Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, November 8, 2018

"ያለማንነቱ በግድ በአጋሜዎች የተጨፈለቀው የኢሮቭ ብሔረሰብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም ኤርትራዊም አይደለሁም "አለ።







"ያለማንነቱ በግድ በአጋሜዎች የተጨፈለቀው የኢሮቭ ብሔረሰብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም ኤርትራዊም አይደለሁም "አለ።
-------------------------------------------------------------------
ኦሮባ – ኢሮብ – ‹‹ወደ ቤት ግቡ ›› ማለት ነው!


የኢሮብ ህዝብ በትግራይ ክልል ጉሎ መኸዳ ወረዳ የሚኖር፣ ራሱን የቻለና ትግርኛ ተናጋሪ ያልሆነም የራሱ የሆነ ማንነትና ቋንቋ ያለው: ኢትዮጵያዊ ነገድ ነው።

ኢሮብ በትግራይ ክልል፣ ምሥራቃዊ ዞን የሚገኝ ሲሆን በምሥራቅ አፋር፣ በሰሜን ደግሞ ኤርትራ ያዋስኑታል፡፡

ብዙዎቻችን የኢሮብን ህዝብ ልክ እንደ ህውሓት ወይም እንደ ትግሬ በመቁጠር ለጉዳዩ ትኩረት ሳንሰጥ እንዲሁ ስናላግጥ ውለናል።
የኢሮብ ህዝብ ልክ እንደ ወልቃይት ዐማራ በትግሬዎች የተዋጠ ነገድ ነው። ትግርኛ አይናገሩም። የራሳቸው ቋንቋና ባሕል ያላቸው። በታሪክ አጋጣሚ ግን ከባንዳዎች መሃል ሳንድዊች ሆነው የተገኙ ምስኪን ማህበረሰቦች ናቸው።

በ2007ዓም በተደረገው የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ መሠረት የኢሮብ ብሔረሰብ ብዛት ህውሓት አውቃ በሴራ ካልቀነሰችው በስተቀር 33407 እንደሆኑ ነው የማእከላዊ እስታስቲክስ መሥሪያቤት ሪፖርት የሚያመለክተው።

"ኢሮብ "የሚለው መጠሪያ ነገዱም ወረዳውም ይጠራበታል።

¶ ይህ ነገድ በውስጡ ሦስት ዓይነት ማኅበረሰቦች ያሉት ሲሆን :-

1•አንደኛው "ቡክናይታ" ይባላል፡፡

2•ሁለተኛው ማኅበረሰብ "ሀሳበላ" ይባላል።

3•ሦስተኛው ማኅበረሰብ ደግሞ "እንዳልገዳም" (አድጋዲ ዓረ) ይባላል፡፡

ህውሃቶች "ኢሮብን " ለኤርትራ ሽጠው ህዝቡን በወልቃይት ለማስፈር ነው ዋነኛ እቅዳቸው ። የትግሬ አንባገነኖች በግድ ከ50 ዓመት በላይ የተጨፍለቁት ኢሮቦች እንደ ዐማራው ህውሓት እንዲጠፍ ከወሰነችባቸው ነገዶች ውስጥ ቀዳሚ ናቸው ።

ይህ ነገድ ልክ እንደወልቃይት ዐማራ በትግራዮች በግድ ማንነቱን ነጥቀው እንዲጠፋ የተፈረደበት ምስኪን ነገድ ነው።

"ሳሆ ብሔረሰብ"
ከኢሮብ ህዝብ ከሚናገረው ቋንቋ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቋንቋ ያለው ነገድ" ሳሆ "በመባል የሚታወቀውና አሁን በኤርትራ ግዛት ውስጥ የሚገኝ ብሔር ብቻ ነው።

" የኢሮብና የሳሆን ብሔረሰቦች" የሚለያያቸው የሚከተሉት እምነትና የኢኮኖሚ መሰረታቸው ብቻ ነው።

በአፋር ግዛት አካባቢ የሚገኙ የኢሮብ ነገድ አባላት ናቸው። ቋንቋቸው ግን አንድ ነው።

የኢሮብ ህዝብ እኔ ነኝ ያለ አራሽ ገበሬ ነው፡፡ ልክ በደቡብ ኢትዮጵያ እንደሚኖሩት " የኮንሶ" ነገዶች ተራራውን በእርከን አሳምረው ምርት የሚያፍሱ ታታሪ ገበሬዎች ናቸው ኢሮቦች።

እነ "ኢህአፓ" የትጥቅ ትግላቸውን ሲጀምሩ በኢሮብ አካባቢው ካሉት ተራሮች መካከል " አሲምባ " የሚባለውን ተጠግተው ነበር የትጥቅ ትግላቸውን የጀመሩት። ኋላ ላይ ህውሓት አርዳ በልታ ድራሻቸውን አጠፋቻቸው እንጂ። ከመታረድ የተረፉትን እነ ተፈራ ዋልዋ ፣ እነ በረከት ስምኦን ፣ እነ አዲሱ ለገሰን በራሷ አምሳል " አራጅ " አድርጋ እስክትፈጥራቸው ድረስ የኢሮብን ህዝብ ቀለብ ተሻምተው የሚበሉ ነበሩ። ኢሮብ ለበድኑ ብአዴንም ባለውለታ ነገድ ነው።

