Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, October 31, 2016

Donald Trump grabs the Ethiopian model P ኢትዮጵያዊቷ ሞዴል ሕይወት በቀለ ዶናልድ ትራምፕን እናግሬው ነበር በጓደኛዬም ይታማል ነበር አለች

ኢትዮጵያዊቷ ሞዴል ሕይወት በቀለ ዶናልድ ትራምፕን እናግሬው ነበር በጓደኛዬም ይታማ ነበር አለች


ኢትዮጵያዊቷ ሞዴል ሕይወት በቀለ ዶናልድ ትራምፕን እናግሬው ነበር በጓደኛዬም ይታማል ነበር አለች

የፍራንክፈርት ከተማና የአካባቢያዋ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ወደ 15 ሺ ይሮ የተጠጋ እርዳታ አሰባሰቡ !



የፍራንክፈርት ከተማና የአካባቢያዋ ኗሪ ኢትዮጵያውያን ወደ 15 ሺ ኤዉሮ የተጠጋ እርዳታ አሰባሰቡ ! በፍራንክፈርትና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለፈዉ ቅዳሜ ኦክቶበር 29 ቀን ባደረጉት ስብሰባ በሕዝባዊ እምቢተኝነቱ አመጽ ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰባቸዉ የቤተሰብ አባላት ወደ 15 ሺ ኤዉሮ የሚጠጋ ገንዘብ ማሰባሰብ መቻላቸዉን አንድ የእርዳታ አሰባሰቢው ግብረ ሃይል ቃል አቀባይ አስታውቑል። በጀርመን የትብብርና ውይይት መድረክ ማዕከልነት በፍራንክፈርት ከተማና አካባቢዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የእርዳታ አሰባሳቢ ልዩ ግብረ ሃይል በመፍጠር ባጭር ጊዜ ውስጥ በተደረገ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን ርብርቦሽ በዚህ ዜና ርዕስ ላይ የተጠቀሰዉ የገንዘብ መጠን ሊገኝ ችሏል።

ይህም ገቢ ሊገኝ የቻለዉ፣ በዋናነት ከመግቢያ ቲኬት፣ ከቶምቦላ፣ከጨረታ ዉድድር እንደሆነ በተጨማሪ ተገልጿል። በተለይ በጨረታዉ ዉድድር፣ የአንዳርጋቸዉ ፅጌ፣ የመምሕር በቀለ ገርባ እና የኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱ ፎቶዎች መቅረብ መቻላቸዉ የብዙዎቹን የስብሰባዉን ታዳሚዎች ቀልብ የሳበ ሲሆን፣ ከፍተኛ ውድድር የታየበትና የማይናቅ የገቢ መጠንምአስገኝቷል። በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመዉ ግፍና ሰቆቃ አንድ ሊያደርገን ካልቻለ ምንጊዜም አንድ ያለ መሆን አባዜ ሊጫወትብን ይችላልና ይህን የፈተና ጊዜ አንድ ሆነን ማሳለፍና ችግሩንም ባጋራ መቑቑም እንዳለብን በመድረኩ በግልፅ ተንፀባርቑል። በተለይም በአሁኑ ሰዓት በሃገሪቱ በሁሉም ማዕዘናት ለነፃነቱና ለመብቱ ደሙን እያፈሰሰ ከሚገኘዉ ወገናችን ጎን መቆም ለነገ የማይባል የዛሬ ተግባራችን መሆን እንደሚገባዉ በስብሰባዉ ታዳሚዎች በትኩረት ተወስቷል። ደሙ በየመንገዱ እየተዘራ ሕይወቱ ለሚያልፈዉ ቀሪ ቤተሰብ የአቅምን እርዳታ መለገስ ሰብዓዊነት እንጂ ከፖለቲካ ጋር የሚያቆራኘዉ አመክንዮም ሰለሌለ፣ ለወደፊቱም ይህ ዓይነቱ ተግባር በተከታታይ መቀጠል እንዳለበት ተሰምሮበታል። ትግል ሳይቸግረዉ፣ ድል ያልሰመረለት ይህ የተካደ ትውልድ ሕልሙና ራዕዩ እዉን እስኪሆን ድረስ ሁሉም በዚህ ታሪካዊና የፈተና ጊዜ ዚግነታዊ አሻራዉን ጥሎ እንዲያልፍ እናት ሀገሩ ጥሪ አያደረገችለት መሆኑን ሊገነዘበዉ እንደሚገባ፣ የስብሰባዉ ታዳሚዎች በቃላት ሳይሆን በዓይን ተናበዋል። በፕሮግራሙ ላይ አጫጭር ግጥሞችም ቀርበዉ በንባብ ተደምጠዋል። እንደ ጴጥሮስ ያችን ሰዓት የመሳሰሉ ምንጊዜም ሀገራዊ መልዕክታቸዉን ጊዜ ያማይሽረዉ ቲያትር ለስብሰባዉ ከጊዜ አንፃር ተቀነባብሮ አሰልቺ ባልሆነና ትምሕርት ሊሰጥ በሚችል መልኩ ቀርቦም ታይቷል። በተለይ በፕሮገራሙ መጨረሻ ላይ መድረኩ ለግልጽ ውይይት ክፍት ሆኖ፣ መነቃቀፍ ከሌለ መተማመን ስለማይኖር፣ እየተነጋገርን በመተባበርና በመተማመን ስንሞት እሬሳችን እየተላከ የምንቀበርባት ሀገር ሳትሆን በሕይወታችንም በቁም የምንኖርባት ኢትዮጵያ እንድትፈጠር የየድርሻችንን አገራዊ ዕዳ መክፈል እንደሚኖርብንና ማንነቱን ለማስከበር ደሙን እየገበረ ከሚገኘዉ ወገናችን ጎን ለመቆም የዛሬ እንጂ የነገ ቀጠሮ ያማያስፈልገዉ የቤት ሥራችን መሆን እንዳለበት በተማመን ተለያይቷል።

ሰበር ዜና:-አፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ደህንነት ህወሃት ላይ ቅሬታዉን እያሰማ ይገኛል !



ልሁል አለም
ያሳለፍነዉ እሮብ ነበር የሶማሌያዉ አል ሸባብ በደቡብ ሶማሌያ የምትገኘዉን ቲየግሎው Tiyeeglow የተባለችዉን ከተማ መቆጣጠሩን ይፋ ያደረገዉ ባኮንና ሂራን የተባሉ ቅርብ የሆኑ ቁልፍ ክልሎችን ለማጥቃት የሚመቸዉ ሲሆን ይህን አል ሸባብ ሄልጋን የሚገኘዉን የአሚሶም ወታደራዊ ጣቢያን በመቆጣጠር የበላይነቱን ተቆጣጥሯል።
የአፍሪካ ህብረቱ ሰራዊት ከፍተኛ መሰዋትነት ከፍለዉ ሞተዉና ቆስለዉ ያስከበሩትን የጦር ቀጠናዎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሆን ብሎ ለአልሸባብ አስረክቦ ሊወጣ የቻለበት ምክንያት እንዲጣራ የሲ አይ ኤ መረጃዎች ለህብረቱ ወታደራዊ መኮንኖች መተላለፉን ዛሬ ከህወሃት ወታደራዊ ደህንነት ምንጮች ለማወቅ ተችሏል።
የአልሸባብ የወታደራዊ ድርጊቶች አፈ ቀላጤ አብዲአሲስ አቡ ሙሳብ ” የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊቶች የጦር ቀጠናዎቹን ለቀዉ እንደወጡ በእግራቸዉ ተክተናል በማለት ያረጋገጠ ሲሆን አብዱአሲስ አያይዞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አል_ኢሊ ከተማን በጥር 11 ሄልጋንን ደግሞ በጥር 23 የለቀቀ ሲሆን በተለይ የመከላከያ ሰራዊቱ ሄልጋንን ለመልቀቅ ባኮበኮቡበት ሁኔታ ላይ ደርሰን በከፈትነዉ ተኩስ መጠነኛ ጉዳት አድርሰናል ”
በማለት የገለጸ ሲሆን ከአብዱአሲስ ፍንጭ እና ከሌሎች በተሰበሰበ ማስረጃ ምክንያት በአልሸባብና በህወሃት መካከል የመረጃ ልዉዉጥ መኖሩን አመላክቷል በማለት የደመደሙት የህብረቱ መኮንኖች ለህወሃት የሐይል ቡድን አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
የህብረቱ ከፍተኛ መኮንኖች በቅርቡ በአዲስ አበባ ላይ በሚደረገዉ የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ ህወሃት ቡድን ማብራሪያ እንዲሰጥ ለማድረግ እየጣሩ ይገኛሉ
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
weyane-leba
    


