Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, November 28, 2018

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት ተከሰተ

ከትላንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ነዳጅ በመጥፋቱ ከፍተኛ የመኪናዎች ሰልፍ እየታየ ነው፡፡ ለእጥረቱ ምክንያቱ ምን እንደሆነ የተጠየቁት የሚመለከታቸው ባለስልጣናት እጥረቱ የተከሰተው ህገወጥ የነዳጅ ገበያ በመጨመሩ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ለሪፖርተር ጋዜጣ መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለእጥረቱ ዋነኛ ምክንያት በሕገወጥ መንገድ ከነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ እየተቀዳ በየመንደሩ ስለሚሸጥ ነው ብለዋል፡፡ ይህን ህገ ወጥ የነዳጅ ንግድ ለመቆጣጠር ባለመቻሉ እጥረቱ ከቀን ወደቀን እየተባባሰ መምጣቱን አስረድተዋል፡፡ ‹‹በአሁኑ ወቅት ከማደያዎች ውጪ በተለይ ቤንዚን በኪዮስኮች ጭምር እየተሸጠ ነው›› ያሉት ሃላፊው ይህንን ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለ ጥረት የላላ መሆኑ ደግሞ ችግሩን እንዳባባሰው ጠቁመዋል፡፡
ይህ አንዲህ እንዳለ የመስሪያ ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ህገ ወጥ የነዳጅ ሽያጩ የተባባሰው ወደጎረቤት አገራት ስለሚሸጥም ነው ሲሉ ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ ስለዚህም ከጎረቤት አገራት ጋር ያለው የንግድ ግንኙነት ገደብ ሊበጅለት እንደሚገባ የጠቆሙት ህዝብ ግንኙነቱ የትኛው ጎረቤት አገር እንደሆነ አልገለፁም፡፡ ይሁንና ኤርትራን ማለታቸው እንደሆነ ይታመናል፡፡

Tuesday, November 27, 2018

የብርቱኳን ዉለታ አለብን ከሳዲቅ አህመድ

ከሳዲቅ አህመድ
ብርቱኳንን የተዋወኳት የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊዎች በታሰሩበት ሰሞን ነው።እራሷ ናት የደወለችልኝ። ስለታሰሩት ኮሚቴዎች ጠየቀችኝ።ስለ እስር ቤት አሰከፊነትም አጫወተጭኝ።ከድምጿ አዘኔታን፣ ርህራሄን ሰምቻለሁ። አቅሟ በቻለው መጠንም ማድረግ የሚገባትን እንደምታደርግ ቃል ገብታ ነበር።

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ዋሽንግተን ዲሲ መጥተን በህገወጥ መንገድ ስለታሰሩት የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች እንድናስረዳ ብርቱኳን ሁናቴዎችን አመቻቸች። በቀነ ቀጥሮውም መሰረት እኔና አብዱሰላም (የደስደስ) ያሲን ቦታው ላይ ተገኘን። ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ከብርቱኳን ጋር በግል ተወያየን።በወቅቱ ስለ ኮሚቴው የምንሰማው ነገር እንዳለ ጠየቀችን።እኔ ማስረዳቱን ስቀጥል ብርቱኳን ድንግጥ አለች።ስቅጥጥ ሲላትም አየሁ።በጣም የምትንሰፈሰፍ ሆና አገኘኋት። እስር ቤት የሚጎዳና የሚሰብር ነው። ብርቱኳን ሚደቅሳ ላሸባሪዎቹና ለማፍያዎቹ ህወሃቶች ሳትሰበር የነርሱን የተፈረካከሰ እኩይ ተግባር ለማድቀቅ የበቃች ጀግና ሴት በመሆኗ ሁሌም አክባሪዋ ነኝ። የህግ ባለሙያ የሆነው አብዱሰላም (የደስደስ) ከህግ አንጻር የኮሚቴውን እስርና በፍትህ ስርአት ዉስጥ የተፈጸመውን ሸፍጥ በተዋጣለት መልኩ አስረዳ።ተሰብሳቢው በተመስጥኦ አዳመጠ።አብዱሰላም (የደስደስ) ንግግሩን ሲጨርስ ጭብጨባው ጎላ ያለ ነበር።
በግዜው የአሸባሪነት ትርክት ( narrative) በአለም የመገናኛ ብዙኋን ላይ ናኝቷል።አሸባሪው ህወሃት በኢትዮጵያዊ ዉስጥ አሸባሪነትን ፈብርኮ የኢትዮጵያን ሙስሊሞችን ለማስመታት ይጥራል።ያሰራቸውን ኮሚቴዎች ጂሃዳዊ ሐረካት በሚባል የሐሰት ዘጋቢ ፊልም ባሸባሪነት ፈርጆ የምእራብን ምጽዋት ለማግኘት ይንደፋደፍ ነበር-ህወሃት። ዛሬ መቀሌ በሽፍታነት የገባው የነ ጌታቸው አሰፋ ቡድን ከዚህ እኩይ ተግባር ያንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ይህንን ሴራ ለማክሸፍ ብርቱኳን ሚደቅሳ ባደባባይ ወጥታ ባትናገርም በውስጥ የተቻላትን አድርጋለች።ከተለተለያዩ አለምአቅፍ ተቋማትም ጋር ትገናኝ ነበር።በተለያቱ ግዜያትም ብርቱኳን እየደወለች ስለኮሚቴው ስትጠይቅኝ ኮሚቴዎቹ በእስር ቤት ውስጥ የሚተነፍሱትን የስቃይ ትንፋሽ እየተነፈሰች እንደሆነ ይሰማኝ ነበር።

