Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, October 27, 2018

ከንግስት ዘውዲቱ ወዲህ የመጀመሪያዋ እንስት ፕሬዝዳንት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ሆኑ


 አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት በመሆን በዛሬው እለት ተሰየሙ።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው ስነ ስርአት የኢፌዴሪ 4ኛ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዲፕሎማትነት የረዥም አመታት ልምድ አዳብረዋል።

ከንግስት ዘውዲቱ ወዲህ የመጀመሪያዋ እንስት ርዕሰ ብሔርም ሆነዋል።
በ1942 አዲስ አበባ ከተማ የተወለዱትና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት የተከታተሉት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ከፍተኛ ትምህርታቸውን በፈረንሳይ ሞንተሌ ዩኒቨርስቲ ተከታትለዋል።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በተፈጥሮ ሳይንስ የወሰዱት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣በተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአለም አቀፍ ግንኙነት ስልጠና መውሰዳቸውም በፓርላማው በተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ላይ ተመልክቷል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥሎ ሁለተኛዋ የሴት አምባሳደር በመሆን ያገለገሉትና በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ የሴት ፕሬዝዳንት የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ በጅቡቲ፣በፈረንሳይና በተለያዩ ሃገራት የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን አገልግለዋል።
በአፍሪካ ህብረትና በኢጋድ የኢትዮጵያ ተወካይ እንዲሁም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዳይሬክተር በመሆንም አገልግለዋል።
በቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪሙን በኬንያ የተባበሩት መንግስታት ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣በአዲሱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኖዮ ጉተሬዝ በአፍሪካ ሕብረት የተባበሩት መንግስታት ተወካይ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት የተባበሩት መንግስታት ቢሮ ሃላፊ ሆነው ማገልገላቸውንም ከሕይወት ታሪካቸው መረዳት ተችሏል።
የ69 አመቷ ዲፕሎማት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሁለት ወንድ ልጆች እናት እንደሆኑም ታውቋል።
ለሚቀጥሉት 6 አመታት የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾሙት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ላለፉት 5 አመታት በፕሬዝዳንትነት ካገለገሉት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ዛሬ በይፋ የፕሬዝዳንትነቱን ስልጣን ተረክበዋል።
በበአለ ሲመታቸው ላይ ባደረጉት ንግግር ለሃገሪቱ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉና የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንደሚያግዙም ቃል ገብተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ የአዲስ አባባ ንግድ ምክር ቤት ባካሄደው ምርጫ ወይዘሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ወይዘሮ መሰንበት ሸንቁጤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት በኋላም የአባይ ባንክ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል።

Women taking bigger roles as parliament elects first female president in modern history


Amb. Sahle-Work Zewde, Ethiopian President

The government of a reformist Prime Minister in Ethiopia, which had appointed half women in its cabinet last week, has elected a female as the country’s president.
Ethiopia’s bicameral parliament today appointed Sahle-Work Zewde, a career diplomat that served her country as an ambassador and later with the United Nations in different capacities.
She told MPs that one of her priorities as president of the country was to be a role model for girls and women, and support Prime Minister Abiy Ahmed’s government reforms, especially in bringing more women to leadership roles.
Sahle-Work Zewde, 68, is the first female head of state in a century. Empress Zewditu, daughter of Menelik II, who reigned from 1916 to 1930, was the first female head of state in Africa.
The sweeping change towards gender parity in government positions is widely admired and considered as a bold move by the government of Abiy Ahmed in the otherwise patriarchal and conservative country.
“In a patriarchal society such as ours, the appointment of a female head of state not only sets the standard for the future but also normalizes women as decision-makers in public life,” tweeted Fitsum Arega, Ahmed’s chief of staff.
Before annointed as president of Ethiopia, Ambassador Zewde has served Special Representative of United Nations Secretary-General António Guterres to the African Union and Head of the United Nations Office to the African Union at the level of Under-Secretary-General of the United Nations.
The french educated diplomat had served as ambassador of Ethiopia to France, Djibouti and Senegal among others.
Zewde will be Africa’s only female head of state currently holding office.

Abiy Ahmed to visit Europe to meet leaders, Ethiopian community





Continuing his global tour to lift his country’s image, Ethiopia’s young Prime Minister will tour Europe to attend the G20 Compact with Africa conference, meet European leaders and a big Ethiopian community in Europe.
Dr. Ahmed will first travel to Paris on Monday to meet with French President Emmanuel Macron. In July, Macron extended an invitation to Ahmed to visit his country.
He will then head to Germany, where he will attend the G20 Compact with Africa (CwA) conference in Berlin.
The G20 Compact with Africa was initiated under the German G20 Presidency to promote private investment in Africa, including in infrastructure. It brings together reform-minded African countries, according to the CwA website.
While in Germany, Abiy Ahmed will held talks with chancellor Angela Merkel on trade, economic and social issues and issues of bilateral interest, according to the Ethiopian consulate in Frankfurt.
On Wednesday, the Prime Minister is expected to address about 20,000 Ethiopians at an event in Frankfurt, who will come from all over Europe.
Abiy Ahmed’s first visit to the United States at the end of July drew the gathering of tens of thousands of Ethiopians in DC, Los Angeles and Minneapolis, who came out to support his political reforms back home.

Thursday, October 25, 2018

ከኦብነግ ጋር ስለ ህዝበ ውሳኔ የተነሳ ነገር የለም ተባለ


ከኦብነግ ጋር በተደረገው ስምምነት ስለመገንጠልም ሆነ ህዝበ ውሳኔ የተነሳ ነገር የለም ተባለ።
የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፋ ከድር የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ኦብነግ ባለፈው ቅዳሜ በአስመራ የተደረሰውን ስምምነት አስመልክቶ ‘’በሶማሌ ክልል ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ ከመንግስት ጋር ተስማምተናል’’ ማለቱን በሬ ወለደ ተረር ተረት ነው ሲሉ አጣጥለውታል።