በቂሊንጦ ማ/ቤት በደረሰው እሳት ቃጠሎ ወቅት 67 ሰዎች ተገድለዋል/ሞተዋል፡፡



(የኢሰመፕ ለልዩ ዘገባ)
በኢትዮጵያ የፌደራሉ መንግስት ከሚያስተዳድራቸው ቃሊቲ፣ ዝዋይና ሸዋሮቢት ማረሚያ ቤቶች በተጨማሪ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙ እስረኞችን የያዘው ‹የቂሊንጦ ጊዜ ቀጠሮ ማረፊያ ቤት አስተዳደር› በርካታ ተጠርጣሪዎች (እስረኞች) የሚገኙበት እስር ቤት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ እስር ቤት 3000 ገደማ እስረኞች የሚገኙ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ግማሽ ያህሉ በሽብር የተከሰሱና ሌሎች የፖለቲካ እስረኛ ናቸው፡፡
ቂሊንጦ እስር ቤት የኦፌኮ ም/ፕሬዚዳንት አቶ በቀለ ገርባ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የቀድሞው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ፣ ጋዜጠኞቹ ካሊድ መሃመድ፣ ጌታቸው ሺፈራውና ዳርሰማ ሶሪ እንዲሁም ሌሎች በርካታ የፖለቲካ አመራሮችና አክቲቪስቶች ታስረው የሚገኙበት ነው፡፡
fire_qlinto
ይህ እስር ቤት በያዝነው አዲስ አመት ዋዜማ (ነሀሴ 2008) ላይ የእሳት ቃጠሎ ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ በዚህ ቃጠሎ የተነሳ በወቅቱ የተጎዱ ሰዎች ማንነትና መጠን በታሰበው ፍጥነት ቶሎ ሳይገለጽ ቢቆይም የኋላ ኋላ መንግስት በቃጠሎው ወቅት በእሳት ተቃጥለውና ‹ለማምለጥ ሲሞክሩ የተገደሉ› በሚል 23 ሰዎች መሞታቸውን ገልጾ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት ባደረገው ማጣራት በወቅቱ ከተፈጠረው እሳት ቃጠሎ ጋር በተያያዘ በአጠቃላይ 67 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ከእነዚህ ሟቾች ውስጥ በቃጠሎ የሞቱት 22 ሰዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 45 ሰዎች ‹‹ሊያመልጡ ሞክረዋል›› በሚል በመንግስት ታጣቂዎች (የማ/ቤቱ ጠባቂዎች) የተገደሉ ናቸው፡፡
በወቅቱ ህይወታቸውን ካጡ ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው፣ በጭስ ታፍነው የጤና መታወክ የገጠማቸው በርካቶች ናቸው፡፡ ለአብነትም በእነ ከድር መሃመድ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦበት በጊዜ ቀጠሮ ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳርሰማ ሶሪ የመተንፈሻ አካሉ ላይ በገጠመው የጤና መታወክ ህክምና ላይ ይገኛል፡፡
ከቃጠሎው ማግስት
በቂሊንጦ የደረሰውን ቃጠሎ ተከትሎ የእስረኛ ቤተሰብ፣ ዘመድና ጓደኞች ለቀናት የጭንቅ ቀናትን አሳልፈዋል፤ እያሳለፉም ነው፡፡ በወቅቱ በደረሰው ቃጠሎ ወቅት የእስረኞችን በህይወት መኖርና አለመኖር ማረጋገጥ አዳጋች ሆኖ፣ ያለምንም መረጃ ቤተሰብ በየዕለቱ ወደቂሊንጦ ሲንከራተቱ ቆይተዋል፡፡ ይህን በማድረጋቸውም ጭንቅ ላይ የሚገኙ የእስረኛ ቤተሰቦች ላይ ‹ለምን ትጠይቃላችሁ› በሚል ድብደባና እስር ደርሶባቸዋል፡፡
መንግስት በወቅቱ በቂሊንጦ የነበሩ (በህይወት የተረፉትን) እስረኞችን ወደተለያዩ እስር ቤቶች ለማዘዋወር ተገድዷል፡፡ ይህንንም ዘግይቶም ቢሆን ለእስረኛ ቤተሰቦች አሳውቋል፡፡ ሆኖም የእስረኛ ቤተሰቦች ከቃጠሎው ወዲህ የሚደርስባቸው እንግልት አልቆመም፡፡ ከዚህ የከፋው እንግልትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ ያለው ግን በእስረኞች ላይ ነው፡፡
ወደ ዝዋይና ሸዋሮቢት እንዲዘዋወሩ የተደረጉት እስረኞች የተለያዩ የሰብዓዊ ክብርን የሚያዋርድ ተግባር እንደተፈጸመባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዝዋይ የተዘዋወሩት እስረኞች ለአስር ቀናት ያህል ካቴና ከእጃቸው ሳይፈታ በእስር አሳልፈዋል፡፡ እነዚህ እስረኞች ሁለት፣ ሁለት ሆነው በአንድ ካቴና ታስረው መጸዳጃ ቤት ሲሄዱም፣ ሲመገቡና ሲተኙ ሳይቀር በእስር አንድ ላይ ሆነው እንደነበር ተረጋግጧል፡፡
እስረኞቹ ከምግብ ሌላ ማናቸውም ነገሮች እንዳይገቡላቸው ተከልክለው፣ ጠያቂዎቻቸውን ከ3 ደቂቃ በላይ እንዳያነጋግሩ ተደርገው ሰንብተዋል፡፡ በተለይም እየደረሰ ያለውን ግፍ በተመለከተ የተናገረ ሰው አሸዋ ላይ ራቁቱን ሆኖ ግርፋት ይፈጸምበት ነበር፡፡ አሸዋ ላይ የሚገረፈው እስረኛ ውሃ እየተደፋበት ሰውነቱ አሸዋውን እንዲይዘው ተደርጎ፣ ከዚያም ሰውነቱን እንዳይታጠብ ተገድቦ በስቃይ እንዲቆይ ይደረጋል፡፡ በጠባብ ክፍል ውስጥ በርካታ እስረኞችን በማጨቅ ሰው በሰው ላይ ተደራርቦ እንዲተኛ ተገድዶ ነበር (በተለይ ዝዋይ)፡፡
ሸዋሮቢት የተዘዋወሩትም ቢሆን ተመሳሳይ በደል እንደተፈጸመባቸው ነው ማረጋገጥ የተቻለው፡፡ በዚሁ እስር ቤት የቆይ እስረኞች አንዳንዶቹ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ከመፈጸሙ ጋር በተያያዘ ቤተሰብ ሊጠይቃቸው በሄደ ወቅት አንድ ክፍል ውስጥ አስቀምጠው በመስኮት ከወገብ በላይ ብቻ እየታዩ ‹አለሁ› እንዲሉ መገደዳቸውን ከቤተሰቦቻቸው ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
የእስረኞቹ ወደቂሊንጦ መመለስ
ጥቅምት 2009 ዓ.ም መግቢያ ጀምሮ ወደተለያዩ እስር ቤቶች ተበትነው የነበሩ ተጠርጣሪዎች ወደ ቂሊንጦ መመለስ ጀምረዋል፡፡ ሆኖም ግን የቂሊንጦ ማ/ቤት አስተዳደር እስረኞችን ፍ/ቤት እያቀረበ አይደለም፡፡ ይህ ሪፖርት እስከተዘጋጀበት ዕለት ድረስ እስረኞች በፍ/ቤት ቀጠሯቸው መሰረት ፍ/ቤት ሊያቀርቧቸው አልቻሉም፡፡ ለምሳሌ ጥቅምት 9/2009 ዓ.ም ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል ችሎት ቀጠሮ የነበራቸው እነ ከድር መሃመድ (20 ሰዎች) እና እነ ትንሳኤ በሪሶ (10) ሰዎች ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ተረጋግጧል፡፡
ጥቅምት 14/2009 ዓ.ም ቀጠሮ የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬም በተመሳሳይ በቀጠሮው ዕለት ፍ/ቤት አልቀረበም፡፡ ለዚህም ከማ/ቤቱ አስተዳደር ተጠርጣረውን ላለማቅረቡ በቂ ምክንያት ለፍርድ ቤቱ አላቀረበም፡፡
አሁን ላይ ወደ ቂሊንጦ የተመለሱት ታሳሪዎች በአንጻራዊነት የተሻለ ሁኔታ ላይ ናቸው ለማለት ቢቻልም አሁንም ግን የመጠየቂያ ሰዓት ገደብ አለባቸው፡፡ ቢበዛ ለ10 ደቂቃ ብቻ ነው ቤተሰቦቻቸውን እንዲያነጋግሩ የሚፈቀድላቸው፡፡ ከምግብ ሌላ ማናቸውም ነገር እንዲገባላቸው አይፈቀድም፡፡ የጥርስ ሳሙናና ቡርሽ፣ ቫዝሊን፣ በሶ እና የመሳሰሉት አስፈላጊ ነገሮች እንኳ አይገቡላቸውም፡፡
መንግስት እስረኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ ስለመሆኑ
የኢትዮጵያ መንግስት በቂሊንጦ ለደረሰው አደጋ እስረኞችን ተጠያቂ በማድረግ ክስ ሊመሰርት መሆኑ ታውቋል፡፡ መንግስት በቁጥር የበዙ እስረኞችን በተጠርጣሪነት ይዞ ምርምመራ በማድረግ ላይ እንደሆነና ምስክሮችንም እያዘጋጀ እንዳለ የታወቀ ሲሆን፣ ተጠርጣሪዎቹ በቂሊንጦ ለደረሰው አደጋና ይህንንም ተከትሎ ለጠፋው የሰው ህይወትና ንብረት ተጠያቂ ናችሁ ሊባሉ እንደሚችሉ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ መንግስት ይህን እያደረገ የሚገኘው የደረሰው ቃጠሎ መንስኤና ቃጠሎውን ተከትሎ የደረሰው ጉዳት በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ባልተገለጸበት ሁኔታ ነው፡፡ መንግስታዊው “የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን” ማጣራት አደርጋለሁ ማለቱና በሚቀጥለው ሳምንት ለፓርላማ ሪፓርት አቀርባለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡
(በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት ተዘጋጀ)