ብርቱኳን ከህወሃት እስር ቤትና የሽብር ጥቃት ተርፋ፣ መንፈሷን በለውጥ እሳቤ አጎልብታ፣ አሜሪካ በቆየችባቸው አመታቶች በትምርቷ ተራቃ የመጠቀች ድንቅ ሴት ናት።ብርቱኳን ለብዙ ሴት እህቶች #የይቻላል መንፈስን የለገሰች፣በትግል ጣራ ላይ ወጥታ ሌሎች ሴቶችን የሳበች የሴት ተምሳሊት ናት።ዛሬ ሴቶች አገሪቷን ለመምራት ግማሹን ካቢኔ ሲረከቡ፣ሴቶች በተለያየ የስልጣን እርከን ላይ ሲቀመጡ በውስጣቸው ብርቱካናዊ ቁርጠኝነት፣ብርቱካናዊ የአላማ ጽናት አለ ቢባል የእብለት አይሆንም።ብርቱኳን የምርጫ ቦርድን መምራቱ ቢያንሳት እንጂ አይበዛባትምና ልብ ያለው ልብ ይበል።
ይህ ብርቱካናዊ የትግል ጥላ አሁንም ባሉ፣ገና በሚወለዱ ሴት ልጆች ላይ አርፎ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች እርሷን መስለው ከርሷ በላይ ይሆኑ ዘንድ ምኞቴ ነው።እኛም ወንዶች ከርሷ ጥንካሬ ብዙ የምንማረው ነገር አለ ስል ብርቱዋን ብርቱካን መልካም የስራ ዘመን ይሁንልሽ እያልኩ ነው።
በዚህ አጋጣሚ ከላይ የጠቀስኩትን የአምኒስቲ ኢንተርናሽናል ስብሰባም ይሁን ሌሎች የዲፕሎማሲና የላቢ (lobby) ስራዎች ላይ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ጥያቄ የኔ ብሎ ሚዲያ ላይ ሳይወጣ በውስጥ ብዙ ስራዎችን ሲሰራ የነበረውን ዝምተኛውን ጀግና ከባዱ በላቸው ሳላመሰግን አላልፍም።

Monday, November 26, 2018

ኦነግ አዲስ ፓርቲ አይደለሁም እንደ አዲስ አልመዘገብም አለ

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር(ኦነግ) ከምርጫ ቦርድ ጋር የጀመረው ውዝግብ ቀጥሏል፡፡ ከውጭ አገር የገቡ ፓርቲዎች በሙሉ በቦርዱ እንዲመዘገቡ ጥሪ የተላለፈ ሲሆን ኦነግ ግን አልመዘገብም ብሏል፡፡
ለዚህ ያቀረበው ምክንያት ደግሞ በ1983 የሽግግር መንግስቱ ጊዜ የተመዘገብኩ ስለሆነ ድጋሚ መመዝገብ አያስፈልገኝም የሚል ነው፡፡ ይህንኑ ምክንያት ጠቅሶ ለምርጫ ቦርድ ማመልከቻ አስገብቶ የነበረ ቢሆንም በዛሬው እለት ማመልከቻው ውድቅ እንደሆነበት ከምንጮች ሰምተናል፡፡ አሁን በስራ ላይ ባለው የቦርዱ ህግ መሰረት አንድ ፓርቲ ለሁለት የምርጫ ወቅቶች ካልተወዳደረ ምዝገባው እንደሚሰረዝ መደንገጉን ለማወቅ ችለናል፡፡
በመሆኑም ፓርቲው እንደአዲስ እንደሚመዘገብ በህጉ ላይ ተቀምጧል፡፡ እንደአዲስ ለመመዝገብ መተዳደሪያ ደንብ ማቅረብ፣ ጠቅላላ ጉባኤ ማከናወን፣ አባላትን ማሳወቅና ሌሎችም ሂደቶችን ማለፍ ይጠይቃል፡፡ የኦነግ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አዳባ ግን የቦርዱን ውሳኔ እንደማይቀበሉት ገልፀው ይግባኝ እንደሚሉ ተናግረዋል፡፡

Thursday, November 8, 2018

"ያለማንነቱ በግድ በአጋሜዎች የተጨፈለቀው የኢሮቭ ብሔረሰብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም ኤርትራዊም አይደለሁም "አለ።







"ያለማንነቱ በግድ በአጋሜዎች የተጨፈለቀው የኢሮቭ ብሔረሰብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም ኤርትራዊም አይደለሁም "አለ።
-------------------------------------------------------------------
ኦሮባ – ኢሮብ – ‹‹ወደ ቤት ግቡ ›› ማለት ነው!


የኢሮብ ህዝብ በትግራይ ክልል ጉሎ መኸዳ ወረዳ የሚኖር፣ ራሱን የቻለና ትግርኛ ተናጋሪ ያልሆነም የራሱ የሆነ ማንነትና ቋንቋ ያለው: ኢትዮጵያዊ ነገድ ነው።

ኢሮብ በትግራይ ክልል፣ ምሥራቃዊ ዞን የሚገኝ ሲሆን በምሥራቅ አፋር፣ በሰሜን ደግሞ ኤርትራ ያዋስኑታል፡፡

ብዙዎቻችን የኢሮብን ህዝብ ልክ እንደ ህውሓት ወይም እንደ ትግሬ በመቁጠር ለጉዳዩ ትኩረት ሳንሰጥ እንዲሁ ስናላግጥ ውለናል።
የኢሮብ ህዝብ ልክ እንደ ወልቃይት ዐማራ በትግሬዎች የተዋጠ ነገድ ነው። ትግርኛ አይናገሩም። የራሳቸው ቋንቋና ባሕል ያላቸው። በታሪክ አጋጣሚ ግን ከባንዳዎች መሃል ሳንድዊች ሆነው የተገኙ ምስኪን ማህበረሰቦች ናቸው።

በ2007ዓም በተደረገው የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ መሠረት የኢሮብ ብሔረሰብ ብዛት ህውሓት አውቃ በሴራ ካልቀነሰችው በስተቀር 33407 እንደሆኑ ነው የማእከላዊ እስታስቲክስ መሥሪያቤት ሪፖርት የሚያመለክተው።

