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ በማስፈለጉም፣ የግራውንድ ስቴሽን ግንባታ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ዶር ጌታሁን ጠቁመዋል፡፡
የዚህ ማዕከል ግንባታና የመሣሪያዎች ተከላ ተጠናቆ በመጪው ዓመት መጀመርያ ሥራ እንደሚጀምር፣ ይህም ከሳተላይ በሚደረግ የመሬት ምልከታ የሚሰበሰብ የመረጃ ፍላጎትን 50 በመቶ ይመልሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ መግለጻቸውን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

Monday, April 1, 2019

የ6 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት ቡድን ግብረ-ሃይል በማቋቋም እየሰራ መሆኑን ገለጸ


 የ6 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት ቡድን የፓርቲዎችን አባላት ውህደትና የአዲሱን አገር አቀፍ ፓርቲ ምስረታ ሂደት መርኃ-ግብር ለማውጣት ግብረ-ሃይል በማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡

ጥምረት የፈጠሩት ፓርቲዎቹ ኢዴፓ፣ ሰማያዊ፣ መኢአድ፣ የጋምቤላ ክልላዊ ንቅናቄ፣ አርበኞች ግንቦት 7ና የቀድሞ አንድነት ፓርቲ አመራርና አባላት ናቸው፡፡
ስድስቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህን የሚያሰፍንና ዜግነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ ፕሮግራም እንዲሁም የምርጫ ወረዳን መሰረት አድርጎ የሚዋቀር  አደረጃጀት ያለው ፓርቲ ለመመስረት ማቀዳቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
በዚህም መሰረት ፓርቲዎቹ የአባላት ውህደትና የአዲሱን ፓርቲ ምስረታ መርሃ-ግብር አውጥተዋል፡፡
ስልጠናና የፖሊሲ ሰነዶች የሚያዘጋጅ የምሁራን ስብስብ፣ የአባላትን መረጃ የሚያዘጋጅና የሚያዋህድ፣ የፋይናንስ ጉባኤ ዝግጅት እንዲሁም የህዝብ ግንኙነት ግብረ-ሃይል ማቋቋማቸውንም ጥምረቱ አስታውቋል፡፡
ፓርቲዎቹ ግንቦት 1 እና 2 አዲሱን የፖለቲካ ፓርቲ መስራች ጉባኤ ፣ የፓርቲውን ፕሮግራም፣ ስያሜና አርማ ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ቦይንግ ኩባንያ በ737 ማክስ አውሮፕላን ላይ የነበረውን “ኤምካስ” የተሰኘው የመቆጣጠሪያ ሲስተም በመቀየር ችግሩን ፈትቼዋለሁ ሲል ገለጸ


 (ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 19/2011) በአሜሪካ የሚገኘው አውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ ኩባንያ በ737 ማክስ አውሮፕላን ላይ የነበረውን “ኤምካስ” የተሰኘው የመቆጣጠሪያ ሲስተም በመቀየር ችግሩን ፈትቼዋለሁ ሲል ገለጸ።
እጅግ ዘመናዊ ከሚባሉት የቦይንግ 737 ማክስ ስሪቶች በኢትዮጵያና ኢንዶኔዥያ ተከስክሰው በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ካለቁ በኋላ ቦይንግ ከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል ።