ኦብነግ የሶማሌ ክልል ህዝብ እስከመገንጠል ድረስ ውሳኔ እንዲሰጥ ከመንግስት ጋር ስምምነት ላይ ደርሼ ነው ወደ ሀገር ቤት የምገባው ማለቱን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።
በጉዳዩ ላይ የፌደራሉ መንግስት እስከአሁን የሰጠው ይፋዊ ምላሽ የለም።
ለበርካታ ጊዜያት ተገናኝተዋል። አያሌ ድርድሮችን አድርገዋል። ለዓመታት እየተስማሙ፡ እያፈረሱ ቆይተዋል።
በሸፍጥ ላይ የተመሰረተ ድርድር እያለ የሚወቅሰው ኦብነግ ተደራዳሪዎቹ እየታገቱበትም ድርድሩን ማቆም አልፈለገም።
ከአመራሮቹ መካከል እየካዱ፡ ግንባሩን አፍርሰናል ብለው ከህወሃት አገዛዝ በተደጋጋሚ ሲስማሙ ቢቆዩም ህወሃትም ቀጣይ ድርድር ከመጠየቅ ኦብነግም ሳያቅማማ ጥያቄውን ከመቀበል ወደኋላ ብለው አያውቁም።
አንድም ጊዜ ግን የተሳካ ድርድር ሳያድርጉ የህወሃት አገዛዝ ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ ገብቷል።
ያለፈው ቅዳሜ በኤርትራ አስመራ የተደረገው የሁለቱ ወገኖች ድርድር ግን አንዳች ውጤት ላይ መደረሱን ነው ዘገባዎች ያመለከቱት።
በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ተደራዳሪውን ቡድን የመሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ‘’የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር በሃገር ቤት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል በመወሰን ከስምምነት ላይ ደርሰናል’’ ማለታቸው ተገልጿል።
ኢሳት ከኦብነግ አካባቢ ያገኘው መረጃም ግንባሩ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወስኖ ወደሀገር ቤት ለመግባት መስማማቱን የሚያረጋግጥ ነው። የስምምነታቸው ዝርዝር መረጃ ግን ከሁለቱም ወገኖች አልተገልጸም።
ሆኖም የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ለቢቢሲ ሶማልኛ የሰጡት ቃለመጠይቅ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ምክንያቱ ደግሞ የአስመራው ስምምነት የሶማሌ ክልል ህዝብ ህዝበ ውሳኔ ማድረጉን የሚያካትት ነው ማለታቸው ነው።
የግንባሩ የውጭ ግንኙነት ፀሐፊ አቶ አህመድ ያሲን ሼክ ኢብራሂም ከኢትዮጵያ መንግሥት ስለደረሱበት ስምምነት አስመልክቶ እንደገለፁት የሶማሌ ህዝብ ዕጣ ፈንታውን በነፃነት ራሱ መወሰን እንዳለበት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
በስምምነቱ መሰረትም የራስን ዕድል በራስ መብትን ለመወሰን ህዝበ- ውሳኔ እንዲካሄድና ህዝቡ ከኢትዮጵያ መገንጠል ከፈለገ ያ መብት እንዲከበር፡ መቆየትም ከፈለገ ያ ውሳኔ እንዲከበርለት ውሳኔ ላይ ደርሰናል ነው ያሉት የኦብነጉ ከፍተኛ አመራር አህመድ ያሲን ሼክ ኢብራሂም። ይህንንም ለማስፈጸም ከሁለቱም ወገኖች የተወጣጣ ኮሚቴ እንደሚመሰረት ገልጸዋል።
ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ስለአስመራው ስምምነት ግልጽ መረጃ ባለመቅረቡ የኦብነግ መግለጫ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል።
ኢሳት ጉዳዩን በተመለከተ ከፌደራሉ መንግስት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
ሆኖም በአስመራው ድርድር የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን አባል ሆነው የተገኙት የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ ዑመር በግል ማህበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት ጽሁፍ ጉዳዩን በሬ ወለደ ተረት ተረት ሲሉ ነው ያጣጣሉት።
አቶ ሙስጠፋ እንደሚሉት አስመራ ላይ በተደረገው ንግግር ኦብነግ እንደ ሌሎች ትጥቅ ይዞ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ተቃዋሚዎች የትጥቅ ትግሉን አቁሞ ትግሉን በሰላማዊ መንገድ አገር ውስጥ ገብቶ ለማካሄድ ተስማምቷ።
ከዚህ ውጭ ስለ ህዝበ ውሳኔም ሆነ ስለ መገንጠልም የተነሳ ነገር የለም ሲሉ ነው የገለጹት።
የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚጠበቀው በሶማሌ ህዝብ ፍቃድና ፍላጎት እንጂ በሌሎች ጩኸት አይደለም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ አቶ ሙስጠፋ ኡመር።
የሶማሌ ክልል ህዝብ ከኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጋር በሰላም ለመኖር የሚፈልግ ህዝብ ስለሆነ  የፓለቲካ ቁማርተኞች መጫወቻ ባያደርጉት ጥሩ ነው በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በስተመጨረሻ ደግሞ ቢቢሲ አማርኛው ክፍል የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ስለ ሶማሌ ክልል ሕዝበ ውሳኔ የተናገሩት በሚል ያወጣው ሪፖርት ስህተት ነው ብሏል።
ስህተቱ እንዴትና በምን መልኩ እንደተፈጠረ ግን ያለው ነገር የለም።

የንጉስ አጼ ሃይለስላሴ ሐውልት በመጠናቀቅ ላይ ነው ተባለ

የንጉስ አጼ ሃይለስላሴ ሐውልት በመጠናቀቅ ላይ ነው ተባለ

 በአፍሪካ ሕብረት ጽሕፈት ቤት ውስጥ የቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉስ አጼ ሃይለስላሴ ሐውልት ስራ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገለጸ።
ለአፍሪካ ሕብረት ምስረታ ከፍተኛ ሚና ተጫውተው ሳለ አስተዋጽኧቸው ግን መዘንጋቱና የክዋሜ ንክሩማህ ሐውልት ብቻ መቆሙ ብዙዎችን ያነጋገረ ነበር።

በአፍሪካ ሕብረት ምስረታም ሆነ የአፍሪካ ሃገራት ከቅኝ ግዛት ለመውጣት በሚያደርጉት ትግል በኢትዮጵያ መሪነታቸው ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ንጉስ ሃይለስላሴ ሐውልታቸው በአፍሪካ ሕብረት ጽሕፈት ቤት ውስጥ እንዲቆም ከፍተኛ ተጽእኖ ያደረጉት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና መንግስታቸው እንደነበርም ሲገለጽ ቆይቷል።
የዛሬው የአፍሪካ ሕብረት ከ55 አመት በፊት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ግንቦት 25/1963 የአፍሪካ አንድነት ሆኖ በአዲስ አበባ በ32 የአፍሪካ ሃገራት ሲመሰረት የአስተናጋጇ ሃገር ርዕሰ ብሔርና የመጀመሪያውን የድርጅቱን ጸሐፊ አቶ ክፍሌ ወዳጆን የሰጡት ንጉስ ሃይለስላሴ የአፍሪካ ሃገራት የካዛብላንካና ሞኖሮቪያ በሚል በሁለት ቡድን ሲከፈሉ ወደ አንድ እንዲሰበሰቡና በጋራ እንዲቆሙ አብይ ሚና መጫወታቸውም ሲገለጽ ቆይቷል።
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንደ አውሮፓውያኑ በ2002 ወደ አፍሪካ ሕብረትነት መሸጋገሩን ተከትሎ በቻይና መንግስት ሙሉ ወጪ አዲስ ጽሕፈት ቤት በአዲስ አበባ መከፈቱም ይታወቃል።
በቻይና መንግስት ሙሉ ድጋፍ በ200 ሚሊየን ዶላር ወደ አንድ መቶ ሜትር ርዝመት ያለው ግዙፍና ዘመናዊ ህንጻ ከ6 አመት በፊት ሲጠናቀቅ የመታሰቢያ ሐውልት የቆመው ለቀድሞው የጋና መሪ ዶክተር ክዋሜ ንክሩማህ ብቻ ነበር።
ይህ ከፍተኛ ተቃውሞ የቀሰቀሰ ቢሆንም የአፍሪካ ሕብረት በኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄ ስላልቀረበበት ሳይቀበለው ቆይቷል።
አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ ጉዳዩ እንደገና የተንቀሳቀሰ ሲሆን በዚህም ተቀባይነት በማግኘቱ የአጼ ሃይለስላሴ ሐውልት ግንባታ ተጀምሯል።
ከሁለት ወር በኋላ በፈረንጆቹ አዲስ አመት መጀመሪያ በጥር ወር 2011 ሐውልቱ እንደሚመረቅም ከወጣው መርሐ ግብር መረዳት ተችሏል።