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ንግግር በትግራይ ነጻ አውጪው መከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ መናጋገሪያ ሆኗል


Birhanu
ከናትናኤል ኃይለማርያም
የአርበኞች ግንቦት ሰባትሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ለመከላከያ ሰራዊት አባላት፣የፌደራለ እና የክልል ፖሊስ አባላት፤ለአጋዚ ልዩ ጦር አባላት እና ለሌሎች ስርአቱ ታጣቂዎች ያደረጉት ጥሪ በሰራዊቱ ዉስጥ ከፍተኛ መነጋገሪያ ከመሆኑም በተጨማሪ ሰራዊቱ ከህዝብ ጋር ለመቆም የመጨረሻ ዉሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገዉ ጥሪ ነዉ ሲሉ እነዚሁ ምንጮች ጠቅሰዋል።የተደረገዉን ጥሪ መቀበላቸዉን ለማመላከት ሀሳባቸዉን የገለጹት የሰራዊቱ አባላት እንዳሉት “ መከላከያዉ የህዝብ ሳይሆን የህዉሀት ቡድን አገልጋይ እየሆነ መምጣቱን ሙሉ በሙሉ ያወቁበት ደረጃ ላይ መድረሳቸዉን እና ሊቀመንበሩ እንዳሉት ሰራዊቱ የቁም እስረኛ ሲሆን በተለይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከተጀመረ ጀምሮ ምን እንደሚያደርግ እና ወዴት እንደሚሄድ የጠራ አቅጣጫ ባለማግኘቱ እና ባለበት ከፍተኛ ጫና የተነሳ አማራጭ በማጣት በሰራዊቱ ዉስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አክለዉም በአሁኑ ሰአት አዛዦቻቸዉ ድንጋጤ ዉስጥ ከመሆናቸዉ የተነሳ በሰራዊቱ ላይ ያለዉ ቁጥጥር እና ማስጠንቀቂያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን እንዲሁም ከአንድ ብሄር የሆኑ አባላት ባንድ ላይ ለግዳጅም ሆነ ለስምሪት እንደማይመደቡና በግል ህይወታቸዉ ዉስጥ ስለላን እያካሄዱ ነጻነታቸዉን ፍጹም እንደነጠቋቸዉም ገልጸዋል፡፤በዚህም ምክንያት ከሰራዊቱ መካከል ያሉ አንዳንድ አድር ባይ አባላትን ሳይቀር የሕዉሐት ገደብ ያለፈ ጥርጥር ወደተቃዋሚነት ስለለወጣቸዉ በአሁኑ ሰአት በጥቂት ቁጥር ከሚቆጠሩ የግል ሰዎቻቸዉ በቀር ሰራዊቱ ልቡ ከህዝብ ጎን ሆኗል ብለዋል፡፤ በየጊዜዉ ለግዳጅ ሲወጡ ወደነጻነት ታጋዮች ከነትጥቃቸዉ የሚቀላቀሉ እና በቡድን በመደራጀት በየጫካዉ የሚመሸጉ የሰራዊት አባላት ቁጥር ከቀን ወደቀን እየጨመረ መምጣቱንም አመልክተዋል።
ፕሮፈሰር ብርሀኑ ነጋ ለሰራዊቱ ያደረጉትን ጥሪ በርካታ ሰዎች ለዉጥ የሚያመጣ ጥሪ መሆኑን በመግለጽ እነሱን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ መከላከያ ሰራዊቱ ወገኑ ላይ መተኮስ እንዲያቆም እና የመሳሪያ ነጠቃን እና በ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሰበብ የሚደረግባቸዉን የጅምላ አፈሳ እንዲሁም ግድያ በመቃወም ወደጫካ ከገቡ ወጣቶች እና አርሶ አደሮች እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዉ፤ ከሳምንታት በፊት በፍኖተ ሰላም ከተማ 18 የመከላከያ ሰራዊቶች እና አራት ያጋዚ አባላት ሰራዊቱን ከድተዉ መዉጣታቸዉን አስታዉሰዋል።በተለይ በአማራ ክልል አገዛዙ በስፋት ለማከናወን አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ያለበትን የመሳሪያ ነጠቃ ሽሽት ወደየጫካዎች በመግባት ላይ ያለዉ ህብረተሰብ እየጨመረ መምጣቱን እና የኮማንድ ፖስት አባላት ወጣቶችን ያለምንም ምክንያት ስለሚያስሩዋቸዉ በፍኖተ ሰላም በከተማዋ ዉስጥ አዛዉንቶች፤ሴቶች እና ህጻናት ብቻ እየቀሩ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተያያዘ ዜናም በባህር ዳር ከተማ ከስድስት ሳምንት በፊት ወቶ የነበረዉና መመዘኛዉ ከ10ኛ ክፍል በላይ የነበረዉ የመከላከያ ምዝገባ ፤ተመዝጋቢ በማጣቱ ምክንያት ማስታወቂያዉ ከወጣ ከሁለት ሳምንት በሗላ መስፈርቱ ወደ 6ተኛ ክፍል ዝቅ ብሎም ባለመሳካቱ በአሁኑ ሰአት ወጣቶች ወደ መከላከያ ቢገቡ ጥቅማጥቅሞችን እንደሚያገኙ ዉስጥ ዉስጡን በቅስቀሳ መልክ እየተወራ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ይህ በእንዲ እንዳለ የክልሉ አየር መንገድ ለአዉሮፕላን አብራሪነት እና ለቴክኒሺያንነት የቅጥር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ምናልባት በስራ አጥነት ሲሰቃይ የከረመዉን ወጣት በዚ መልክ በመመዝገብ ወደመከላከያ ስለጠና ሊወስዱት ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸዉም ጠቁመዋል። የህዋት መንግስት ለመከላከያ እና ለፖሊስ አባላት መላቀቂያም ሆነ ፈቃድ መጠየቅ እንደማይቻል ቢያስተላልፍም እየከዱ እና እየጠፉ በሚለቁ አባላት ምክንያት አለመተማመን የመጣዉን የሰራዊቱን ቁጥር ለመጨመር በሰበብ አስባቡ በቁጥጥር ስር ያዋላቸዉን ወጣቶች በማባባል እና በማስገደድ ወደ ስልጠና ለማስገባት ሙከራ እያረገ ይገኛል ሲሉም ተደማጠዋል።
ከአመት በፊት ጀምሮ ሰራዊቱን እየለቀቁ የሚሄዱ አባላት ቁጥር በተለይ ህዝባዊ ትግሉ ከተጀመረ በሁዋላ በመጨመሩ፤የህዋት መንግስት በየክልሉ የመከላከያ ሰራዊትነት ምዝገባን ለማካሄድ ከጥሩ የደሞዝ ክፍያ ጋር ጥሪ ቢያደርግም የሚመዘገብለት ማጣቱ በሌሎች አስገዳጅ መንገዶች ወጣቶችን በማታለል በግዳጅ ወደ መከላከያ ያስገባበት ሁኔታ መኖሩን ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።