"ኢሮብ "የሚለው መጠሪያ ነገዱም ወረዳውም ይጠራበታል።

¶ ይህ ነገድ በውስጡ ሦስት ዓይነት ማኅበረሰቦች ያሉት ሲሆን :-

1•አንደኛው "ቡክናይታ" ይባላል፡፡

2•ሁለተኛው ማኅበረሰብ "ሀሳበላ" ይባላል።

3•ሦስተኛው ማኅበረሰብ ደግሞ "እንዳልገዳም" (አድጋዲ ዓረ) ይባላል፡፡

ህውሃቶች "ኢሮብን " ለኤርትራ ሽጠው ህዝቡን በወልቃይት ለማስፈር ነው ዋነኛ እቅዳቸው ። የትግሬ አንባገነኖች በግድ ከ50 ዓመት በላይ የተጨፍለቁት ኢሮቦች እንደ ዐማራው ህውሓት እንዲጠፍ ከወሰነችባቸው ነገዶች ውስጥ ቀዳሚ ናቸው ።

ይህ ነገድ ልክ እንደወልቃይት ዐማራ በትግራዮች በግድ ማንነቱን ነጥቀው እንዲጠፋ የተፈረደበት ምስኪን ነገድ ነው።

"ሳሆ ብሔረሰብ"
ከኢሮብ ህዝብ ከሚናገረው ቋንቋ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቋንቋ ያለው ነገድ" ሳሆ "በመባል የሚታወቀውና አሁን በኤርትራ ግዛት ውስጥ የሚገኝ ብሔር ብቻ ነው።

" የኢሮብና የሳሆን ብሔረሰቦች" የሚለያያቸው የሚከተሉት እምነትና የኢኮኖሚ መሰረታቸው ብቻ ነው።

በአፋር ግዛት አካባቢ የሚገኙ የኢሮብ ነገድ አባላት ናቸው። ቋንቋቸው ግን አንድ ነው።

የኢሮብ ህዝብ እኔ ነኝ ያለ አራሽ ገበሬ ነው፡፡ ልክ በደቡብ ኢትዮጵያ እንደሚኖሩት " የኮንሶ" ነገዶች ተራራውን በእርከን አሳምረው ምርት የሚያፍሱ ታታሪ ገበሬዎች ናቸው ኢሮቦች።

እነ "ኢህአፓ" የትጥቅ ትግላቸውን ሲጀምሩ በኢሮብ አካባቢው ካሉት ተራሮች መካከል " አሲምባ " የሚባለውን ተጠግተው ነበር የትጥቅ ትግላቸውን የጀመሩት። ኋላ ላይ ህውሓት አርዳ በልታ ድራሻቸውን አጠፋቻቸው እንጂ። ከመታረድ የተረፉትን እነ ተፈራ ዋልዋ ፣ እነ በረከት ስምኦን ፣ እነ አዲሱ ለገሰን በራሷ አምሳል " አራጅ " አድርጋ እስክትፈጥራቸው ድረስ የኢሮብን ህዝብ ቀለብ ተሻምተው የሚበሉ ነበሩ። ኢሮብ ለበድኑ ብአዴንም ባለውለታ ነገድ ነው።

"ዳውሃን "የኢሮብ ነገድ ዋና ከተማ ሲሆን፤ ኢትዮ አሜሪካዊው 6 ተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ኢትዮጵያዊው አትሌት ምሩጽ ይፍጠርም የኢሮብ ነገድ አባላት ናቸው። ነፍሱን ይማረውና ምሩጽ በደህና ጊዜ ይህን ጉድ ሳይሰማ አርፏል። ይብላኝ ለቅዱስ ፓትሪያርኩ አይናቸው እያየ ነገዳቸው በቁሙ ተሽጦ ኤርትራዊ ነህ ለተባለው።

ይኽ ነገድ ባለፉት 50 ዓመታት የአካባቢው የተፈጥሮ ሁኔታና የትግራይ ትግሪኝ የፖለቲካ ኤሊቶች ኅብረት ፈጥረው ከምድረ ገጽ ድምጥማጡን ሊያጠፉት የወሰኑበት አሳዛኝና ምስኪን ሀዝብ ነው። ኢሮብ በሰሜናዊ ምስራቅ ትግራይ የሚኖር ብሔረሰብ ነው።

ሻአቢያና ህውሓት ደግሞ ይኼንን ብሔር በኢትዮጵያዊነቱና ኢትዮጵያዊነቱን በማቀንቀኑ ይጠየፉታል። አሁን ግን በሁለቱ ምክክር ከነ አካቴው ህውሓትና ሻአቢያ ተባብረው ድምጥማጡን ለማጥፈት የወሰኑና የቆረጡ ይመስላል።

ተመልከቱ አንድም የትግሬ ህውሓት ባለሥልጣን ወጥቶ ከጎናቸው ሊቆም አልፈቀደም። የራያ ዐማራውና ፆታውን ቀይሮ ህውሓት የሆነው ደፋሩ ጌታቸው ረዳ ሊያናግራቸው በኼደ ጊዜ የኢሮብ አባላት " ትግርኛ ስለማንሰማ በዐማርኛ " አውራን እንዳሉትም ይነገራል። ለዚህም ነው እንደ ባርያ እንዲሸጡ የተፈረደባቸው።

ዛሬ የኢሮብ ህዝብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለሻአቢያም እንዲሁም ለህውሓትም ግልጽ የሆነ መልእክት አስተላልፏል። እኛ ኢትዮጵያውያን እንጂ ኤርትራውያን አይደለንም። አራት ነጥብ ብለው ወስነው እርግጡን ተናግረዋል። በሌላም በኩል በዛሬው ዕለት በዓዲግራት ከተማ የሚኖሩ የኢሮብ ነገድ አባላት ታሪካዊ የሆነ ኃይለኛ ስብሰባ ከማካሔድ አልፈው በቀጣይም ለሚያደርጉት ትግል በከተማ ደረጃ 9 ኣባላት ያለው ኣስተባባሪ ኮሚቴ በማቋቋም ሰብሰባቸውን አጠናቅቀዋል።