Wednesday, October 24, 2018

የአማራ ክልል ላወጣው መግለጫ የትግራይን ህዝብ ይቅርታ ይጠይቅ ተባለ


(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 14/2011) የትግራይ ክልላዊ መንግስት በራያ ጉዳይ የአማራ ክልል ላወጣው መግለጫ እንዲጠይቅ  አሳሰበ።
ትላንት ማምሻውን የወጣው የትግራይ ክልል መግለጫ የአማራ ክልል መንግስት የራያ ጉዳይ በሃይል መፍታት አይቻልም በሚል ላወጣው መግለጫ ምላሽ እንደሆነም ተመልክቷል።

በአማራ ክልል መንግስት በኩል የወጣው መግለጫ መሰረታዊ የሆነ ሕገ መንግስታዊ ጥሰት ያለበትና በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ለዘመናት የኖረውን አብሮነት የሚጎዳ አደገኛ አካሄድ መሆኑን በመጥቀስ ለትግራይ ህዝብ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና የትግራይ ህዝብ በጥብቅ እናሳስባለን ይላል።
የአማራ ክልል ለማሳሰቢያ እስከአሁን የሰጠው ምላሽ የለም።
የትግራይ ክልል የራያው ውዝግብ ዳግም ከተቀሰቀሰ ካለፈው ቅዳሜ ወዲህ ለሁለተኛ ጊዜ ያወጣው ማሳሰቢያ ለአማራው ክልል የትላንት ምላሽ መሆኑ ተመልክቷል።
የትግራይ ክልል መንግስትና ህዝብ ሰላሙን አስጠብቆ የክልሉን ውስጣዊ ችግሮች ለመፍታት ሌትና ቀን በሚረባረብበት ወቅት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያወጣው መግለጫ  ከትንኮሳ የማይተናነስ ጠባጫሪ አቋም ነው ይላል ከመቀሌ ትላንት ማምሻውን የወጣው መግለጫ።
የአማራ ክልል መስተዳድር ማክሰኞ ዕለት እንዳስታወቀው ሁለቱ ክልሎች በሚያዋሰኑት የወልቃይትና የራያ አላማጣ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶች የሰላም መታወክ እየገጠመ ይገኛል።
ይህ የሰላም መታወክ ለአማራው ክልል ትልቅ የፀጥታ ስጋት ሆኗል ብሏል።
የትግራይ ክልል መንግስትን ያስቆጣውም ትግራይ እንደምን ለሌላው ሰላም ማጣት ሰበብ ተደርጋ ትወቀሳለች የሚል ነው። መግለጫውንም አሳዛኝና ጠብ ጫሪነት ነው ሲል ወቅሷል።
የትግራይ ክልል የሁሉም ብሄር ብሄረሰብ ተወላጆች ሕገ መንግስታዊ መብታቸውና ነፃነታቸው ተከብሮ በሰላምና በክብር የሚኖሩባት ክልል ሆና እያለች ዜጎች በማንነታቸው የሚፈናቀሉባትና የአማራ ክልል ሰላም ችግር ፈጣሪ መባሏ አሳዛኖናል ይላል የትግራይ ክልሉ መግለጫ።
የትግራይ ክልል ለየትኛውም አካባቢ የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል።
የተከሰተው ግጭት መነሻው የራያ አካባቢ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ሲሆን ይህንን ጥያቄ ከህዝቡ ጋር በመነጋገር ሕገ መንግስታዊ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ በአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲም ሆነ በኢህአዴግ ጉባኤዎች አቅጣጫ መቀመጡ ይታወሳል የሚለውን በአማራ ክልል መንግስት መግለጫ የተጠቀሰውን የትግራይ ክልል መስተዳድር ሕገ መንግስቱ በማንነት ጉዳይ ላይ ያስቀመጠውን ስርዓት በመጣስ በሌላ ክልል የውስጥ ጉዳይ ጠልቃ መግባቱን የሚያረጋግጥ መግለጫ ነው ሲል ከሷል።
በዚህም በራያና በወልቃይት አካባቢዎች ለተፈጠሩ ችግሮች የአማራ ክልል መንግስት ኃላፊነቱን መውሰድ ይኖርበታል በማለት የትግራይ ክልል በመግለጫው አስታውቋል።
በአጠቃላይ የአማራ ክልል መንግስት ያወጣው መግለጫ መሰረታዊ የሆነ ሕገ መንግስታዊ ጥሰት ያለበትና በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ለዘመናት የኖረው አብሮነት የሚጎዳ አደገኛ አካሄድ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም እና የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትም ለትግራይ ህዝብ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና የትግራይ ህዝብ በጥብቅ እናሳስባለን ሲል ያጠቃልላል።
ለትግራይ ክልል መንግስት ማሳሰቢያ የአማራው መስተዳድር ምላሽ ይሰጣል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

በዴር ሱልጣን በግብጽ የሃይማኖት መሪዎችና በእስራዔል ፖሊስ መካከል ግጭት ተፈጠረ


በኢየሩሳሌም የሚገኘው ዴር ሱልጣን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እንዳይታደስ በከለከሉ የግብጽ የሃይማኖት መሪዎችና በእስራዔል ፖሊስ መካከል ግጭት ተፈጠረ።
እድሳቱን ለማከናወን ወደ ቤተክርስቲያኑ ሊገቡ የነበሩ ሰራተኞችን የግብጽ ጳጳሳትና መነኮሳት ክልከላ ማድረጋቸውን ተከትሎ የእስራዔል ፖሊስ ርምጃ ወስዷል።