በአማራው ተጋድሎ የተነሳ ዳሸን ቢራ ኪሳራ ውስጥ እየወደቀ ነው | “ዳሸን ቢራ የጠጣ የወገኑን ደም የጠጣ ነው”



dashen
(ዘ-ሐበሻ) የአማራው ሕዝብ ከትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ጋር እያደረገ ባለው የነጻነት ትግል አንደኛው አካል ዳሸን ቢራን ማዳከም እንደሆነ በተደጋጋሚ ከአማራው ተጋድሎ አስተባባሪዎች ሲገልጹ ነበር:: የአማራው ተጋድሎ በተፋፋመባቸው ጎንደር እና ጎጃም የዳሽን ቢራን የጫኑ መኪኖች ጥቃት ሲደርሰባቸው ቆይቷል:: በተለይም ዳሸን ቢራ በአማራ የልማት ድርጅት ስም የተቋቋመ የትግራይ ነጻ አውጪው መንግስት ንብረት በመሆኑ ይኸው ጨካኝ መንግስት አማሮችን ሲገድል የዳሸን ቢራ ንብረቶችን ሁሉ ተጠቅሟል::
በአሁኑ ወቅት በመላው አማራ ክልል ዳሸን ቢራን የጠጣ የወገኑን ደም የጠጣ ነው በሚል በተደረገ ቅስቀሳ ሕዝብ ቢራውን መጠጣት አቁሟል:: ሰዎች ሲጠጡ ከተገኙም “የወንድምህን ደም ጠጣ” እየተባሉ እንደሚረገሙ የሚደርሰን መረጃ ያመለክታል::
ከአማራ ክልል አሞራው ምንአለ ባሻ በለቀቁት መረጃም ይህንኑ አረጋግጠዋል:: መረጃቸው እንደወረደ ይኸው:-
የልጆቻችን ደም አንጠጣም ያለው የአማራ ህዝብ ከዳሸን ጋር እጅግ ተለያይቷል።በተለይም የባህርዳሩ ብቸኛ አከፋፋይ #ኮበል ኢንዱስትሪ ጥበቃዎች ባህር ዳር ላይ ወጣቶችን ከአጋዚ ጋር በመተባበር በጥይት ካረገፏቸው በኋላ ዳሸን በሁሉም የአማራ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ከህዝብ ተለይቷል።
ጎንደር እንፍራንዝ አካባቢ የተወሰደው እርምጃ ለዚህ ማሳያ ነው።ይህ ያስጨነቀው የጥረት ኮርፖሬት በግዳጅ እንዲሸጡ እና እንዲገዙ በሚል #የባህርዳር ግሮሰሪ ባለቦቶችን #በአቫንቲሊሰበስብ መሆኑን መረጃው ደርሶናል።የዳሽን ቢራ ስራአስኪያጅ በጠራውና ታደሰ ጥንቅሹ ይመራዋል በተባለው ስብሰባ ውይይቱ ምን ላይ ይደረሳል የሚለው መልስ እጅግ በጣም ቀላል ነው። #የልጆቻችን ደም አንጠጣም የሚለው የአማራ ህዝብ በሁሉም አካባቢ ቀጥሏል።

ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ በአራት ድርጅቶች ተመሰረተ!!!!



አራት የፖለቲካ ድርጅቶች ወያኔን ለመታገል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ የተሰኘ የጋራ ንቅናቄ መመስረታቸው ይፋ ሆነ፡፡ እነዚህም አርበኞች ግንቦት ሰባት የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፡ የኦሮሞ ዶሞክራሲያዊ ንቅናቄ፡ የአፋር ህዝብ ፓርቲና የሲዳማ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሲሆኑ ምስረታውን አስመልክቶም በመጪው እሁድ ኦክቶበር 30/2016 መሪዎቹ በሚገኙበት በዋሽንግተን ዲሲ የፊርማ ስነ-ስርአት እንደሚደረግ ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄን ምስረታን አስመልክቶም በመጪው በዋሽንግንወ ዲሲ በሚደረገው የፊርማ ስነ-ስርአት ላይ ለመገኘትም የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ሊ/መንበር የሆኑት አቶ ሌንጮ ለታና ም/ሊ/መንበር የሆኑት አቶ ዲማ ነገዎ እንዲሁም የአፋር ህዝብ ፓርቲ ሊ/መንበር የሆኑት ዶ/ር ኮንቴ ሙሳ አሜሪካ መግባታቸው ሲታወቅ የሲዳማ ህዝብ ዲሞክራሲያው ንቅናቄ ሊ/መንበር የሆኑት አቶ በቀለ ዋዩ በቅርቡ አሜሪካ እንደሚገቡ ይጠበቃል፡፡
የአዲሱን ንቅናቄ ምስረታን በይፋ በሚያበስረውና እሁድ በዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገው የመሪዎቹ የፊርማ ስነ-ስርአት ላይ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ሊ/መንበር ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ እንደሚገኙ የሚጠበቅ ሲሆን ዜናውን እስከአጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ አሜሪካ መግባታቸው ያለመታወቁን ዜናው ጨምሮ ሲያስረዳ ከፊርማው ስነ-ስርአት በተጨማሪ አራቱም የአራቱም መሪዎች በተገኙበት ህዝባዊ ጉባኤ እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል፡፡

A message to the participants of the Oromo Leadership Convention in Atlanta



oromo
By Berhanu Gutema Balcha (PhD)
We follow very closely your vigorous and enduring efforts to advance the Oromo people’s struggle. There is always less costly and less time consuming road to victory. On the contrary, very huge sacrifices and terrible losses can make the victory pointless. “A Pyrrhic victory is a victory that inflicts such a devastating toll on the victor that it is tantamount to defeat”. Great leaders are willing to compromise to save the people, and we hope that the 12. November 2016 the Oromo Leadership Convention in Atlanta will aim to suggest a better and less costly road to victory for all in Ethiopia. “The means by which we achieve victory are as important as the victory itself.”
Many people hope that it is possible to formulate a mainstream political agenda for the Oromo people that can help to build trustworthy and effective cooperation with other non-Oromo political groups in Ethiopia. Trustworthy and effective cooperation will create synergy in the anti-TPLF struggle. However, it is very difficult to accommodate extreme objectives in a mainstream political agenda. Accommodating an extreme goal in the mainstream political agenda can create a risk to make a vague and ambiguous political agenda such as “self-determination”, “up to secession”, “referendum” etc., which could not attract any meaningful and trustworthy cooperation with other non-Oromo political groups. People under subjugations have unconditional rights to struggle in whatever way possible, whether it is agreed or not. So it is not essential now to have an agreement with other horizontal non-Oromo political groups about how to solve probable subjugations in the future. No one is forced to live under subjugation that whether there is an agreement or not.

Sunday, October 30, 2016

ኮንትራታቸውን የጨረሱ የወያኔ ሰራዊት አባላት አዲስ ኮንትራት አንፈርምም አሉ!



