Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, October 28, 2016

የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ ተጠየቀ

የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ ተጠየቀ

ኢሳት (ጥቅምት 18 ፥ 2009)Image result for canada
የካናዳ መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ልማታዊ ትብብር በመጠቀም በሃገሪቱ ዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊትን እንዲያደርግ የካናዳ የፓርላማ አባላት ጠየቁ።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ካለው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ወደ 1ሺ 600 አካባቢ ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውን ያወሱት የፓርላማ አባላቱ የካናዳ መንግስት ማንኛውንም አማራጭ በመጠቀም እርምጃ እንዲወስድ ፒተር ኬንት የተባሉይ የፓርላማ አባል አሳስበዋል።
ለሃገራቸው መንግስት የጽሁፍ መልዕክትን ያቅረቡት የፓርላማ አባሉ፣ ካናዳ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ድጋፍ ለዴሞክራሲ መከበር ስትል ተጽዕኖን ለማድረግ በአማራጭነት መመልከት እንደሚገባት ጠይቀዋል።
“ሁሉም ኢትዮጵያ ሰላምና ደህንነቱ ተጠብቆ መኖር ይኖርበታል” ሲሉ በጽሁፋቸው ያመለከቱት ፒተር ኬንት በህግ የበላይነት የሚያምን መንግስት ብቻ ይህንን ስርዓት ተግባራዊ ሊያደርግ እንደሚችል አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ ህብረት አዋጁ የሰብዓዊ መብት ረገጣን ያባብሳል ሲሉ ስጋታቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል።
አሜሪካ በተለየ መልኩ ዜጎቿ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ ማሳሰቢያን የሰጠች ሲሆን፣ የሃገሪቱ ዕርምጃ በሌሎች አለም አቀፍ አካላት ዘንድ ስጋት መፍጠሩ ይነገራል።
መቀመጫቸውን በካናዳ ያደረጉት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጠንካራ ዕርምጃን መውሰድ ይኖርበታል ሲሉ ዘመቻ ሲያካሂዱ መቆየታቸውን CBC የተሰኘ የሃገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።
በኢትዮጵያ ከሽብርተኛ ድርጊት ጋር በተያያዘ ለእስር ተዳርጎ የሚገኝ አንድ ካናዳዊ ለማስለቀቅ የካናዳ መንግስት ማንኛውንም ጫና ማድረግ እንዳለበት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማቱ በመጠየቅ ላይ ናቸው።
ባሽር ማክታል የተባለው ካናዳዊ ወደ ሶማሊያ ባቀና ጊዜ በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር ውሎ በሽብርተኛ ወንጀል ክስ የእድሜ ልክ ዕስራት እንደተላለፈበት ለመረዳት ተችሏል።
ይሁንና የሃገሪቱ የፓርላማ አባላትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት የካናዳ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫናን በማሳደር ግለሰቡ እንዲለቀቅ የሚተየቅ ዘመቻን እያካሄዱ እንደሆነ ታውቋል።
https://travel.gc.ca/destinations/ethiopia

Ethiopia - Exercise a high degree of caution

There is no nationwide advisory in effect for Ethiopia. However, you should exercise a high degree of caution due to the volatile security situation.

Borders with Eritrea (including the Danakil Desert), Sudan and South Sudan, as well as the Somali and Gambella regions - Avoid all travel

Global Affairs Canada advises against all travel to the area within 10 km of the borders with Eritrea and South Sudan, as well as to the Somali and Gambella regions and the Danakil Desert. Avoid all travel within 20 km of the border with Sudan.
See Safety and security for more information.

Border with Kenya - Avoid non-essential travel

Global Affairs Canada advises against non-essential travel to areas within 10 km of the border with Kenya due to inter-tribal clashes and banditry.
See Safety and security for more information.

Amhara and Oromia Regions - Avoid non-essential travel

Global Affairs Canada advises against non-essential travel to Amhara and Oromia Regions due to ongoing unrest. The city of Addis Ababa is not included in this advisory.

No comments:

Post a Comment

wanted officials