ከአንድ ዓመት በፊት ጣሪያው የተደረመሰውን የኢትዮጵያ ገዳም ለማሳደስ ከፍተኛና እልህ አስጨራሽ ትግል መካሄዱን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ይዞታ ለመንጠቅ በየጊዜው ሙከራ የሚያደርጉት ግብጻውያን ገዳሙ እንዳይታደስ በሃይል ያደርጉትን ክልከላ የእስራኤል ፖሊስ በማስቆም በዛሬው ዕለት  ዕድሳቱ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።
በኢየሩሳሌም በሚገኘው የዴር ሱልጣን ገዳማት የኢትዮጵያና የግብጽ የሃይማኖት መሪዎች ውዝግብ ሁለት መቶ ዓመታትን ያስቆጠረ ነው።
ኢትዮጵያ በዴር ሱልጣን ገዳም ያላት መብት ከግብጽ ወደ አከባቢው መግባት አስቀድሞ በዙ ዘመናትን ያስመዘገበ እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል።
በ18ኛው ክፍለ ዘመን ኢብራሂም ጉሃሪ የተባሉ ግብጻዊ የሃይማኖት ሰው ከስምንት ረዳቶቻቸው ጋር ወደ ኢየሩሳሌም በማቅናት የይገባኛል ጥያቄ ካነሱበት ጊዜ ጀምሮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ዴር ሱልጣን የውዝግብ ማዕከል ሆኖ ቆይቷል።
በኢትዮጵያ ነገስታት ትኩረት ባለመሰጠቱ ኢትዮጵያ በዴር ሱልጣን ያላት ይዞታ እየተሸረሽረ አሁን በገዳሙ ጣሪያ የሚገኘው አንድ ቤተክርስቲያን ብቻ ቀርቷል።
ግብጻውያን ይህንንም የቀረውን የኢትዮጵያ ይዞታ ለመንጠቅ ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም።
በየጊዜው በግብጻውያን በሚነሳ የይገባኛል ጥያቄ ምክንያት ግጭቶች ሲፈጠሩ እንደነበረ የገዳሙ አባቶች ይናገራሉ።
ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ላይ የኢትዮጵያ ይዞታ በሆነ የዴር ሱልጣን ገዳም ጣሪያው ተደርምሶ በገዳሙ ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ የሚታወስ ነው።
መደበኛውን ቤተክርስቲያኒያዊ አገልግሎት መስጠት ያልቻለው ገዳሙ ለአንድ ዓመት ያህል በወሰደው ድርድርና ከእስራዔል መንግስት ጋር በተደረገ ስምምነት የእድሳት ተግባሩ እንዲከናወን ፍቃድ መገኘቱን ነው ለማወቅ የተቻለው።
ይሁንና ገዳሙ ተዘግቶ እንዲቀር በሂደትም ቁልፉን ከኢትዮጵያ እጅ ለመንጠቅ የፈለጉት ግብጻውያን እድሳቱ እንዳይከናወን ችግር መፍጠራቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በትላንትናው ዕለት እድሳቱን ለማከናወን ወደ ገዳሙ የመጡትን የግንባታ ሰራተኞች እንዳይገቡ ለማድረግ የግብጽ የሃይማኖት አባቶችና ተከታዮች የገዳሙን መግቢያ በር በመዝጋት ብጥብጥ መፍጠራቸውን በቪዲዮ ተደግፎ ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
በእስራዔል መንግስት ፍቃድ የተሰጠውን የእድሳት ተግባር የከለከሉት ግብጻውያን በሃይል የግንባታ ሰራተኞቹ ላይ የጣሉት ክልከላ ውደ ግጭት በማምራቱ የእስራዔል ፖሊስ ጣልቃ መግባቱም ተገልጿል።
ከፖሊስ ጋር ግብግብ ውስጥ የገቡት ግብጻውያን በመጨረሻም ፖሊስ በሃይል ከአካባቢው እንዲወገዱ አድርጓቸዋል።
ፖሊስ ግብጻውያን ጳጳሳትንና መነኮሳትን ጭምር በመጎተት ከስፍራው ካራቃቸው በኋላ የእድሳት ስራው ሊጀመር መቻሉ ታውቋል።
በዴር ሱልጣን የኢትዮጵያ ገዳም አበባት አባ ገብረኪዳን ሺፈራው ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት የእዳሳቱ ስራ እስከሚያልቅ በጸሎትና በማንኛውም እገዛ ኢትዮጵያውያን ከገዳማቸው ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።
ግብጻውያን ከመንግስታቸው አንስቶ በእስራዔል ነዋሪ የሆኑት ተባብረው የኢትዮጵያን ይዞታ ለመንጠቅ እያደረጉ ያሉትን ግብግብ ኢትዮጵያውያንም በአንድነት ሆነው ገዳማቸውን እንዲታደጉትም ጥሪ ተደርጓል።

የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ስልጣን ለቀቁ


የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ስልጣናቸውን ለቀቁ። አዲስ ፕሬዝዳንትም ተሰይሟል።
በአዲስ አበባ ለአንድ ሳምንት ግምገማ ሲያደርግ የቆየው የጋምቤላ ክልል ገዢ ፓርቲ በገዛ ፈቃዳቸው የለቀቁትን ሊቀመንበሩንና ምክትላቸውን በሌሎች መተካቱን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበርና የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱትና ምክትላቸው አቶ ሰናይ አኩዎር ይቅርታ ጠይቀው በለቀቁበት የአዲስ አበባው ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መገኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በጋምቤላ የጋትሉዋክ ቱት አመራር ከስልጣን እንዲወርድ የተቃውሞ ሰልፍ ሲደረግ ቆይቷል።
በዚህ ተቃውሞ በተወሰደ የሃይል ርምጃም በትንሹ አስር ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል።
ለወራት የዘለቀው የህዝብ ጩሀት በመጨረሻም ሰሚ አገኘ።
የጋምቤላ ክልል ነዋሪ አመራሩ እንዲነሳለት ህይወቱን የገበረለትን ተቃውሞ ሲያደርግ ነበር የቆየው።
ባለፉት ሶስት ወራት በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች ለፌደራሉ መንግስት ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።
በአመራር ላይ ያለው የጋትሉዋክ አስተዳደር በኢትዮጵያ የመጠውን የለውጥ ሂደት የሚያደናቅፍ ከመሆኑ ባሻገር የህወሀት የጭቆና አገዛዝን ማስቀጠል የመረጠ በመሆኑ በአስቸኳይ ይነሳ የሚለው ጥያቄ ተነስቷል።
ተቃውሞው በተለይ የክልሉ ፕሬዝዳንት ላይ ያነጣጠረ ነበር።
ለዚህም ሁለት ምክንያቶች ይነሳሉ። አንደኛው የክልሉ ፕሬዝዳንት ጋትሉዋክ ቱት በትውልድ ደቡብ ሱዳናዊ በመሆናቸው በስደት ወደኢትዮጵያ ለገቡትና በቁጥር በጋምቤላ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን ለሚበልጡ ደቡብ ሱዳናውያን ያደላሉ የሚል ነው።
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከህወሀት አገዛዝ ጋር እጅና ጓንት ሆነው የክልሉን ህዝብ ለጭቆናና ብዝበዛ እየዳረጉት እንደሆነ ይጠቀሳል።
የህወሃት ዘመን አፈናና በደል ጋምቤላ ተጠናክሮ መቀጠሉን ህዝቡ በምሬት ይገልጻል።
በቅርቡ ለውጡን ለመታዘብ ሀገር ቤት የገቡትን በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆኑት ዶክተር ማኛንግን ጨምሮ ከ10 በላይ አክቲቪስቶችን የግትሉዋክ ቱት አስተዳደር ማሰሩ ተቃውሞውን አጠናክሮታል።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፕሬዝዳንት አቶ ኦባንግ ሜቶ ወደ ጋምቤላ ባመሩ ጊዜ የጋቱዋክ ቱት አመራር የፈጠረውን ችግር መነሻ በማድረግ በአዲስ አበባ መግለጫ የሰጡት አቶ ኦባንግ የፌደራሉ መንግስት በጋምቤላ አስተዳደር ላይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቃቸውም የሚታወስ ነው።
ለወራት የህዝብ ብሶትና እሮሮ ከተሰማ በኋላ ትላንት ምላሽ መገኘቱን ነው የደረሰን መረጃ የሚያመለክተው።
አዲስ አበባ የገቡትና ግምገማቸውን ከጀመሩ አንድ ሳምንት የሆናቸው የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጋህአዴን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከአንድ ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን አሳውቀዋል።
ህዝብ ለውጥ እንደሚፈልግ፣ አመራሩ እንቅፋት ሆኖ እንደቆየ አባላቱ ጠንከር ያለ ግምገማ ማድረጋቸውን ተከትሎ የህዝብ ተቃውሞ የቀረበባቸው አቶ ጋትሉዋክ ቱትና ምክትላቸው አቶ ሰናይ አኩዎር በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተስምቷል።
ፓርቲው አቶ ኦሙድ ኡጁሉን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አኙአያ ጃከን ደግሞ ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡም ታውቋል፡፡ አቶ ኦሙድ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ክልሉን እንደሚመሩ ነው የተገለጸው።
በግምገማው ላይ  ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ መገኘታቸው ታውቋል።
የክልሉ ህዝብ ልማት የተጠማ በመሆኑ አዲሱ አመራር ጊዜውን በግል አጀንዳዎችና ሽኩቻ ከማጥፋ ይልቅ ራሱን ከጎሰኝነትና ከጥላቻ በማጽዳት የክልሉን አመራር በማጠናከር የህዝቡን ችግር ሊፈታ እንደሚገባ ማስገንዘባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ ገልጸዋል።
ከኃላፊነት የተነሱት አመራሮችም በድርጊታቸው ተጸጽተው ይቅርታ መጠየቃቸው እና ህዝቡን ለመካስ በተመደቡበት የስራ መስክ ለመሰማራት መወሰናቸውም ተመክልቷል።
ኢሳት ያነጋገራቸው የጋምቤላ አክቲቪስቶች ግን የጋትሉዋክ አመራር አባላት ለፈጸሙት የግድያና የዘረፋ ወንጀል በህግ ሊጠይቁ ይገባል ባይ ናቸው።