ይሕም ሆኖ ግን እንዳይበሩ የተደረጉት የቦይንግ የማክስ ስሪቶች በቅርቡ ወደ ሥራ ለመመለስ እስካሁን የወሰነ ሀገር የለም ።
የኢንዶኒዥያው ላየን አየር መንገድ አውሮፕላን በተከሰከሰ በአምስተኛ ወሩ የኢትዯጵያ አየር መንገዱ አደጋ ሲደገም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ አየር መንገዶች የ737 ማክስ ስሪቶችን ላለማብረር ወስንዋል። ይህም በቦይንግ ላይ የቢሊዮን ዶላሮች ኪሳራን ማድረሱ ነው የተገለጸው።
እናም ቦይንግ ኩባንያ ዋናው የችግሩ ምንጭ እንደሆነ የሚጠረጠረውን “ኤምካስ” የተሰኘውን የመቆጣጠሪያ ሲስተም ቀይሬያለሁ ብሏል ።
ያም ሆኖ እንዳይበሩ የተደረጉት የብዙ ሃገራት የማክስ ስሪቶች በቅርቡ ወደ ሥራ ለመመለስ እስካሁን አልወሰኑም ።
ይህም የሆነው ቢያንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተከሰከሰበትን ምክንያት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የምርመራ ውጤት ስለሚጠበቅ ነው ተብሏል።
ኤምካስ የተባለውን ሲስተም አድሻለሁ የሚለው ቦይንግ አሁን አውሮፕላኖቹ ተመሳሳይ ችግር ውስጥ ቢገቡ ማስጠንቀቂያ የሚልክ ዘዴኝ የያዘ ነው። ይህ ዘዴ ቀደም ሲል እንደ አማራጭ የነበረ እንጂ አስገዳጅና መደበኛ ሲስተም ሆኖ ከቦይንግ የቀረበበት ሁኔታ ጨርሶ እንዳልነበረ የአቪየሽን ባለሞያዎች ይናገራሉ።
ይህ አሁን ተሻሽሎ ይገጠማል የሚባለው የቅድመ ጥንቃቄ ሰጪ ሲስተም በኢንዶኒዢያውም ኾነ በኢትዯጵያው አየር መንገድ ላይ ያልነበረ ነው ተብሏል። ቦይንግ እንደገለጸው ይህ ሲስተም መገጠሙ አውሮፕላኑ የሚቃረኑ ምልክቶችን ሲሰጥ ለፓይለቶቹ ጥቆማን ይሰጣል።
ቦይንግ ለደንበኞቹ ይህን ሲስተም የምገጥምላችሁ በነጻ ነው፤ አንዳችም ክፍያ አልጠይቃችሁም ብሏል።
ቀደም ሲል የነበረው ሴንሰር ግን የኢንዶኒዢያው  አውሮፕላን ምርመራ ውጤት እንዳመላከተው  አውሮፕላኑ በአፍጢሙ እንዲደፋ የሚያደርግበት ሁኔታ አለ። ይህም የሚሆነው ሚዛኑን ለመጠበቅ የሚልከው መልዕክት (ሲግናል) እርስበርሱ የሚጣረስ እንደሆነ ነው የተገለጸው።
ይህም ከአብራሪዎቹ ቁጥጥር ውጭ የሚሆን ነገር ነው ተብሏል። የተከሰከሰው የኢንዶኔዢያ አየር መንገድ ከ20 ጊዜ በላይ የአውሮፕላኑ አፍንጫ ቁልቁል እንዲያዘምና እንዲምዘገዘግ አድርጎታል ።
አሁን ቦይንግ አድሼዋለሁ የሚለው ሶፍትዌር በአውሮፕላኑ አፍንጫ የምትገኘው ሴንሰር እርስ በርሱ የሚጣረስ መልዕክት ካስተላለፈ ኤምካስ የተሰኘውን መቆጣጠሪያ ልክ እንደ ኤሌክትሪክ ባልቦላ ራሱን በራሱ እንዲያጠፋ የሚያደርግ ነው ተብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከእስክንድር ነጋ ጋር ለመወያየት እንደሚፈልጉ ገለጹ


 ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከጋዜጠኛና የሰብአዊ መብት ታጋዩ እስክንድር ነጋ ጋር ለመወያየት እንደሚፈልጉ አስታወቁ።
ዶክተር አብይ አህመድ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን አስመልክቶ ከ40 በላይ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን፥ምሁራን እንዲሁም ታዋቂ ሰዎች በጽሁፍ ላቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