የወያኔ ሰራዊት አባላት የሆኑና የሰባት አመት ኮንትራታቸውን የጨረሱ አዲስ የሰባት አመት ኮንትራት እንዲፈርሙ የቀረበላቸውን ጥያቄ በአባላቱ ተቀባይነት ያለማግኘቱ ሲታወቅ በመከላከያም በኩል በወቅቱ ከሚገኝበት ሁኔታ ሳቢያ ሰራዊቱን ማሰናበት ያለመፈለጉ ታውቋል፡፡
የደረሰን መረጃ እንደሚያስረዳው የወያኔ መከላከያ ሰራዊት አባላት የሆኑ በ1999 ዓ/ምና 2001 ዓ/ም የተቀጠሩ የፈረሙት የሰባት አመት የስራ ኮንትራት በመጠናቀቁ ምክንያት ሁለተኛ ዙር የሰባት አመት ኮንትራት እንዲፈርሙ ደብዳቤ ቢደርሳቸውም በአብዛኛው የሰራዊቱ አባላት እስካሁን ለመፈረም ፈቃደኛ ያለመሆናቸው ይልቁንም ወደ የቤተሰባቸው መመለስ እንደሚፈልጉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
መረጃው አያይዞም የመከላከያ ሰራዊቱ አመራር አካላት የምንገኘው በፈታኝ ወቅት ላይ ነው በሚል ኮንትራት የጨረሱትን የሰራዊቱ አባላት አዲሱን ኮንትራት እንዲፈርሙ ለማግባባት ቢሞክሩም እስከአሁን ያልተሳካላቸው መሆኑን ሲያስረዳ በአንፃሩም ሰራዊቱም በዚህ ወቅት ማሰናበት እንደማይችሉ ለአባላቱ የገለጹ መሆኑን ያስረዳል፡፡
በተጨማሪ ኮንትራቱን አንፈርምም ያሉት የሰራዊቱ አባላት በቆይታቸው ሊያገኙት የሚችሏቸውን ማንኛውም ጥቅማ ጥቅም በመከልከል አስገድዶ ለማስፈረም የተለመደው ሙከራ መደረጉ የማይቀር መሆኑን መረጃው ሲያስረዳ በአሁኑ ሰአት የወያኔ ስርአት የገጠመውን ፈተና በሰ ራዊት ሀይል ለመቋቋም በመጣር ላይ መሆኑና ተጨማሪ ሰራዊት መመልመል ያለመቻሉ ተጨማሪ ፈተና በሆነበት በአሁኑ ወቅት ኮንትራታቸው ን በጨረሱ የሰራዊቱ አባላትን በግዳጅ በስራ ለማቆየት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ሊፈጥር የሚችለው ችግር ምልክቶች ከወዲሁ እየታዩ መሆኑንም ጨምሮ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Friday, October 28, 2016

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቱሪዝም እንዱስትሪው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ ነው

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቱሪዝም እንዱስትሪው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ ነው

ጥቅምት ፲፮ (አሥራ ስድስት ቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ የተከሰተው ህዝባዊ ተቃውሞና ተቃውሞውን ተከትሎ የታወጀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣ በእያመቱ ከ3 ቢሊዮን ዶላር ያላነሰ ገቢ የሚያስገኘውን የቱሪዝም እንዱስትሪ ክፉኛ እንደጎዳው ፋይናንሻል ታይምስ ዘግቧል።
ምንም እንኳ ገዢው ፓርቲ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች ችግር የሌለባቸው በመሆኑ ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ መግባት እንደሚችሉ ቢናገርም፣ የውጭ አገር የአስጎብኝ ድርጅቶች አማካሪዎች ግን ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁም በሁዋላ ሁኔታው አስፈሪ በመሆኑ ቱሪስቶች እንዳይጓዙ መክረዋል።
አሜሪካ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ ፣ እንግሊዝና ሌሎችም የአውሮፓ አገራት ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ ያወጡት ማስጠንቀቂያ ገዢውን ፓርቲ በእጅጉ ያበሳጨው ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቱሪስቶችን አይመለከትም የሚል መግለጫ አውጥቷል። ማንኛውም ዜጋ ዋና ዋና በሚባሉት መንገዶች እንዳይጓዝ ታግዶ ባለበት ወቅት እንዲሁም ቱሪስቶች ጉዳት ሲደርስባቸው እርዳታ ለመስጠት የሚችሉ የኢምባሲ ሰራተኞች ከአዲስ አበባ 40 ኪሎሜትር ውጭ እንዳይወጡ ታግደው በሚገኙበት ወቅት አዋጁ ቱሪስቶችን አይመለከትም መባሉ ግራ አጋብቷል።
የቨርሲክ ማፕል ክሮፍት የአደጋ ተንታኝ የሆኑት ኢማ ጎርዶን ፣ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ካለፉት ሳምንታት ጋር ሲነጻጸር ጸጥ ያለ ቢመስልም፣ ተቃውሞው ግን አልቆመም ብለዋል። የስራ ማቆም አድማ፣ ከተሞችን ሰው አልባ ማድረግ፣ እና ሌሎችም ሰላማዊ ትግሎች አሁንም ድረስ እየተካሄዱ መሆኑን የገለጹት ተንታኟ፣ እነዚህን ድርጊቶች በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ሆነ በፖሊስ ለማስቆም እንደማይቻል ገልጸዋል።
ተቃውሞውን የሚያካሂዱ ወገኖች እንዴት አድርገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንደሚቋቋሙት መላ ከዘየዱ በሁዋላ፣ በተለይም ማህበራዊ ሚዲያ መዘጋቱን፣ የፖለቲካ ውይይት መከልከሉንና ስብሰባ ማከሄድን አለመቻሉን አስመልክቶ መፍትሄ ከፈለጉ በሁዋላ አመጹ እንደገና ሊካሄድ ይችላል ብለዋል።  የውጭ አገር ኩባንያዎች ህዝባዊ ተቃውሞውን ተከትሎ በአገር ውስጥ በመቆየትና በመልቀቅ መካከል እየዋዠቁ ነው።

ወታደራዊ ምዝገባ ለማካሄድ ቅስቀሳ እየተካሄደ ነው


ጥቅምት ፲፮ (አሥራ ስድስት ቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :- የመከላከያ ሰራዊቱ የተለያዩ አጋጣሚዎችን በመጠቀም እየጠፋ በመምጣቱ የሃይል መሳሳት ያጋጠመው አገዛዙ፣ ወጣቶችን ወደ ውትድርና ስልጠና ለመውስድ አዲስ ማስታወቂያ እያስነገረ ቢሆንም፣ ጥሪው ተቀባይነት አላገኘለትም። በአማራ ክልል በሚገኙ ከተሞች እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ ወጣቶች እንዲመዘገቡ የሚያሳስቡ ማስታወቂያዎች እንየተነገሩ ነው። ቀደም ብሎ በግልጽ ይወጣ የነበረው የወታደር የቅጥር ማስታወቂያ ተቀባይነት ማጣቱ በሚዲያ ከተዘገበ በሁዋላ፣ አገዛዙ ቅጥሩን በተለዬ መንገድ ለማስፈጸም እንቅስቃሴ ጀምሯል። ወጣቶቹ የትምህርት ስልጠና እንደሚሰጣቸው እየተነገራቸው እንዲመዘገቡ በማድረግና ስልጠናውን በአዋሽና በሌሎችም ቦታዎች እንዲካሄዱ በማድረግ፣ ወጣቶችን ወደ ውትድርና የማስገባት እቅድ መነደፉን ምንጮች ገልጸዋል።
የህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ አዲስ ባወጣው አዋጅ ፣ አዋጁ እስከሚነሳበት ጊዜ ድረስ ወታደሮች የስራ መልቀቂያ ወይም የእረፍት ፈቃድ መጠየቅ አይችሉም። በዚህ ውሳኔ ከ7 ሺ ያላነሱ 7 አመታት አገልግለው የስራ መልቀቂያ የጠየቁ ወታደሮችን አግቶ ለመያዝ እንዳስቻለው ምንጮች ገልጸዋል። የ7 አመታት ግዴታቸውን ፈጽመው የስራ መልቀቂያ የሚያቀርቡ ወታደሮች መበራከቱን ተከትሎ ገዢው ፓርቲ በአዳዲስ ምልምል ወታደሮች ለመተካት ቢያልምም ይህም እቅዱ አልተሳካም።
ሰራዊቱ በህጋዊ መንገድ ስንብት ሲጠይቅ “በኢትዮጵያ ሰንደቃላማ እና በመለስ አጽም” እየተባለ ይለመን የነበረው አሰራር ዋጋ አልባ መሆኑን ተከትሎ፣ የመልቀቂያ ጥያቄያቸውን በድፍረት ሲያቀርቡ የነበሩ በርካታ ወታደሮች ታስረዋል። በሁለቱ ክልሎች የተፈጠረውን ተቃውሞ ተከትሎ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች የጠፉ ሲሆን፣ ብዙዎች መሳሪያቸውን እየሸጡ ከህዝብ ሲቀላቀሉ ሌሎች ደግሞ የነጻነት ሃይሎች ተቀላቅለዋል።
በሌላ በኩል አገሪቱን የሚገዛው ወታደራዊ እዙ ወይም ኮማንድ ፖስቱ ከ800 በኦሮምያና አማራ ክልሎች ከወታደሮች የተቀሙ ከ 513 ጠመንጃዎች ከ300 በላይ የሚሆኑትን አስመልሻለሁ ብሎአል።
የተባለው አሃዝ ትክክል ይሁን አይሁን ማረጋጋጥ ባይቻልም፣ ወታደሮች አሁንም ድረስ መሳሪያቸውን እየያዙ እንደሚጠፉ ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ። የሚጠፉ ወታደሮች የተሻለ አቀባባልና አያያዝ እንደሚደረግላቸው የአርበኞች ግንቦት7 ሊ/መንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ መገልጻቸው ይታወሳል።