Tuesday, October 23, 2018

የለውጡ አደናቃፊ የተባሉ የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ኢስማዔል አሊሴሮና ሌሎች 18 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ታገዱ

ከፌደራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ሰመራ ገቡ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 16/2011)የአፋር ክልል ገዢ ፖርቲ አብዴፓ ውስጥ የተፈጠረውን መሰንጠቅ ተከትሎ ከፌደራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ወደ ሰመራ መግባታቸው ተገለጸ።
ለውጡን በሚደግፉና በሚቃወሙ የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አብዴፓ መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ፓርቲውን ለሁለት መክፈሉ ታውቋል።

የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ስዩም አወል ምክትላቸውን ጨምሮ የቀድሞ የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ኢስማዔል አሊሴሮንና ሌሎች 18 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ትላንት አግደዋል።
በፕሬዝዳንቱ የታገዱት አመራሮችም በፊናቸው ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ የለውጡ አደናቃፊ የተባሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ማገዳቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ከፌደራል ወደ አፋር ያቀኑት ከፍተኛ አመራሮች አልታውቁም። የአፋር ህዝብ ተቃውሞውን ማሰማቱን ቀጥሏል።
የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አብዴፓ ለሁለት መሰንጠቁ በአፋር ህዝቡ እያሰማ ላለው ተቃውሞ ትልቅ ድል ተደርጎ እየተወሰደ ነው።
ፓርቲውን በአመራርነት የያዙት ሰዎች ከአዲስ አበባው የፌደራል መንግስት ይልቅ ለመቀሌው የህወሃት ቡድን ታዛዥ ናቸው የሚለው ተቃውሞ ላለፉት አራት ወራት የአፋር ክልል ከተሞችን አዳርሷል።
በተለይም የክልሉ ፕሬዝዳንትና የአብዴፓ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ስዩም አወል የህወሃት ረጅም እጅ በፓርቲው ውስጥ ጉልበት እንዲኖረው መፍቀዳቸው ጠንከር ያለ ተቃውሞ አስከትሎባቸዋል።
ህወሃቶች የአፋርን ጨውና ማዕድን በበላይነት እንዲቆጣጠሩና ፍጹም የበላይ እንዲሆኑ አድርገዋል የሚባሉት አቶ ስዩም አወል በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ አፋር ምድር እንዳይገባ ሲከላከሉ ነበር ተብሏል።
ባለፈው ሀምሌ ወር ወደ አፋር ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከአፋር ወጣቶች ጋር እንዳይገናኙ ገደብ የጣሉት አቶ ስዩም አወል ከባህር ማዶ ወደ ሀገር ቤት የገቡ የአፋር የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አክቲቪስቶች ወደ ክልል እንዳይመጡ እንቅፋት በመፍጠር ክስ እንደቀረበባቸው የሚታወስ ነው።
የአፋር የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ፕሬዝዳንት አቶ ገአስ አህመድ በአዲስ አበባ መግለጫ በመስጠት የፌደራሉ መንግስት በአፋር እየተካሄደ ያለውን አፈና እንዲያስቆም መጠየቃቸው ተገልጿል።
ያለማቋረጥ በአፋር ክልል ለወራት ሲካሄድ የነበረው የህዝብ ተቃውሞ በዋናነት አቶ ስዩም አወል የሚመሩት የክልሉ አስተዳደር ስልጣን እንዲለቅ፣ እንዲሁም የህውሃት ጣልቃ ገብነት እንዲቆም የሚጠይቅ ነው።
ከየአቅጣጫው ጫናው የበረታበት የአፋር ገዢ ፓርቲ ለሁለት መሰንጠቁ ሲገለጽ የህዝቡ ተቃውሞ ሰሚ እያገኘ ለመምጣቱ አመላካች ነው ተብሏል።
ፓርቲውን ለሁለት የሰነጠቀውም ለውጡን በሚቃወመው የአቶ ስዩም አወል ቡድንና ስልጣን ለቀን ለአዲስ አመራር እንስጥ በሚለው ምክትል ፕሬዝዳንቱ በሚመሩት እንጃ መሀል ነው።
ክልሉን ለረጅም አመታት የመሩት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል አሊ ሴሮም የህዝብ ድምጽ ይሰማ በልው አቋም መያዛቸውን ነው ያገኘነው መረጃ የሚያመልክተው።
ለሁለት የተከፈለው ፓርቲው የጎሳን መስመር መከተሉ ደግሞ በቀጣይ የእርስ በእርስ ግጭት እንዳያስከትል ስጋት ፈጥሯል።
አቶ ስዩም ፓርቲውም በጎሳ ለሚዛመዱት ሰው አስረክባለሁ ማለታቸው ስጋቱን ጨምሯል።
ሁለቱም ቡድኖች በየፊናቸው የእገዳ ውሳኔ ማስተላልፋቸው የተገለጸ ሲሆን ከህዝብ ወገን የቆመው የምክትል ፕሬዝዳንቱን ቡድን ለማጥቃት የአቶ ስዩም አወል አንጃ የህወሀትን ድጋፍ እየፈለገ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ዛሬ እንደተሰማው ደግሞ የአፋር ገዢ ፓርቲ መስንጠቅን ተከትሎ የሚፈጠረውን አደጋ ለማስቅረትና መፍትሔ ለመስጠት ከፌደራል መንግስት ከፍትኛ የኢህ አዴግ አመራር ቡድን ወደ አፋር አቅንቷል።
ስለአመራር ቡድኑ ዝርዝር መረጃ ባይገኝም እየተጠናከረ የመጣውን የህዝብ ብሶት መልስ ለመስጠት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስተዳደር ከውሳኔ መድረሱን የሚያመላክት ርምጃ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የአቶ ስዩም አወል አንጃ ከስልጣን ከተወገደ ህወሀት በአፋር የሰነዘረው ረጅም እጅ ሊቆረጥ የሚችል ነው ተብሏል።