የኢሮብ ህዝብ በየትኛውም ክፍለ ዘመንና በየትኛውም የታሪክ አጋጣሚ የኤርትራ አካል ሆኖ ኣያውቅም "ኢሮብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም አይደለም" ።

እናም ጎበዝ ይኼን እንደ ወልቃይት ፣ እንደ ጠገዴ፣ እንደ ራያና እንደ አላማጣ ህዝብ በግድ ትግሬ ነህ ተብሎ የህውሓት በትር የሚያርፍበትን ህዝብ ቢያንስ በሞራል ከጎኑ ልንቆም ይገባል።

ነገዱን ሁለቱ ሻአቢያና ህውሓት በረቀቀ ጥበብ ሊያስወግዱት የሚፈልጉት ነገድ ነው። እናም ይኽን ከፍተኛ የህልውና አደጋ ውስጥ ገብቶ ያለውን የኢሮብ ውሁድ ነገድ ለማዳን ድምፅ እንሁናቸው።

-ትግራይ ውስጥ "ኩናማ " ምዕራብ ትግራይ ሸራሮ አካባቢ እስከ ተከዜ ወንዝ በስፋት ይገኛል
-አሳሁርታ/ሳሆ/ቢሄረሰብ ከአክሱም ሰሜን ከራማ ምዕራብ እስከመረብ ወንዝ በስፋት ይገኛል
-ኢሮፕ አዲግራት ጉሎመከዳ አውራጃ እስከ አሲምባ ተራራ ድረስ ይገኛል ።

በጣም የሚያሳዝነው እነዚህ ታላላቅ ቢሔረሰቦች የራሳቸው ልዩ ዞን የላቸውም በቋንቋቸው አይማሩም እንደኔ እንደእኔ አዲግራት የኢሮፓውያን ዋና ከተማ መሆን አለባት አክሱም የአሳውርታዎች ሸራሮ የኩናማ ዋና ክልላዊ ከተማ መሆን አለባቸው ታዲያ የእውነት ፍትህ ካለ ነው::

ቀጣይ ትግራይ ውስጥ ያለንማንነቱ እየተጨፈለቀ ስላለው

"ዋጅራት ብሔረሰብ "በቅርቡ ይጠብቁን።

#ልሣነ-ዐማራ
#Amharapress

የራያ እና የወልቃይት የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄን አስመልክቶ ከሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) የተሰጠ መግለጫ




~"ራያ ቀደም ሲል በወሎ ጠቅላይ ግዛት ውሰጥ የነበረ ሲሆን ከ1985 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ተጠቃሎ በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ክልል አስተዳደር ስር ይገኛል፡፡ ይህንን ተከትሎ ለበርካታ አመታት በቋንቋቸውና በባህላቸው የመታወቅ ብሎም የመጠቀም፣ የማዳበር እና የማስፋፋት ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው እንደተጣሰ በአዲስ አበባ የሚገኙ የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሰመጉ አስረድቷል"


~"በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ ዜጐች በአማርኛ ቋንቋ እንዳይነጋገሩና የአማርኛ ሙዚቃ እንዳይሰሙ እየተከለከሉ ነው፤ ይህንን ትዕዛዝ ጥሶ የተገኘ ሰው እየተደበደበና እየታሰረ ይገኛል"

(ጥቅምት 16 ቀን 2011 ዓ.ም)

በትግራይ ክልል አላማጣ ከተማ የራያን ህዝብ የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ይዘው ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓም ሰልፍ በወጡ ዜጐች ላይ የክልሉ ልዩ ኃይል በወሰደው የሃይል እርምጃ ቢያንስ 9 ሰዎች በጥይት ተመተው መገደላቸውን፤ 16 ወጣቶች በጥይት መቁሰላቸውን፤ እንዲሁም ከ50 በላይ ወጣቶች እየተደበደቡ ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ለሰመጉ አረጋግጠዋል፡፡ በተጨማሪም ከ500 በላይ የሚሆኑ የአላማጣ ወረዳ ወጣቶች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው በቆቦ ከተማ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ ከተገደሉት ሰዎች መካከል፡

1)ነጋሲ እዮብ
2)ካሳ ንጉስ
3) መሀመድ ዋከዬ
6) ሞላ አብርሃም እንደሚገኙበት የሰመጉ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ራያ ቀደም ሲል በወሎ ጠቅላይ ግዛት ውሰጥ የነበረ ሲሆን ከ1985 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ተጠቃሎ በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ክልል አስተዳደር ስር ይገኛል፡፡ ይህንን ተከትሎ ለበርካታ አመታት በቋንቋቸውና በባህላቸው የመታወቅ ብሎም የመጠቀም፣ የማዳበር እና የማስፋፋት ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው እንደተጣሰ በአዲስ አበባ የሚገኙ የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሰመጉ አስረድቷል፡፡ የራያ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ለሰመጉ እንደገለፁት ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ እየተፈፀሙ ያሉ የመብት ጥሰቶችን ለጠቅላይ ሚንስትር ቢሮ እና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ ቢያሳውቁም መንግስት ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት በመንፈጉ ችግሩ ተባብሶ እዚህ ደረጃ ደርሷል፡፡

ራያ አላማጣ


የፌደራል መንግስት የራያ ህዝብ ያነሳውን ህገ- መንግስታዊ የማንነት ጥያቄ እና ከጥያቄው ጋር ተያይዞ እየተከሰቱ ያሉትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በሰከነ ሁኔታ ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በተከተለ መንገድ እንዲፈታ ሰመጉ ይጠይቃል፡፡ በተጨማሪም መንግስት ከራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የዜጐችን በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነት እና የነፃነት መብቶች ላይ ጥሰት የፈፀሙ እና ያስፈፀሙ አካላትን አጣርቶ ለፍርድ እንዲያቀርብ ሰመጉ ይጠይቃል፡፡

በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) ከዚህ ቀደም ”በኢ.ፌዲሪ ሕገ-መንግስት መሠረት የማንነት ጥያቄ በሚያነሱ ዜጐች ላይ የሚፈጸመው ግድያ፣ ሕገወጥ እስራት፣ አፍኖ መሠወር፣ ማፈናቀልና ንብረት መንጠቅ በአስቸኳይ ይቁም” በሚል ርዕስ 141ኛ ልዩ መግለጫውን ግንቦት 24 ቀን 2008 ዓም ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ሰመጉ በመግለጫው የመጀመሪያ ክፍል የአማራ ብሔረተኝነት የማንነት ጥያቄ በማንሳታቸው ምክንያት 34 የወልቃይት ተወላጆች መገደላቸውን፣ 93 ሰዎች ታፍነው የደረሱበት አለመታወቁን ጨምሮ በተለያዩ ሰዎች ላይ ድብደባ ማሠቃየት፣ ሕገ ወጥ እስራቶች መፈፀሙን እና የእርሻ መሬት፣ መኖሪያ ቤትና ንብረታቸውን መነጠቃቸውንና ዜጎች መፈናቀላቸውን ዘርዝሯል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የወልቃይትን ሕዝብ የማንነትና የታሪክ ጥያቄ ለማጥፋት የአካባቢውን ነባር የቦታ ሥያሜዎች በአዲስ ሥያሜዎች መቀየራቸውን የኮሚቴው አባላት መግለፃቸውን ጠቅሶ ሰመጉ በሪፖርቱ ይፋ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ከ141ኛ ልዩ መግለጫ በኋላም የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የአማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ በተለያዩ ጊዜያት በወልቃይት ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ለሰመጉ ሲያመለክቱ ቆይተዋል፡፡

ጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የአማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ለተለያዩ ለሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማትና ለኤምባሲዎች የተነጠቀ የአማራ ማንነታችን እንዲመለስልን ለ6ኛ ጊዜ የቀረበ አቤቱታ በማለት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡ ኮሚቴው ከ1974 ዓም ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ግፍና በደል ሲፈፀምበት ቢቆይም ለሕዝቡ ጩኸት መንግስት የሚጠበቅበትን ምላሽ እንዳልሰጠ አስረድቷል፡፡ የሕዝቡን ጥያቄ ለማፈን እያጋጠሙ ያሉ ወቅታዊ ችግሮች ናቸው በማለት ኮሚቴው በአቤቱታው ላይ ከዘረዘራቸው ችግሮች መካከል፤



ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ኮሚቴ አባላትን በፀረ ሽብር ሕግ በመክሰስና በማሰር ከቆየን በኋላ መንግስት ለሰላም ሲል በወሰደው እርምጃ ከእስር የተፈታን ቢሆንም አሁንም የኮሚቴው አባላት በየሄዱበት እየታሰሩ ነው፤ ሌሎች አባላትም ወደ ቤታቸው እንዳይመለሱ ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸዉ በስደት ላይ ይገኛሉ፤

ከዚህም በተጨማሪ በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ ዜጐች በአማርኛ ቋንቋ እንዳይነጋገሩና የአማርኛ ሙዚቃ እንዳይሰሙ እየተከለከሉ ነው፤ ይህንን ትዕዛዝ ጥሶ የተገኘ ሰው እየተደበደበና እየታሰረ ይገኛል፤

ነሐሴ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ በወልቃይት ጠገዴ የሚገኙ ወጣቶችና እና የማንነት ጥያቄ የሚያቀርቡ አዛውንቶች እየተደበደቡና እየታሰሩ እንዲሁም ከአካባቢያቸዉ እንዲሰደዱ እየተደረገ ይገኛል፡፡

በተለይ በአሁኑ ሰዓት ጥያቄያችንን ለማዳፈን የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ:: በዚህም ምክንያት ሕይወታችንና እንደ ህዝብ የመቀጠል ህልውናችን አደጋ ውስጥ ገብቷል በማለት የወልቃይት ህዝብ የማንነት ጠያቂ ኮሚቴ አባላት ለሰመጉ በአካል ቀርበው አመልክተዋል፡፡ በዚህም መሠረት የወልቃይት ጠገዴን ሕዝብ አካባቢውን ጥሎ እንዲሰደድ የተለያዩ ጫናዎች እየተፈፀሙባቸው እንደሚገኝና የመከላከያ ሃይልና የፌዴራል ፖሊስ በቦታው ተሰማርቶ ከተጋረጠብን ከፍተኛ የአደጋ ስጋት ሊጠብቀን ይገባል ብለዋል፡፡

ሰመጉ የፌዴራል መንግስት ለወልቃይት ህዝብ የማንነት ጥያቄ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከር በአስቸኳይ ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ፤ እንዲሁም የሰው ህይወት ያጠፉ፣ አካል ያጎደሉና ንብረት ያወደሙ አካላትን በአስቸኳይ ለህግ እንዲያቀርብ፤ ለተጐጂዎች ተመጣጣኝ ካሳ እንዲከፈልና የተፈናቀሉ ሰዎችን መልሶ በማቋቋም ወደቀያቸው እንዲመልስ፤ ለደህንነታቸውም ዋስትና እንዲሰጥ አጥብቆ ይጠይቃል፡፡