የአጋዚ ጦር እየተበታተነ ነው ተባለ

የአጋዚ ጦር እየተበታተነ ነው ተባለ

ጥቅምት ፲፰ (አሥራ ስምንት ቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :- በቅርቡ አጋዚ ክፍለጦርን ለቀው የወጡ ወታደሮች ለኢሳት እንደገለጹት ጦሩ ከምንጊዜው በላይ እየተበታተነ ይገኛል። አብዛኛው የሰራዊቱ አባል በክፍለጦሩ ውስጥ የሚታየውን ፍጹም ዘረኝነት በመጥላት እየጠፋ ፣ ክፍለጦሩን አመናምኖታል። በአሁኑ ሰአት 2 ሺ የሚሆኑ አባላት ብቻ የቀሩ ሲሆን፣ ከ2007 ዓም ጀምሮ እስካሁን ወደ 3 ሺ የሚደርሱ የአጋዚ ወታደሮች ጥለው ጠፍተዋል። በተለይ ጦሩ ሶማሊያ ገብቶ ከወጣ በሁዋላ አብዛኛው የሰራዊት አባላት አጋጣሚውን ተጠቅመው ጥለው ጠፍተዋል። በእያንዳንዱ ቲም ውስጥ ቀደም ብሎ 10 ወታደሮች የነበሩ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰአት 3 ብቻ ይገኛሉ።
አብዛኞቹ የአጋዚ ጦር አባላት በአብዛኛው በኦሮምያ ሻሸመኔ አካባቢ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የአጋዚ ጦር አባላት ቁጥር መመናመኑን ተከትሎ ከአጋዚ ጦር ውጭ ያሉ ወታደሮች እንዲመደቡ መደረጉንም ገልዋጸል። የአጋዚ ጦር አባላት ሁኔታዎች ቢመቻችላቸው ሁሉም ከሰራዊቱ ለመልቀቅ ፈቀዳኛ ናቸው የሚሉት አባላቱ፣ በአሁኑ ጊዜ አጋጣሚውን እየፈለገ የሚወጣውን ወታደር ለመተካት አዲስ ምልምል ወታደሮችን ማግኘት አልተቻለም ይላሉ።
በሶማሊያ በአጋዚ ጦር አባላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንም ወታደሮቹ ተናግረዋል። ሶማሊያ ገብተው ከፍተኛ መስዋትነት ቢከፍሉም፣ በመልሱ ምንም ጥቅም አለማግኘታቸውን ተናግረዋል። ከዚህም በላይ ከሻለቃ በላይ ያሉት አዛዦች ከአንድ ብሄር የተውጣጡ በመሆናቸውና ትእዛዝ የሚሰጡትም እነሱ በመሆናቸው፣ ተራው ወታደር ሊቃወም ቢሞክር በቀጥታ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ ኢሳት በቡድን ያነጋገራቸው አባላቱ ተናግረዋል።

የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ ተጠየቀ

የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ ተጠየቀ

ኢሳት (ጥቅምት 18 ፥ 2009)Image result for canada
የካናዳ መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ልማታዊ ትብብር በመጠቀም በሃገሪቱ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ የካናዳ የፓርላማ አባላት ጠየቁ።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ካለው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ወደ 1ሺ 600 አካባቢ ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውን ያወሱት የፓርላማ አባላቱ የካናዳ መንግስት ማንኛውንም አማራጭ በመጠቀም እርምጃ እንዲወስድ ፒተር ኬንት የተባሉይ የፓርላማ አባል አሳስበዋል።
ለሃገራቸው መንግስት የጽሁፍ መልዕክትን ያቅረቡት የፓርላማ አባሉ፣ ካናዳ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ድጋፍ ለዴሞክራሲ መከበር ስትል ተጽዕኖን ለማድረግ በአማራጭነት መመልከት እንደሚገባት ጠይቀዋል።
“ሁሉም ኢትዮጵያ ሰላምና ደህንነቱ ተጠብቆ መኖር ይኖርበታል” ሲሉ በጽሁፋቸው ያመለከቱት ፒተር ኬንት በህግ የበላይነት የሚያምን መንግስት ብቻ ይህንን ስርዓት ተግባራዊ ሊያደርግ እንደሚችል አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ ህብረት አዋጁ የሰብዓዊ መብት ረገጣን ያባብሳል ሲሉ ስጋታቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል።
አሜሪካ በተለየ መልኩ ዜጎቿ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ ማሳሰቢያን የሰጠች ሲሆን፣ የሃገሪቱ ዕርምጃ በሌሎች አለም አቀፍ አካላት ዘንድ ስጋት መፍጠሩ ይነገራል።
መቀመጫቸውን በካናዳ ያደረጉት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጠንካራ ዕርምጃን መውሰድ ይኖርበታል ሲሉ ዘመቻ ሲያካሂዱ መቆየታቸውን CBC የተሰኘ የሃገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።
በኢትዮጵያ ከሽብርተኛ ድርጊት ጋር በተያያዘ ለእስር ተዳርጎ የሚገኝ አንድ ካናዳዊ ለማስለቀቅ የካናዳ መንግስት ማንኛውንም ጫና ማድረግ እንዳለበት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማቱ በመጠየቅ ላይ ናቸው።
ባሽር ማክታል የተባለው ካናዳዊ ወደ ሶማሊያ ባቀና ጊዜ በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር ውሎ በሽብርተኛ ወንጀል ክስ የእድሜ ልክ ዕስራት እንደተላለፈበት ለመረዳት ተችሏል።
ይሁንና የሃገሪቱ የፓርላማ አባላትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫናን በማሳደር ግለሰቡ እንዲለቀቅ የሚተየቅ ዘመቻን እያካሄዱ እንደሆነ ታውቋል።
https://travel.gc.ca/destinations/ethiopia

Ethiopia - Exercise a high degree of caution

There is no nationwide advisory in effect for Ethiopia. However, you should exercise a high degree of caution due to the volatile security situation.

Borders with Eritrea (including the Danakil Desert), Sudan and South Sudan, as well as the Somali and Gambella regions - Avoid all travel

Global Affairs Canada advises against all travel to the area within 10 km of the borders with Eritrea and South Sudan, as well as to the Somali and Gambella regions and the Danakil Desert. Avoid all travel within 20 km of the border with Sudan.
See Safety and security for more information.