አማራና ኦሮሚያ የሚባሉ ክልሎችን የፈጠረው ኢህአዴግ ነው

አማራና ኦሮሚያ የሚባሉ ክልሎችን የፈጠረው ኢህአዴግ ነው ተባለ

አማራና ኦሮሚያ የሚባሉ ክልሎችን የፈጠረው ኢህአዴግ ነው ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ።
ከማንነት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች ህገመንግስታዊ ስርዓቱን ለማፍረስ የሚደረግ ሙከራ ነው ሲሉም የህወሃት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ከድምጸ ወያኔ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ እንደገለጹት የወልቃይትና ራያ የማንነት ጥያቄዎች የቀድሞውን የጠቅላይ ግዛት መዋቅር ለመመለስ የሚደርግ እንቅስቃሴ ነው ።
በሌላ በኩል የማንነት ጥያቄን በተመለከተ በአፈጉባዔዋ የተሰጠውን መግለጫ አዛብቶ አቅርቧል በማለት ፌዴሬሽን ምክር ቤት የአማራ መገናኛ ብዙሃንን ወቅሷል።
የአማራ መገናኛ ብዙሃን የመግለጫውን ያልተቆራረጠ ቪዲዮ ሙሉውን ለህዝብ እንደሚለቅ አስታውቋል።
አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ አማራ ክልል ይካለሉ እያሉ አካባቢዎችን እየጠቀሱ የሚጠይቁትን ጂኦግራፊ ምን እንደሆነ ያማያውቁ ናቸው ሲሉ ነው  ለድምጸ ወያኔ በሰጡት ቃለመጠይቅ።
ባህርዳርና ጎንደር ላይ ሆነው ወልቃይት ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ፣ ራያ አዘቦ የእኛ ነው ብለው የሚጮሁና ሰልፍ የሚወጡ ሰዎች የቀድሞውን ጠቅላይ ግዛት ለመመለስ የሚፈልጉ ናቸው ያሉት አቶ ጌታቸው አማራ ክልልን የፈጠረው ኢህአዴግ፣ አማራ የሚባል ክልል አልነበረም ሲሉ ገልጸዋል።
ወልቃይት፣ ራያም ሆነ ሌላ አካባቢ ወደ አማራ ክልል ይመለስ የሚለው ጥያቄ ህገመንግስቱን የሚያፍርስ እንደሆነም አቶ ጌታቸው በቃለመጠይቁ ላይ አንስተዋል።
‘’የህዝብ ፍላጎትን ግምት ውስጥ ያላስገባ ግዛታችን  የሚል ጥያቄ በታሪክም በህግም አያስኬድም።
በኢትዮጵያ ታሪክ አማራ የሚባል ክልል አልነበረም፣ ኦሮሞ የሚባል አልነበረም፣ ትግራይ የሚባል ክልል አልነበረም።
ምናልባት ትግራይ ለረዥም ግዜ የነበረው ግዛት በተወሰነ መልኩ ተቀራራቢ ነው ማለት ይቻላል።
የትግራይ ክፍለ ሃገር በታሪክም ትግራይ የሚባል የሚታወቅ ክፍል አለ። በታሪክ አማራ የሚባል ክልል ግን አልነበረም፣ አማራ ጠቅላይ ግዛት የሚባልም አልነበረም። በታሪክ አማራ የሚባል አካባቢ አልነበረም።
ኦሮሞ የሚባል ክልል በፊት አልነበረም፣ ኦሮሚያ የሚባል ክልል የኢህአዲግ ህገ መንግስት የፈጠረው ነው። ብለዋል የህወሀቱ አቶ ጌታቸው ረዳ።
አቶ ጌታቸው የህዝብ ፍላጎትን ከግምት ያላስገባ ሲሉ ወልቃይትና ራያዎች በየትኛው ህዝበ ውሳኔ ወደ ትግራይ ክልል እንደተጠቃለሉ የሚገልጽ ማብራሪያ ግን አላቀረቡም።
በትግርኛ ቋንቋ ለድምጸ ወያኔ ቃለመጠይቅ የሰጡት አቶ ጌታቸው ረዳ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በወሎ ክፍለሀገር እንደተፈተኑ የገለጹ ሲሆን እሳቸው ፈተናውን የወሰዱበት አከባቢ አሁን በትግራይ ክልል ውስጥ መጠቃለሉን አለመረዳታቸው አስገራሚ እንደሆነባቸው ነው ቃለመጥይቁን የተከታተሉ ወገኖች የሚገልጹት።
አቶ ጌታቸው በማንነት ዙሪያ የሚቀርቡ ጥያቄዎች ህገመንግስቱን የሚያፈርስ በመሆኑ እንደህወሀትና ኢህ አዴግ ልናወግዘው ይገባልም ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፌደሬሽን ምክር ቤት የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ በአፈጉባዔዋ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ያቀረበው ዘገባ የተዛባ ነው ሲል ቅሬታውን ማቅረቡ ታወቀ።
ፌደሬሽን ምክር ቤት በደብዳቤው እንደገለጸው አፈጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ መሃመድ የማንነት ጥያቄን በተመለከተ አጠቃላይ በሆነ መልኩ የሰጡትን ማብራሪያ የአማራ መገናኛ ብዙሃን  ድርጅት ባልደረባ በሚመቸው መልኩ አዛብቶ አቅርቧል ሲል ከሷል።
የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ወዲያውኑ ምላሽ የሰጠ ሲሆን በቀረበው ዘገባ የህግም ሆነ የጋዜጠኝነት ስነምግባር ጥሰት የሌለው ነው ብሏል።

Over 200 detained amid continued deadly protest in Northern Ethiopia




Security forces of the Tigray region detained over 200 people in Raya Waja and Raya Qobo. The whereabouts of most of the detainees is not known, according to residents who spoke to ESAT.
Ninety of the detainees have reportedly been held at the Maichew prison.
On Sunday, Tigray region special police killed five residents of Alamata, a town sitting 470 miles north of the capital Addis Ababa on the route to the regional capital Mekele.
The people of Raya have been voicing their demand on the status of their administration which is under the Tigray region. They say they are Amharas and hence should not be under the administration of the Tigray region.
The residents took to the streets on Sunday to once again show their objection of being administered under the Tigray region.
Hospital sources told ESAT on Monday that 35 people have been admitted for gunshot wounds. Thirteen of them have sustained serious wounds, according to hospital sources.
Protests spread to Mehoni, Raya Waja and Raya Qobo today where residents blocked a bus en route from Mekele to the capital Addis Ababa. The residents demand the release of detainees before freeing the bus.
Meanwhile, war of words continued between the Amhara and Tigray regions, one side accusing the other of fomenting the crisis.

Monday, October 22, 2018

በውጭና በሃገር ውስጥ የሚገኙ ጳጳሳት ከ25 አመታት በኋላ በጋራ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ጀመሩ

    በውጭና በሃገር ውስጥ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጳጳሳት ከሩብ ክፍለ ዘመን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በጋራ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ጀመሩ። በየአመቱ በጥቅምትና በግንቦት ወር የሚካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ከ25 አመታት በላይ ለሁለት ተከፍሎ ሲካሄድ ቆይቷል።

አዲስ አበባ ላይ የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቤተክርስቲያኒቱ ጉዳይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሃገራዊ ሁኔታ ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጋር ግንኙነቷን ለማጠናከርም ኮሚሽን እንደሚቋቋም ተመልክቷል።
ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ ለሁለት ተከፍላ የቆየችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ የተካሄደውን ለውጥ ተከትሎ በወረደው እርቅ ፓትሪያርክ አቡነ መርቆሪዎስ ከ25 አመታት በኋላ ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል።
በፓትሪያርክ አቡነ መርቆሪዎስና በፓትሪያርክ አቡነ ማትያስ በጋራ እየተመራ ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ይጠናቀቃል ተብሎም ይጠበቃል።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ከሁለት አመታት ስደት በኋላ ትላንት አዲስ አበባ ገባ።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ከሁለት አመታት ስደት በኋላ ትላንት አዲስ አበባ ገባ። ከጸጥታ ጋር በተያያዘ እንደሆነ በታመነ መልኩ ሕዝባዊ አቀባበል አልተደረገለትም።