በአጠቃላይ ባለፉት አመታት የራያ እና የወልቃይት ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም የማንነት እና እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄን በስፋት ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ ለእነዚህ የማንነት ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ መስጠት አስቸጋሪ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የሁሉንም የፖለቲካ አካላት እና የዜጎችን ገንቢ ተሳትፎ ማረጋገጥ ለሀገር አንድነት ወሳኝ መሆኑን ሰመጉ ይገነዘባል፡፡ በመሆኑም ለአመታት በአፈሙዝ ተዳፍነው የቆዩ ጥያቄዎችን በጥይት ሳይሆን በሕግ እና በስርዓት መፍታት ለዜጐች ሁለንተናዊ መብቶች መከበር ብቸኛው አማራጭ መሆኑን በመገንዘብ መንግስት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ ሰመጉ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም፤ መንግስት ለሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንዲሁም ለህግ የበላይነትና የፍትሕ ስርዓቱን ለማሻሻል የገባውን ቃል እንዲተገብርና የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲ መብቶችን እንዲያከብርና እንዲያስከብር ሰመጉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

የአማራ ሕዝብና ግዛት አንድነትና ኢተነጣጣይነትን ከማስከበር ጋር በተያያዘ ከአብን የተሰጠ መግለጫ



የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ–አብን ከሚታገልላቸውና ትግሉ የሚጠይቀውን መስዕዋትነት ሁሉ ለመክፈል ከዝግጁም በላይ ከሆነባቸው የአማራ ሕዝብ የኅልውና ጥያቄዎች ውስጥ የመጀመሪያው የአማራን ሕዝብና ግዛት አንድነትና ኢተነጣጣይነት ተፈጥሯዊ መብቱን ማስከበር ነው።
አማራ ጠል ኃይሎች ወደ ትግል ሲገቡ ጀምረው የአማራውን ሕዝብ በጠላትነት ፈርጀው የተነሱ፥ ይህንን የአማራ ጥላቻቸውን በትግል ሰነዳቸው ሳይቀር አካተው ሲታገሉ ኖረው በለስ ቀንቷቸው አገራዊ ሥልጣን ሲቆናጠጡ፥ አስቀድሞ የነበራቸውን የአማራ ጥላቻ መንግስታዊና ተቋማዊ ቅርፅ በመስጠት ሥርዓትና ሥሪት እንዲሆን አድርገዋል። አማራ ጠል ብሔርተኛ የፖለቲካ ኃይሎች አማራውን በነጠለና ባገለለ መልኩ፥ የአማራ ሕዝብ እንደሕዝብ ሳይሳተፍ፣ ሳይፈቅድና ይሁንታውንም ሳይሰጥ፤ ለበርካታ ሺህ ዓመታት የኖረባቸው ታሪካዊ ርስቶቹ በፖለቲካ ውሳኔ ወደ ተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች እንዲካለሉ ተደርጓል።
የአማራ ታሪካዊ ርስቶች ወደ ተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች ከተካለሉ በኋላም ልዩ ልዩ የሰፈራ ፕሮግራሞችን በመንደፍ ዴሞግራፊያዊ አለመመጣጠን እንዲፈጠር በማድረግ ነባር አማራዋችን የመዋጥ እና መሰልቀጥ ሁኔታዎች ከመኖራቸውም በላይ የየግዛቶች ታሪካዊ ባለቤት የሆኑትን አማራዎች ስልታዊ በሆነ መንገድ ቁጥራቸውን በመቀነስ የዘር ማሳሳት፣ ያለፈቃዳቸውና በተፅዕኖ ወደ ተካለሉባቸው አስተዳደሮች ማንነታቸውን የማስቀየር የማንነት ገፈፋ፣ የማንነት መገለጫዎቻቸውን እንዳያዳብሩና እንዳይጠቀሙ አፈናና ጫና በማሳደር የማንነት ቅየራ፣ አፋኝ ቢሮክራሲ በመፍጠር ተማረው እንዲሳደዱ ማድረግ፣ ማንነታችን ይከበርልን ጥያቄ ለምን አነሳችሁ የሚል ጅምላ እስር፣ ድብደባ፣ ዘር ማጥራት፣ በአማራነታቸው የማሸማቀቅና የመነጠል ኢሰብአዊ ድርጊቶች ተፈፅሞባቸዋል፤ አሁንም ድረስ ቀጥሏል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በተለይ በወልቃይት፣ ራያና መተከል ታሪካዊ ርስቶችና በእነዚህ ርስቶች በሚኖሩ አማራ ወገኖች ላለፉት 27 ዓመታት የታየው ዘር ማጥፋትና ፍጅት መቆም አለበት ብሎ ያምናል። መፍትሔውም በፖለቲካ ውሳኔ የተወሰዱ የአማራ ርስቶችና አማራ ወገኖች ወደ ነባራዊ የአማራ አስተዳደር በተወሰዱበት አግባብ በፖለቲካ ውሳኔ መመለስ ብቻ መሆኑን በአንክሮ ይገነዘባል። ከዚህ በተቃራኒ ትናንት ጥቅምት 23/2011 ዓ/ም የኢፌዴሪ መንግስት ከወሰንና ማንነት ጋር ተያያዥ ጥያቄዎችን ለመመለስ ገለልተኛ አጥኚ ኮሚቴ ማቋቋሙን በፌዴሬሽን ምክርቤት በኩል ይፋ አድርጓል። አብን የኢፌዴሪ መንግስትን አካሄድ አምርሮ ያወግዛል። ከማውገዝም ባለፈ መላውን የአማራ ሕዝብ ከጫፍ ጫፍ በማነቃነቅ በጽናት የሚታገለው መሆኑንም ይገልፃል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ–አብን የኢፌዴሪ መንግስት ከወሰንና ማንነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን በገለልተኛ አጥኚ ኮሚቴ ለመፍታት ያስቀመጠውን አቅጣጫ የሚቃወምባቸው ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው።