Border with Kenya - Avoid non-essential travel

Global Affairs Canada advises against non-essential travel to areas within 10 km of the border with Kenya due to inter-tribal clashes and banditry.
See Safety and security for more information.

Amhara and Oromia Regions - Avoid non-essential travel

Global Affairs Canada advises against non-essential travel to Amhara and Oromia Regions due to ongoing unrest. The city of Addis Ababa is not included in this advisory.

በኢትዮጵያ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 12 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከስራቸው ታገዱ


ኢሳት (ጥቅምት 18 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራቶች ውስጥ ከተቋቋሙበት አላማ ውጭ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉት 12 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከስራቸው ታገዱ።
ከአራት አመት በፊት አጨቃጫቂ ነው የተባለው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የሚቆጣጠረው አዋጅ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በየጊዜው ቁጥጥር እየተደረገባቸው ከስራቸው የሚደረጉ ሃገር በቀልና የውጭ ድርጅቶች ቁጥር እየጨማረ መምጣቱም ታውቋል።
የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ የስራ ፈቃዳቸው የታገደባቸው ተቋማት ፈቃድ ሲያወጡ እንሰራለን ካሉት ስራ ውጭ ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው ነው ሲል ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።
ይሁንና ድርጅቶቹ በምን አይነት ስራ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ እንደነበርና የሃገር ውስጥ አሊያም የውጭ ይሁኑ መንግስት ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ተቆጥቧል።
አንዳንድ ድርጅቶች ከውጭ እንደመቋቋቸው የውጭ ተቋማት ተልዕኮ ለማስፈጸም ይሞክራሉ ሲሉ የኤጀንሲው ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
ባለፉት ሶስት ወራቶች ውስጥ ብቻ ከተቋቋሙበት አላማ ውጭ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ድርጅቶችን በስም ያልጠቀሰው መንግስት ከታገዱት የበጎ አድራጎት ተቋማት በተጨማሪ ከስድስት ድርጅቶች የመጀመሪያና የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱም ተነግሯል።
የኢትዮጵያ መንግስት የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ያወጣውን አዋጅ ተከትሎ አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት ዕርምጃው የተቋማቱን ስራ ለመከታተል እንደሆነ ስጋታቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል።
የአዋጁ መተግባርን ምክንያት በማድረግ ከ100 የሚበልጡ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ስራቸውን እንዳቋረጡ የሚታወስ ነው።

በታንዛኒያ ለእስር የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር ከ500 በላይ መድረሱ ተገለጸ

በታንዛኒያ ለእስር የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር ከ500 በላይ መድረሱ ተገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 18 ፥ 2009)
በታንዛኒያ በህገ-ወጥ መንገድ ገብታችኋል ተብለው በተለያዩ ጊዜያት ለእስር የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር ከ500 በላይ መድረሱን የሃገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ።
የሃገሪቱ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ከአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ ጠይቃ በመጠባበቅ ላይ መሆኗ ታውቋል።
ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ታንዛኒያን እና ሌሎች የአካባቢውን ሃገራት ለመሸጋገሪያነት እየተጠቀሙ መሆኑን ዘ ሲቲዝን የተሰኘ የታንዛኒያ ጋዜጣ ዘግቧል።
በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙትን እነዚህኑ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ የአለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት ጥረት ቢደረግም ድጋፍ ሊያገኝ አለመቻሉን በታንዛኒያ የድርጅቱ ተወካይ ቃሲም ሱፊ ለመገኛና ብዙሃን አስረድተዋል።
በታንዛኒያ በተለያዩ ጊዜያት በህገ-ወጥ መንገድ ገብቷችኋል ተብለው በቁጥጥር ስር ከዋሉት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተጨማሪ ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸው በጎረቤት ማላዊ እና ሌሎች ሃገራት በእስር ላይ እንደሚገኙም ታውቋል።
በማላዊ ብቻ 120 ኢትዮጵያውያን በሶስት እስር ቤቶች የሚገኙ ሲሆን፣ የህገሪቱ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ኢትዮጵያውያኑ በአስከፊ የጤና ችግር ውስጥ የሚገኙ በመሆኑ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ዘመቻን እያካሄዱ ይገኛል።
ባለፈው አመት በሃገሪቱ የተለያዩ ክልሎች የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ተለያዩ ሃገራት በመሰደድ ላይ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።

ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!
ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም
ይቺ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስንት የመከራ ወንዞችን ተሻግራለች! ገና ስንት ትሻገራለች! ስንት የግፍ ተራራዎችን አቋርጣለች! ገና ስንት ታቋርጣለች! ስንት የበደል ሰይፎችንና ጦሮችን አምክናለች! ገና ስንት ታመክናለች! ስንት የውጭ ኃይሎችን አሳፍራለች! ገና ስንቱን ታሳፍራለች! ስንት አምባገ- ነኖችን እያለቀሰች ቀብራለች! ገና ስንቱን ትቀብራለች! ጭቆና ከኢትዮጵያውያን ደም ሙልጭ ብሎ ወጥቶ በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በዳኝነት በጠራ ደም እስቲተካ ድረስ “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ” ትጸልያለች! እግዚአብሔርም ቃል ኪዳን አለበት ይሰማታል! የኃያላን ኃያል ኢትዮጵያ እንድትፈርስ አይፈቅድም!
የኢትዮጵያን መፈራረስ የሚመኙ ግለሰቦችም መንግሥቶችም ሞልተዋል፤ ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ የሚመኙ ጭንጋፍ ልጆችም አሏት፤ ማኅጸንዋ እየደማ እየረገማቸው ሰላምና እንቅልፍ አጥተው አብጠው ይፈነዳሉ፤ የኢትዮጵያን መፈራረስ የሚመኙ መንግሥቶች ሁሉ ከዚህ በፊት ቀድመው ፈራርሰዋል፤ ወደፊትም ይፈራርሳሉ።
የአገራቸው ፍቅር፣ የእርስበርሳቸው ዝምድና፣ የተራራውና የሸለቆው፣ የሜዳውና የገደሉ፣ የበረሀውና የለምለሙ፣ የዝናቡና የወንዙ፣ የዓየሩና የነፋሱ፣ የበዓላቱና የድግሱ፣ ያለውን አብሮ መቋደሱ፣ ተዝካሩ፣ ሙታዓመቱ ለሞቱ፣ መላእክቱ፣ ቅዱሳቱ፣ ሰማዕታቱ፣ እየተሸከሙ ያደረሱት ጸሎቱ፣ ለምዕተ-ዓመታት የተከማቸው እምነቱ፣ ሃይማኖቱ፣ በዚህ ሁሉ የተገነባው ኅብረቱ እንዴት ይፈርሳል! ማን ችሎ ያፈርሰዋል! አፍራሾች ቀድመው ይፈርሳሉ!
አንዳንዶች ቢጨነግፉም፣ አንዳንዶች ቢክዱም፣ አንዳንዶች ሆዳም ቢሆኑም፣ አንዳንዶች ቢወላውሉም፣ ኢትዮጵያ ልጆች አሏት፣ አሁንም የሚሞቱላት፣ ያልበሏት፣ የሚሳሱላት፤ ያልሸሿት፤ አፈሯን የሙጢኝ ብለው አፈርሽ እንሁን የሚሏት፣ ደሀነትም ሆነ ጭቆና ካንቺ አይለዩንም የሚሏት፤ ኢትዮጵያ ዛሬም ልጆች አሏት ስትፈርስ ቆመው የማያዩ፣ ሲያማት ነፍሳቸውን ዘልቆ የሚያማቸው፣ ሳልፈርስ አትፈርስም ነው ቃል ኪዳናቸው!
ቱርክና ግብጽ መጥተው ሄደዋል፤ ፖርቱጋል መጥቶ ሄዷል፤ እንግሊዝ መጥቶ ሄዷል፤ ኢጣልያ መጥቶ ሄዷል፤ ጠላቶች እየመጡ በመጡበት ተሸኝተዋል፤ ወዳጆች በጨዋነት ተስተናግደው ተዋኅደዋል፤ ቤተ ሙሴ፣ ቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ እስልምና ኢትዮጵያዊ ሆነዋል፤ ዛሬ እንግዳ አይደሉም፤ ዛሬ ባዕድ አይደሉም፤ ኢትዮጵያ በፍቅር ለመጣ ፍቅር ነች፤ ምቹ ነች፤ በጠብ ለመጣ እሾህ ነች፤ ትዋጋለች።
ኢትዮጵያ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ ለአንቺ የተናገረው ይመስለኛል፤ ‹‹ብርሃንሽ መጥቶአልና፣ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፤ አብሪ፤ እነሆ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ይሸፍናል፤ ነገር ግን በአንቺ ላይ እግዚአብሔር ይወጣል፤ ክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል፤ አሕዛብም ወደብርሃንሽ፣ ነገሥታትም ወደመውጫሽ ጸዳል ይመጣሉ። ዓይኖችሽን አንስተሽ በዙሪያሽ ተመልከቺ፤ እነዚህ ሁሉ ተሰብስበው ወደአንቺ ይመጣሉ፤ ወንዶች ልጆችሽ ከሩቅ ይመጣሉ፤ ሴቶች ልጆችሽንም በጫንቃ ላይ ይሸከሙአቸዋል፤ በዚያን ጊዜ የባሕሩ በረከት ወደአንቺ ስለሚመለስ፣ የአሕዛብም ብልጥግና ወደአንቺ ስለሚመጣ አይተሽ ደስ ይልሻል፤ ልብሽም ይደነቃል፤ ይሰፋማል፤ የግመሎች ብዛት የምድያምና የጌፌር ግመሎች ይሸፍኑሻል፤ ሁሉ ከሳባ ይመጣሉ፤ ወርቅንና ዕጣንን ያመጣሉ፤ የእግዚአብሔርንም ምስጋና ያወራሉ፤ የቄዳር መንጎች ሁሉ ወደአንቺ ይሰበሰባሉ፣ የነባዮትም አውራ በጎች ያገለግሉሻል፤ እኔን ደስ ሊያሰኙ በመሠዊያዬ ላይ ይወጣሉ፤ የክብሬንም ቤት አከብራለሁ።›› (60፡1-7)
ኢትዮጵያ ትወድቅ ይሆናል፤ ግን ያለጥርጥር ትነሣለች፤ በፊትም ወድቃ ተነሥታለችና፤ ኢትዮጵያ ትሰነጠቅ ይሆናል፤ ግን ያለጥርጥር ትገጥማለች፤ በፊትም ተሰንጥቃ ገጥማለችና፤ ለኢትዮጵያ በጎ የማይመኙላት የአየሉ ቢመስሉም የንስሐ ጊዜ ስትሰጣቸው ነው፤ ኢትዮጵያ ዕብሪተኞችንም ትሕትና ታስተምራቸዋለች፤ ዕብሪተኞች ከነዕብሪታቸው በራሳቸው እሳት ቀልጠው እስቲያልቁ ኢትዮጵያ ትእግስትዋ አያልቅም፤ ኢትዮጵያ ትእግስት ነችና።
በበጎ መንፈስ እስከተመራን ድረስ፣ ፍርሃትንና አለመተማመንን፣ ጥላቻን፣ ጠብንና ድብድብን፣ ሊዘሩብን ከሚፈልጉ ርኩሳን መናፍስት ከራቅን ኢትዮጵያችን አትፈርስም፣ የደፈረሰውም ቶሎ ይጠራል።