ወደ ሃገር የመመለሻ ጊዜው ጭምር ሲለዋወጥበት የቆየው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የመንግስት ባለስልጣናት፣ቤተሰቦቹ እንዲሁም አትሌቶች ተቀብለውታል።
በብራዚል ሪዮ ኦሎምፒክ በነሐሴ ወር 2008 በማራቶን ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን አፈና በይበልጥም ግድያውን በመቃወም ስርአቱን በኦሎምፒክ መድረክ መቃወሙ ይታወሳል።
ከሁለት አመት በፊት በብራዚል ሪዮ ኦሎምፒክ ለኢትዮጵያ ሜዳሊያ ያስገኘው ሆኖም በስደት ከብራዚል ወደ አሜሪካ ያቀናው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በኢትዮጵያ የሚገኙት ባለቤቱና ልጆቹንም ወደ አሜሪካ መውሰዱ ይታወሳል።
ላለፉት 2 አመታት ከሁለት ወር ያህል በስደት የቆየው ጀግናው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ አዲሰ አበባ ሲገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁና የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተቀብለውታል።
ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ሌሎች አትሌቶች እንዲሁም የኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ እንዲሁም ቤተሰቦቹ በአቀባበል ስነስርአቱ ላይ ተገኝተዋል።
አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በመስከረም ወር 2011 ኢትዮጵያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግለት መርሃ ግብር ከተያዘለት በኋላ ከጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ የመመለሻ ቀኑ መራዘሙ ተመልክቷል።
የመምጫው ቀን በይፋ ሳይገለጽም ትላንት ጥቅምት 11/2011 አዲስ አበባ ካባለቤቱና ከ2 ልጆቹ ጋር ገብቷል።
ወላጆቹም በአቀባበል ስነስርአቱ ላይ እንደነበሩም ታውቋል።

Congressman urges U.S. to impose sanctions on ex Ethiopian spy chief


One of rare photos believed be Getachew Assefa

A congressman wrote a petition urging the United States to apply the Global Magnitsky sanctions against a former Ethiopian spy chief who is implicated in a wide range of crimes and human rights violations.
In a letter to the Secretary of State Mike Pompeo and the Secretary of Treasury Steve Mnuchin, Representative Mike Coffman of the 6th district of Colorado said the former head of the Ethiopian National Intelligence and Security Service, Getachew Assefa, “has been implicated in numerous serious crimes, including ethnic based violence in different parts of Ethiopia.”
The letter says the application of the Magnitsky Act will allow the President of the United States to impose visa and asset sanctions.
“By specifically targeting Assefa, the United States also demonstrate that no one will be beyond the reach of being held accountable and will face the consequences of their actions.”
Getachew Assefa has headed the security and intelligence arm of the TPLF controlled government until his removal by the government of Abiy Ahmed in June.
He has been implicated in the disappearance, torture, imprisonment and extrajudicial killings of dissidents.
In August, an Ethiopian court had issued an arrest warrant on the former spy chief. But he has been hiding in Tigray since he was removed from office.
Pro TPLF social media activists say he is recently appointed as security advisor to the administrator of the Tigray region.
Getachew Assefa has never been seen in public and has shunned the media. There are only a couple of photos believed to be the former spy chief available in the public domain. 

Sunday, October 21, 2018

የትግራይ ልዩ ሃይል ከወልቃይትና ራያ እንዲወጣ ተጠየቀ


 የትግራይ ልዩ ሃይል ከወልቃይትና ራያ ወጥቶ በምትኩ የፌደራል ፖሊስ እንዲገባ ተጠየቀ።
ልሳነ ግፉአን የተሰኘው የወልቃይት ጠለምት ጠገዴ መብት ተሟጋች ድርጅት በራያ እየተካሄደ ያለውን ጥቃት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ወገንተኛ የሆነው የትግራይ ልዩ ሃይል ሰላም የሚያስከብር ባለመሆኑ ገለልተኛ የሆነ አካል በአካባቢው መስፈር ይገባዋል።

ከራያ ተወላጆች ጎን እንቆማለን ያለው ልሳነ ግፉአን ህወሃት በቀረጸው ህገመንግስትም ሆነ በህወሃት በተዋቀረው ፌደራል ስርዓቱ የማንነት ጥያቄዎች ፈጽሞ ሊመለሱ አይችሉም።
በሌላ በኩል በራያ ተወላጆች ላይ የትግራይ ልዩ ሃይል የሚወስደውን አፈና ግድያና እስር በመቃወም በበርካታ የአማራ ክልል ከተሞች ሰልፍ ተጠርቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም በአላማጣ አፈሳውና እስሩ ለስድስተኛ ቀን መቀጠሉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ህወሃቶች የማንነት ጥያቄ ህገመንግስቱን የሚያፈርስ ነው የሚል አቋም እያንጸባረቁ በሚገኙበት በዚህን ወቅት ከየአቅጣጫው ለራያዎች ድጋፍ እየተሰጠ ነው።
በወልቃይት ጠለምትና ጠገዴ የማንነት ጥያቄ ላይ ድጋፍ በማድረግ የሚንቀሳቀሰው ልሳነ ግፉአን የራያን ህዝብ መሬት ለመዝረፍና ማንነቱን በሃይል ለመጨፍለቅ የሚደረገው አፈና ትግሉን ያጠናክረዋል እንጂ አያዳክመመው ሲል አጋርነቱን አሳይቷል።
ልሳነ ግፉአን ለኢሳት በላከው መግለጫ ላይ እንደገለጸው በወገናችን የራያ ህዝብ ላይ እንዲህ ዓይነት የጭካኔ ተግባር መፈጸሙ በእጁ አሳዝኖናል ብሏል።
በመሆኑም ሽብር ፈጣሪው የህወሀት ልዩ ሃይል በአስቸኳይ ከራያና ወልቃይት መሬት ለቆ እንዲወጣና በምትኩ የፌደራል ፖሊስ የአከባቢውን ሰላም እንዲያስከብር ለፌደራሉ መንግስት ጥሪ አቀርባለሁ ሲል ገልጿል ልሳነ ግፉአን።
በትግራይ ልዩ ሃይል ታፍነው የት እንደትወሰዱ የማይታወቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ የራያ ተወላጆች በአስቸኳይ እንዲፈቱ የጠየቀው ልሳነ ግፉአን በጭካኔ ለተገደሉት ራያዎች ለቤተሰቦቻቸው ካሳ እንዲከፈልም ጠይቋል።
የራያና ወልቃይት የማንንት ጥያቄ በህውሀት እንደማይመለስ የገለጸው ልሳነ ግፉአን ጉዳዩን የህወሀት ህገመንግስት ሊፈታው የማይችለው ሲል ገልጿል።
ታሪካዊና ባህላዊ መሰረትን ባጠና መልኩ የማንነት ጥያቄን ለመመለስ የፌደራል መንግስቱ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቋል።
በሌላ በኩል በራያ ተወላጆች እየተፈጸመ ያለውን አፈና ግድያና እስር በማውገዝ በበርካታ የአማራ ክልል ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል።
የፊታችን እሁድ ጥቅምት 18 የጠራውን ሰልፍ የጠየቁ ከ10 በላይ ከተሞች ፍቃድ ማግኘታቸውን የደረሰን መረጃ ያመልክታል።
ባሕር ዳር፣ ወልዲያ፣ ጎንደር፣ ፍኖተ ሰላም፣ እንጅባራ፣ ደብረ ታቦር፣ደብረ ብርሃን፡ ደብረ ማርቆስ፣ ከሚሴ፣ ደሴና ሰቆጣ ዕሁድ ዕለት ለራያዎች አጋርነታቸውን ለማሳየት አደባባይ ይወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከራያ በተጨማሪ አደጋ ላይ የወደቀውን ጣና ሀይቅንና በላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት ላይ የተጋረጠውን የመፍረስ አዝማሚያ በማንሳት ትኩረት እንዲሰጠው የሚጠይቅ ይሆናልም ተብሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም በአላማጣ ዛሬም አፈናና እስር በመካሄድ ላይ መሆኑን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
ስድስተኛው ቀኑን በያዘው የትግራይ ልዩ ሃይል ርምጃ በርካታ የራያ ተወላጆች እየታሰሩ መሆኑ ታውቋል።
አንድ ሳምንት ባስቆጠረው የአላማጣ ውጥረት የታሰሩት ሰዎች ቁጥር በትትክል ባይታወቅም ከ500 በላይ እንደሚሆን ግምቶች አሉ።
አምስት ሰዎች በትግራይ ልዩ ሃይል በተሰውደ ርምጃ መገደላቸው የሚታወስ ነው።