1) የአማራ ሕዝብ ታሪካዊ ርስቶች ባለቤት የአማራ ሕዝብ ነው። ይህ ኃቅ ተገርስሶ የአማራ ሕዝብ ሳይጠየቅ፣ ሳይሳተፍና ይሁንታውንም ሳይሰጥ በኃይልና በፖለቲካ ውሳኔ ወልቃይት፣ ራያና መተከልን ጨምሮ የተለያዩ የአማራ ሕዝብ ርስቶች ወደ ተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች ተካለዋል። የተወሰዱ ርስቶች በኃይልና በፖለቲካ ውሳኔ የተደረጉ እንጂ በሕግና ኮሚቴ በማዋቀር በጥናት ስላልሆነ የተወሰዱ ርስቶችና ወገኖቻችን በተመሳሳይ መልኩ በፖለቲካ ውሳኔ ወደ ነባራዊ የአማራ አስተዳደር እንዲመለሱ ከማድረግ ውጭ ያለውን አካሄድ ሁሉ አብንም ሆነ መላው የአማራ ሕዝብ አይቀበለውም።
2) የፌዴሬሽን ምክርቤት የተቋቋመው ጥያቄ የሚቀርብባቸው የአማራ ርስቶችና ወገኖች በፖለቲካ ውሳኔ ወደ ተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች ከተካለሉ በኋላ ነው። ይኸው መንግስታዊ ተቋም ለበዳይ ወገን ባደላ መልኩ ጥያቄያቸውን በሰላማዊ መንገድ ሲያቀርቡ በነበሩ ወገኖች መከራና ሲቃይ ሲያላግጥ የኖረ ነው። ይባስ ብሎም ፌዴሬሽኑን በአፈጉባዔነት የሚመሩት ግለሰብ ሕገወጡን የአማራ ርስቶች ቅርምትና በአማራ ወገኖች ላይ የደረሰውን የዘር ማጥፋት በጠንሳሽነት ያስፈፀመው ሕወኃት የሥራ አስፈፃሚ አባል በመሆናቸውና በቅርቡም ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ ለአንድ ወገን ባደላ መልኩ «ራያም ሆነ ወልቃይት መሬቱም ሆነ ሕዝቡ የትግራይ ነው» የሚል መግለጫ የሰጡ በመሆናቸው፥ በተለይ ከዚህ ጋር የተያያዙ የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎችን በገለልተኝነት ይመራሉ ብለን አናምንም። ስለሆነም ከሕገመንግስት መጽደቅና መሰል ጥያቄዎችን ለመፍታትም መንግስታዊ ተቋም ከመደራጀቱ በፊት የፖለቲካ ውሳኔ ተወስኖ በኃይል ወደ ተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች የተካለሉ አማራ ወገኖቻችንም ሆኑ ርስቶቻችን በኮሚቴ ይመለሳሉ ብለን ስለማናምን የመንግስትን ውሳኔ አንቀበለውም።
3) የኢፌዴሪ መንግስት አማራው የሕዝብና ግዛት አንድነትና ኢተነጣጣይነት ተፈጥሯዊ መብቱ እንዲከበርለት ያነሳውን የኅልውና ጥያቄ ለመፍታት ዳተኝነት ከማሳየቱም በላይ ጉዳዩን እልባት ለመስጠት እየሄደበት ያለው መንገድ ለጨቋኝና ጭቆና ውግንና የመቆም ያህል ነው። መንግስት የወልቃይት፣ ራያና መተከል ጉዳይ የመላው የአማራ ሕዝብ ጉዳይ መሆኑን ሆነ ብሎ በመርሳት በገለልተኛ አጥኚ ኮሚቴ ሽፋን ዛሬም የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን የአማራ ሕዝብ ባላሳተፈና ባገለለ መልኩ እያደረገ ያለው አካሄድ ፈፅሞ ተቀባይነት የለውም። አብን ለዚህን ዓይነት መንግስታዊ አካሄድ ፈፅሞ እውቅና አይሰጥም። የተሳሳተውን የመንግስት አካሄድም መላ ሕዝባችንን አስተባብረን አምርረን በጽናት የምንታገለው ይሆናል። የመንግስት አካሄድ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን የአማራ ሕዝብ ያገለለ ስለሆነ አንቀበለውም።
በአጠቃላይ የኢፌዴሪ መንግስት እየሄደበት ያለው መንገድ ከአገራዊ አንድነትና የሕዝብ ለሕዝብ መተማመን ይልቅ አገርን የሚያፈርስና ጥርጣሬን የሚያነግስ፣ ላንድ ወገን ያደላና አማራውን ነጣይነ አግላይ በመሆኑ፤ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ–አብን እንደማይቀበለው ያሳውቃል። ንቅናቄያችን የአማራ ሕዝብ የሕዝብና ግዛት አንድነትና ኢተነጣጣይነት ተፈጥሯዊ መብቱን ለማስከበር ባለፉት 27 ዓመታት ካደረገው ትግል የከፋና መራር ትግልም ከፊቱ እንደተደቀነ ይገነዘባል። ስለሆነም ሁሉም አማራ የኅልውና አደጋውን ለመቀልበስና የአማራን ሕዝብ ኅልውና ለማስቀጠል ትግሉን በባለቤትነት ጭምር ይዞ እንዲመራ ከአብን ጎን እንዲሰለፍ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፥ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!
አማራ በልጆቹ ትግል ታሪኩን ያድሳል!
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ–አብን
ጥቅምት 24/2011 ዓ/ም
አዲስ አበባ፥ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

በሶማሌ ክልል ለመፍጠር የታቀደው ቀውስ ከሸፈ











  በጄነራል አብረሃም ወልደማርያም (ኳርተር) እና በጄነራል ገብሬ ዲላ የታቀደው ቀውስ መክሸፉን የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ገለጹ።

ፕሬዝዳንቱ አቶ ሙስጠፋ ዑመር ለኢሳት እንደገለጹት በህወሀት ጄነራሎች የሚመራው የኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ኔትወርክ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ በሰፊው እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ተደርሶበታል።