በኢትዮጵያ ለምትኖሩ ሁሉ ላይ ፌስቡክን ለመጠቀም TOR browser ይጠቀሙ።

በኢትዮጵያ ለምትኖሩ ሁሉ
ከዴስክቶፓችሁ ላይ ፌስቡክን ለመጠቀም TOR browser ይጠቀሙ።
https://www.torproject.org/projects/torbrowser.html.en 
ይህ ብራውዘር በመንግስት የተቆለፉ ሳይቶችን ይከፍታል ። በመንግስት ክትትል የሚደረግባቸውን ሳይህቶች ከመንግስት ይሸፍናል ። ምርጥ ነው ይሞክሩት!
ተመሳሳይ የቴክኖሎጂ ትምህርቶችን በቪዲዮ አዘጋጅተን እናቀርባለን !


What is the Tor Browser?
I Advise to use TOR Browser in Ethiopia  in such a country that spies the citzen, and TOR coudnot be blocked by the government.

The Tor software protects you by bouncing your communications around a distributed network of relays run by volunteers all around the world: it prevents somebody watching your Internet connection from learning what sites you visit, it prevents the sites you visit from learning your physical location, and it lets you access sites which are blocked.

The Tor Browser lets you use Tor on Windows, Mac OS X, or Linux without needing to install any software. It can run off a USB flash drive, comes with a pre-configured web browser to protect your anonymity, and is self-contained (portable).
Screenshot of
      bundle startup

ስናፕ ቪፒ ኤን የሚባለው አፕልኬሽን ደግሞ ከ ጎግል  ላይ በማውረድ በየሞባይልዎ ወይም ኮምፒተር ላይ ይጫኑት ። ፌስቡክን እና ቫይበርን ያለ አንዳንች እንከን ለመጠቀም ይረዳል ። የሚከተሉትን ሊንኮች በመጫን ዳወን ሎድ ያድርጉ ። ዋይ ፋይ ባለበት አካባቢ አፑን ኦን አድርጉት ። የመንግስታችንን ማዕቀብ ሾልኮ ፌስቡክ ገጭ ይላል ። በአዲስ አበባ እንደዚህ ኢንተርኔት  ከመዘጋቱ በፊት ቪ ፒ ኤን  የጫኑ ኢንተርኔት ቤቶች ደምበኞችን እያስጠቀሙ ናቸው ።Free VPN proxy by Snap VPN
  Free VPN proxy by Snap VPN- screenshot thumbnail
https://play.google.com/store/apps/details?id=free.vpn.unblock.proxy.vpnpro


Monday, October 24, 2016

The U.S. Department of State warns U.S. citizens to defer all non-essential travel to Ethiopia

The U.S. Department of State warns U.S. citizens to defer all non-essential travel to Ethiopia due to ongoing unrest that has led to hundreds of deaths, thousands of arrests, as well as injuries and extensive property damage, especially in Amhara and Oromia States. The U.S. Embassy’s ability to provide consular services in many parts of the country is limited by the current security situation.Image result for us state department
The Government of Ethiopia declared a State of Emergency effective October 8, 2016. An October 15 decree states that individuals may be arrested without a court order for activities they may otherwise consider routine, such as communication, consumption of media, attending gatherings, engaging with certain foreign governments or organizations, and violating curfews. The decree prohibits U.S. and other foreign diplomats from traveling farther than 40 kilometers outside of Addis Ababa without prior approval from the Government of Ethiopia, which severely affects the U.S. Embassy’s ability to assist U.S. citizens. The full text of the decree implementing the State of Emergency is available on the U.S. Embassy’s website.
Internet, cellular data, and phone services have been periodically restricted or shut down throughout the country, impeding the U.S. Embassy’s ability to communicate with U.S. citizens in Ethiopia. You should have alternate communication plans in place, and let your family and friends know this may be an issue while you are in Ethiopia. See the information below on how to register with the U.S. Embassy to receive security messages.
Avoid demonstrations and large gatherings, continuously assess your surroundings, and evaluate your personal level of safety. Remember that the government may use force and live fire in response to demonstrations, and that even gatherings intended to be peaceful can be met with a violent response or turn violent without warning. U.S. citizens in Ethiopia should monitor their security situation and have contingency plans in place in case you need to depart suddenly. 
U.S. government personnel are restricted from personal travel to many regions in Ethiopia, including Oromia, Amhara, Somali and Gambella states, southern Ethiopia near the Ethiopian/Kenyan border, and the area near the Ethiopia/Eritrea border. Work-related travel is being approved on a case-by-case basis. U.S. government personnel may travel to and within Addis Ababa without restrictions. For additional information related to the regional al-Shabaab threat, banditry, and other security concerns, see the Safety and Security section of the Country Specific Information for Ethiopia
Due to the unpredictability of communication in the country, the Department of State strongly advises U.S. citizens to register your mobile number with the U.S. Embassy to receive security information via text or SMS, in addition to enrolling in the Smart Traveler Enrollment Program (STEP). 
For further information:

wanted officials