"ዳውሃን "የኢሮብ ነገድ ዋና ከተማ ሲሆን፤ ኢትዮ አሜሪካዊው 6 ተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ኢትዮጵያዊው አትሌት ምሩጽ ይፍጠርም የኢሮብ ነገድ አባላት ናቸው። ነፍሱን ይማረውና ምሩጽ በደህና ጊዜ ይህን ጉድ ሳይሰማ አርፏል። ይብላኝ ለቅዱስ ፓትሪያርኩ አይናቸው እያየ ነገዳቸው በቁሙ ተሽጦ ኤርትራዊ ነህ ለተባለው።

ይኽ ነገድ ባለፉት 50 ዓመታት የአካባቢው የተፈጥሮ ሁኔታና የትግራይ ትግሪኝ የፖለቲካ ኤሊቶች ኅብረት ፈጥረው ከምድረ ገጽ ድምጥማጡን ሊያጠፉት የወሰኑበት አሳዛኝና ምስኪን ሀዝብ ነው። ኢሮብ በሰሜናዊ ምስራቅ ትግራይ የሚኖር ብሔረሰብ ነው።

ሻአቢያና ህውሓት ደግሞ ይኼንን ብሔር በኢትዮጵያዊነቱና ኢትዮጵያዊነቱን በማቀንቀኑ ይጠየፉታል። አሁን ግን በሁለቱ ምክክር ከነ አካቴው ህውሓትና ሻአቢያ ተባብረው ድምጥማጡን ለማጥፈት የወሰኑና የቆረጡ ይመስላል።

ተመልከቱ አንድም የትግሬ ህውሓት ባለሥልጣን ወጥቶ ከጎናቸው ሊቆም አልፈቀደም። የራያ ዐማራውና ፆታውን ቀይሮ ህውሓት የሆነው ደፋሩ ጌታቸው ረዳ ሊያናግራቸው በኼደ ጊዜ የኢሮብ አባላት " ትግርኛ ስለማንሰማ በዐማርኛ " አውራን እንዳሉትም ይነገራል። ለዚህም ነው እንደ ባርያ እንዲሸጡ የተፈረደባቸው።

ዛሬ የኢሮብ ህዝብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለሻአቢያም እንዲሁም ለህውሓትም ግልጽ የሆነ መልእክት አስተላልፏል። እኛ ኢትዮጵያውያን እንጂ ኤርትራውያን አይደለንም። አራት ነጥብ ብለው ወስነው እርግጡን ተናግረዋል። በሌላም በኩል በዛሬው ዕለት በዓዲግራት ከተማ የሚኖሩ የኢሮብ ነገድ አባላት ታሪካዊ የሆነ ኃይለኛ ስብሰባ ከማካሔድ አልፈው በቀጣይም ለሚያደርጉት ትግል በከተማ ደረጃ 9 ኣባላት ያለው ኣስተባባሪ ኮሚቴ በማቋቋም ሰብሰባቸውን አጠናቅቀዋል።

የኢሮብ ህዝብ በየትኛውም ክፍለ ዘመንና በየትኛውም የታሪክ አጋጣሚ የኤርትራ አካል ሆኖ ኣያውቅም "ኢሮብ ኢሮብ እንጅ ትግሬም አይደለም" ።

እናም ጎበዝ ይኼን እንደ ወልቃይት ፣ እንደ ጠገዴ፣ እንደ ራያና እንደ አላማጣ ህዝብ በግድ ትግሬ ነህ ተብሎ የህውሓት በትር የሚያርፍበትን ህዝብ ቢያንስ በሞራል ከጎኑ ልንቆም ይገባል።

ነገዱን ሁለቱ ሻአቢያና ህውሓት በረቀቀ ጥበብ ሊያስወግዱት የሚፈልጉት ነገድ ነው። እናም ይኽን ከፍተኛ የህልውና አደጋ ውስጥ ገብቶ ያለውን የኢሮብ ውሁድ ነገድ ለማዳን ድምፅ እንሁናቸው።

-ትግራይ ውስጥ "ኩናማ " ምዕራብ ትግራይ ሸራሮ አካባቢ እስከ ተከዜ ወንዝ በስፋት ይገኛል
-አሳሁርታ/ሳሆ/ቢሄረሰብ ከአክሱም ሰሜን ከራማ ምዕራብ እስከመረብ ወንዝ በስፋት ይገኛል
-ኢሮፕ አዲግራት ጉሎመከዳ አውራጃ እስከ አሲምባ ተራራ ድረስ ይገኛል ።

በጣም የሚያሳዝነው እነዚህ ታላላቅ ቢሔረሰቦች የራሳቸው ልዩ ዞን የላቸውም በቋንቋቸው አይማሩም እንደኔ እንደእኔ አዲግራት የኢሮፓውያን ዋና ከተማ መሆን አለባት አክሱም የአሳውርታዎች ሸራሮ የኩናማ ዋና ክልላዊ ከተማ መሆን አለባቸው ታዲያ የእውነት ፍትህ ካለ ነው::

ቀጣይ ትግራይ ውስጥ ያለንማንነቱ እየተጨፈለቀ ስላለው

"ዋጅራት ብሔረሰብ "በቅርቡ ይጠብቁን።

#ልሣነ-ዐማራ
#Amharapress

No comments:

Post a Comment

wanted officials