ሰሞኑን በእነዚሁ የህውሀት ጄነራሎች አስተባባሪነት በተፈጠረ ቀውስ የሁለት ሰዎች ህይወት መጥፋቱን ለማወቅ ተችሏል።

በጄነራል አብረሃምና ጀነራል ገብሬ የሚመራው ኔትወርክ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎችን ይዞ ለውጡን ለመቀልበስ የተዘጋጀ ቢሆንም የክልሉ መንግስት በወሰደው እርምጃ እቅዱ መክሸፉን አቶ ሙስጠፋ ገልጸዋል።

በቀውስ ፈጣሪ ኔትወርክ ውስጥ የቀድሞ የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ ዒሌ እናት እንደሚገኙበትም ታውቋል።
ከጂጂጋ ሰሞኑን የሚሰማው ነገር ጥሩ አልነበረም።
ኢሳት ወደ አካባቢው በመደወል ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደሚሉት የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል በወሰደው ርምጃ አንድ ሰው መገደሉን ተከትሎ ስጋት ውስጥ ገብተዋል።
በሌሎች አከባቢ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ዳግም ሊፈጸም ይችላል በሚል ህዝቡ በቤተክርስቲያን አካባቢ መሰባሰቡን ነው ያነጋገርናቸው የሚገልጹት::

የሰሞኑ ቀውስ መነሻው የተደራጁና ገንዘብ የተከፈላቸው ወጣቶች በሌሎች አካባቢ ተወላጆች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ሲሆን የክልሉ ፕሬዝዳንት በግል ገጻቸው የዘር ጥቃት በክልላችን ቦታ የለውም ሲሉ አውግዘዋል።
በጂጂጋ የተፈጠረውን የሰሞኑን ቀውስ በተመለከተ ኢሳት ያነጋገራቸው የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፋ ዑመር ጄነራል አብረሃም ወልደማርያም ኳርተርና ጄነራል ገብሬ ዲላ የሚመሩትና ለዓመታት በኮንትሮባንድ ንግድ የተሳሰረው ኔትወርክ ከቀውሱ ጀርባ እጁ አለበት ብለዋል።

እነዚህ የህወሃት ጄነራሎች ከቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ዒሌ ተከታዮች ጋር በመሆን በሶማሌ ክልል የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ለመቀልበስ እቅድ ነድፈው እየሰሩበት መሆኑ ተደርሶበታል።

አቶ ሙስጠፋ እንደሚሉት ጄነራሎች የሚመሩት የኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ኔትወርክ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ስራ አጥ የሆኑ ወጣቶችን አሰማርተው የሰሞኑ ጥቃት እንዲፈጸም አድርገዋል።

ከ10ሺህ እስከ 50ሺ ብር ድረስ ለተደራጁት ወጣቶች በተናጠል ገንዘብ መመደቡም ታውቋል።
የአብዲ ዒሌ ወላጅ እናትም በዚሁ ቀውስ ውስጥ እጃቸው እንደሚገኝበት ነው አቶ ሙስጠፋ የገለጹት።
የህወሃት ጄነራሎች በሶማሌ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድ ከፍተኛ ሀብት ያካበቱ መሆናቸው ይነገራል።
ከሶማሌ ላንድ በጂጂጋ በኩል እስከ ጁባ የተዘረጋውን የኮንትሮባንድ ንግድ የሚመሩት ጄነራል አብረሃም ወልደማርያም ኳርተርና ጄነራል ገብሬ ዲላ ከአብዲ ዒሌ መታሰር በኋላ በክልሉ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውም ታውቋል።
አቶ ሙስጠፋ እንደሚሉትም እነዚህ ጄነራሎች አሁንም በሶማሌ ክልል ውስጥ ሆነው በጥቅም ከተሳሰሯቸው ነጋዴዎችና ባለሃብቶች ጋር በመሆን ለውጡን ለመቀልበስ እየሰሩ ቆይተዋል።

የክልሉ መንግስት የእነዚህ ለውጥ ቀልባሾች እቅድ ለማክሸፍ ርምጃ መውሰዱን የገለጹት አቶ ሙስጠፋ ከግጭቱ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማድረግ መጀመሩን ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ሰዓት በጂጂጋም ሆነ በመላው የሶማሌ ክልል አካባቢ ያንዣበበው አደጋ መቀረፉን የተናገሩት አቶ ሙስጠፋ የጄነራሎቹና የአብዲ ዒሌ የሽብር ዕቅድ ከሽፏል ብለዋል።

"ቤተ ክርስትያን በአማርኛ መስበክና መዘመር ተከልክሏል" ዲ/ን ላሊበላ ሙላው



"ቤተ ክርስትያን በአማርኛ መስበክና መዘመር ተከልክሏል"
ዲ/ን ላሊበላ ሙላው ( ለግዮን መፅሔት)
"ወልቃይት በአሁኑ ሰዓት በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለችው። አማርኛ መፅሐፍ ማንበብ፣ በአማርኛ መዝፈን፣ መፈከር፣ መሸለል፣ በአማርኛ ማውራትና በስልክ መነጋገር ተከልክሏል። የአማርኛ ፅሑፍ ያለባቸው ቲሸርቶችን መልበስ ተከልክሏል። የጠ/ሚኒስትር ዓብይ፣ ለማ መገርሳ፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የፋሲል ግንብ፣ የዐፄ ቴዎድሮስ ምስል ያለባቸውን አልባሳት የለበሰ ሰው እስራትና ግርፋት ነው የሚጠብቀው። ወልቃይት ላይ ቤተ ክርስትያን ውስጥ በአማርኛ እንዳይሰበክ ተከልክሏል። ታግዷል። ስብከት በትግርኛ እንዲሆን ተደርጓል። አማርኛ ተወግዟል ማለት ይቻላል።"

wanted officials