እስክንድር ነጋን በተመለከተ በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን፣ ሰብአዊ መብትም እንዲከበር ያደረገውን አስተዋጽኦ እኔም የማደንቀው ነው ብለዋል።
ባነሣቸው ሐሳቦች ምክንያት በመንግሥት በኩል በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ ምንም ዓይነት ጫናና ችግር አይደርስበትም ሲሉም ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምሁራኑና ታዋቂ ሰዎች በጻፉት ደብዳቤ ለሀገራችሁና ለሕዝባችሁ በመቆርቆር፣ ሀገራችሁም የተሻለችና የሠለጠነች እንድትሆን በማሰብ የጻፋችሁትን መልእክት እንደ እናንተ ካሉ በሳል ዜጎች የሚጠበቅ ነው ብለኣውል፡፡በዚሁም መሰረት  ችግሮችን በጨዋነት በመመካከርና የተሻለ የመፍትሔ ሐሳብ በማቅረብ መፍታት እንደሚገባ የእናንተ ተግባር አርአያነት ያልው ነው ሲሉ በምላሻቸው ገልጸዋል፡፡
በሀገራችን የተፈናቀሉ ዜጎችን በተመለከተ ያነሣችሁት ሐሳብ ሁላችንም የምንጋራው ነውም ሲሉ ነው የገለጹት፡፡ እናም በሕዝባችን የተጀመረውን የለውጥ ተስፋ ለማጨለም በሚሠሩ አካላት፣ በሌላ በኩል ደግሞ በቢሮክራሲው ውስጥ ያሉ ኃላፊዎች ችግሮችን በእንጭጭነታቸው ለመፍታት ባለመረባረባቸው የተነሣ የዜጎቻችን መፈናቀል መከሠቱ እኛንም ያሳዝነናል ብለዋል፡፡ይሕንኑም ችግር ለመፍታትና ተፈናቃዮችን ልመመለስ እየተረባረብን ነው ሲሉ ነው የገለጹት። እንደ ታማኝ በየነ ያሉ የወገኖቻቸው ሁኔታ የሚያሳስባቸው ዜጎች ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን ሲወጡ እያየን በመሆኑ ችግሮቻችን እድሜያቸው እንደሚያጥር ርግጠኞች ሆነናል ሲሉም ገልጸዋል።
እስክንድር ነጋን በተመለከተ በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን፣ ሰብአዊ መብትም እንዲከበር ያደረገውን አስተዋጽዖ እኔም የማደንቀው ነው፡፡ ለዚህ ተጋድሎውም ተገቢው አክብሮት አለኝ፥ ያነሣቸውን አንዳንድ ሐሳቦች በተመለከተ ግን መፍትሔው ውይይት ነው ብለዋል፡፡ በቅርቡም ባነሣቸው ጉዳዮች ላይ እንደምንወያይ ተስፋ አደርጋለሁ ሲሉም ነው የገለጹት።
ባነሣቸው ሐሳቦች ምክንያት በመንግሥት በኩል የሚደርስበት ምን ዓይነት ጫናና ችግር አይኖርም ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡
ረዥሙን የለውጥ ጉዞ ጀመርን እንጂ አልጨረስነውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ካሳለፍነው ይልቅ ከፊታችን ያለው ረዥም ነው ነው ብለኣዋል፡፡ እንዲህ እንደናንተ ያገባናል የሚሉ ዜጎች በሰከነ መንገድ ለሀገራቸው የሚችሉትን ሁሉ ሲያበረክቱ ነገ ከትናንት የተሻለ ይሆናል ሲሉም ደብዳቤውን ለጻፉላቸው ምሁራን ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል ፡፡

በአፋር ክልል ከ3 ሺ እስከ 5ሺ በሚሆኑ ታጣቂዎች ጥቃት ተፈጸመ


በአፋር ክልል ከ3 ሺ እስከ 5ሺ በሚሆኑ ታጣቂዎች ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ።
የአፋር የሰብአዊ መብቶች ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ጋአስ አህመድ በክልሉ በተፈጸመው ጥቃት አንድ መንድር በእሳት መቃጠሉን ተናግረዋል።

ግዛትን የማስፋፋት ጥቃት ነው እየደረሰ ያለው የሚሉት አቶ ጋአስ ጥቃቱ በሶማሌ ላንድ፣በጅቡቲና በአልሻባብ ታጣቂ ሃይሎች እየተፈጸመ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ክልሉ እየደረሰበት ያለውን ጥቃት ለፌደራል መንግስቱ በተደጋጋሚ ቢያሳውቅም ምንም ያገኘው ምላሽ አለመኖሩን ነው ለኢሳት የገለጹት።
በአፋር ክልል የተከፈተው ጦርነት 3 ወራትን አስቆጥሯል ይላሉ አቶ ጋአስ አህመስ የአፋር የሰብአዊ መብቶች ድርጅት ሊቀመንበር።
ከዚህ በፊት ይካሄዱ የነበሩ ጥቃቶች ከግጦች፣ከውሃና ከሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ጋር እንደነበርም ይናገራሉ።
የአሁኑ ወረራ ግን ከዛ የተለየና ጥቃቱን የፈጸመውም አካል ቢሆን በቁጥር ከፍተኛ  ነው ብለዋል አቶ ጋአስ አህመድ ከኢሳት ጋር በነበራቸው ቆይታ። -ከ3ሺ እስከ 5ሺ በሚደርስ ታጣቂ ጥቃቱ መፈጸሙን በመግለጽ
በጥቃቱ የሶማሌ ላንድና የኢትዮጵያን ታርጋ የለጠፉ ተሽከርካሪዎች መሳተፋቸውን ነው የሚናገሩት።
እንደ አቶ ጋአስ አባባል ከሆነ ጥቃቱ ዛሬም ቀጥሏል።–በአካባቢ አንድ መንደር በእሳት መጋየቱን በመጠቆም

በአፋር ህዝብ ላይ የተከፈተው ጦርነት ኣንዲህ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ይላሉ።ጥቃቱ በጅቡቲ፣በሶማሌ ላንድና በአልሻባብ የተደረገ ጥቃት መሆኑንም ገልጸዋል።
እንደ እሳቸው አባባል አካባቢው ሰፊ ከመሆኑና የኮንትሮባንድ ንግድ የሚካሄድበት ከመሆኑም ጋር ተያይዞ የመከላከያ ሃይሉ ሁሉንም አካባቢ ለመከላከል አቅሙ የለውም።
ጥቃቱን ሊፈጽም የሚመጣው አካል የሚታጠቀው መሳሪያ ከባድ በመሆኑም የመከላከያ ሃይሉ ሊያስቆመው የሚችል አይደለም ይላሉ።
እስካሁን በተፈጸመው ጥቃትም ከ100 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችና አርብቶ አደርጎ ህይወታቸውን አተዋል፣በቁጥር መገመት የማይቻል ንብረት ወድሟል ብለዋል።
የክልሉ መንግስት ያለውን ሁኔታ ሁሉ ለፌደራል መንግስቱ  ቢያሳውቅም የተሰጠው ምላሽ ግን እንደሌለ ነው የተናገሩት።

Freedom House calls Ethiopia ‘not free’ but says country shows improvement in press freedom, political rights



By Engidu Woldie
ESAT News (February 8, 2019)
The annual report on freedom in the world by Freedom House says Ethiopia has made some improvements in the areas of press freedom and eased restrictions on opposition political parties. The report however said the country still remains not free as it “remains beset by political factionalism and intercommunal violence, abuses by security forces and violations of due process are still common, and many restrictive laws remain in force.”
The country scored 19 out of 100. Its freedom, political rights and civil liberties was scored 6/7, 1 being most free and 7 least free.
The Freedom House report recognized that environment for the media improved significantly during 2018. It also recalled that journalists were freed and critical media like the Ethiopian Satellite Television and Radio (ESAT) were allowed to operate in the country.
“Since Prime Minister Abiy took office in April, the government has eased restrictions on independent media, permitting both greater freedom for journalists and a more diverse range of news for consumers,” the Freedom House report said.
The report also recognizes that the country has made positive improvements in allowing political parties to operate more freely. “Abiy’s administration has pledged reforms that will ease the legal and practical requirements for opposition parties to operate, though substantial changes are necessary before political parties can carry out activities freely… the government took a number of steps that allowed political groupings greater freedom to operate.”
“Prime Minister Abiy’s reforms allow opposition groupings to operate more openly in advance of 2020 elections.”
The report however noted that the government and none of its officials and the people’s representatives at the parliament were elected through free and fair elections. It also said key governance institutions continued to be dominated by the EPRDF. For this and other reasons, the report said, Ethiopia remains ‘not free.’

wanted officials