Tigray special police killed five in Alamata




Tigray region special police have killed five residents of Alamata, a town sitting 470 miles north of the capital Addis Ababa on the route to the regional capital Mekele.
The people of Raya have been voicing their demand on the status of their administration which is under the Tigray region. They say they are Amharas and hence should not be under the administration of the Tigray region.

On Sunday, the residents took to the streets to once again show their objection of being administered under the Tigray region.
Security forces of the region shot and killed five residents while hospital sources told ESAT that 35 people have been admitted for gunshot wounds. Thirteen of them have sustained serious wounds, according to hospital sources.
The burial of five people killed on Sunday was conducted today amid continued clashes with police, who used tear gas to disperse crowds.
In the nearby town of Kobo, the national defense forces opened roads closed by protesters in response to the killings in Alamata.
Sundays killings brought the number people killed in the last one year to 10.

Friday, October 19, 2018

በታንዛኒያ ውቂያኖስ ዳርቻ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ ሰባት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተገልብጠው ህይወታቸውን አጡ።


በታንዛኒያ ውቂያኖስ ዳርቻ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ ሰባት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተገልብጠው ህይወታቸውን አጡ።
መነሻቸውን ከኬኒያ በማድረግ ወደ ደቡብ አፍሪካ በመጓዝ ላይ ከነበሩት 13 ተጓዦች ውስጥ ባጋጠማቸው የጀልባ መገልበጥ አደጋ ሰባቱ መሞታቸውን ማክሰኞ ዕለት የታንዛኒያ ፖሊስ አስታውቋል።
ጀልባዋ ሰኞ ማለዳ ላይ ህንድ ውቅያኖስ የኬኒያ እና የታንዛኒያ የባህር ዳርቻ በጀልባ ጉዞዋቸውን በማድረግ ላይ እያሉ አደጋው እንዳጋጠማቸው የአገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል።
የታንጋ ግዛት ፖሊስ ኮማንደር ኤዲዋርድ ኩሞንቤ እንዳሉት ”ከተጓዦቹ መሃከል12ቱ ኢትዮጵያዊያን ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ አንዱ የሌላ አገር ዜጋ ያለው የጀልባዋ ካፒቴን ነበር። ዜግነቱን ግን ማረጋገጥ አልቻልንም። ምክንያቱም እስካሁን ድረስ አልተያዘም። ሰባቱ ወዲያውኑ ሲሞቱ አምስቱ በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ደርሶባቸዋል። አድራሻውን አጥፍቶ የተሰወረውን ካፒቴን ለመያዝ ፖሊስ አሰሳውን አጠናክሮ ቀጥሏል።” ሲሉ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።
የታንዛኒያ የስደተኞች ቢሮ የሟቾቹን ኢትዮጵያዊያን የቀብር ስነስርዓት አፈጻጸም ከኢትዮጵያ ኤንባሲ ጋር በጋራ በመተባበር ለማስፈጸም እንቅስቃሴ መጀመሩን ዴይሊ ኔሽን ዘግቧል።
በተያያዥ 20 ህገወጥ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ በታንዛኒያ አቆራርጠው ሲገቡ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ካለ ህጋዊ ፍቃድ መግባታቸውን ተከትሎ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንደሚታይ ፖሊስን ጠቅሶ ኒውስ አፍሪካ ዘግቧል።
ከኬንያ ሞምባሳ ተነስተው ወደ ታንዛንያ በጀልባ በመጓዝ ላይ እያሉ በደረሰ የመስጠም አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ስምንት ኢትዮጵያውያንን አስከሬን ወደ አገር ቤት ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዛሬ አስታውቋል።
የኬኒያው ዴይሊ ኔሽን ሰባት ኢትዮጵያዊያን መሞታቸውን ሲገልጽ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር በበኩሉ ቁጥራቸውን ስምንት አድርሶታል። አንዱ ሟች ኢትዮጵያዊ ከጉዳተኞቹ መሃክል ይሁን አይሁን እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

Tuesday, October 16, 2018

የአሰቦት ገዳም መነኮሳት የድረሱልን ጥሪ አሰሙ


በምዕራብ ሐረርጌ ሜኤሶ ወረዳ የሚገኘው የአሰቦት ገዳም መነኮሳት የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው ተባለ።
በታጣቂዎች ተከበናል፣ለቃችሁ ውጡ ተብለናል፣ የሚደርስልን የለም የሚሉት የገዳሙ መነኮሳት በተኩስ ድምጽ ተሸብረናል በማለት ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥሪ አቅርበዋል።
ፋይል
ከጥቅምት ሰባት ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ከፍተኛ ማዋከብ እየተፈጸሙ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።
የሜኤሶ ወረዳ አስተዳዳሪ ከታጣቂዎቹ ጎን በመሆን ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ መነኮሳቱ ላይ ጫና እየፈጠሩ መሆኑም ተገልጿል።
መነኮሳቱ ቤተክህነትና መንግስት እንዲደርስላቸው ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትሪያትክ አቡነ ማቲያስ  እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ ካህናትንና ክርስቲያኖችን ማጥቃትና ማፈናቀል ቤተክርስቲያንን የማዳከም አንዱ ስልት ነው ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።
የተመሰረተው በ13ኛው መቶ ክፍለዘመን ነው። መስራቹ ደግሞ አቡነ ሳሙዔል ነበሩ።
በአህመድ ግራኝ የወረራ ዘመን ጥቃት ደርሶባቸው ከጠፉ ገዳማት አንዱ ነበር።
ከእነደገና የተቋቋመው በ1911 እንደኢትዮጵያ አቆጣጠር ነው።
በቀድሞ ሀረርጌ ክፍለሀገር በአሁኑ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረርጌ ሚኢሶ ወረዳ የሚገኘው የአሰቦት ገዳም፣ ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የተቆራኙ አጋጣሚዎችን አስተናግዷል።
በተለይም በሶማሊያ ወረራ ወቅት፡ በሶማሊያ ጦር ጥቃት የደረሰበት የአሰቦት ገዳም አብዛኛው ክፍሉ ወድሞ እንደነበር የታሪክ መጽሃፍት ያስረዳሉ።
በወረራው ጊዜ በገዳሙ የነበሩ ከ500 በላይ መነኮሳት ታቦት ይዘው አካባቢውን ጥለው የተሰደዱ ሲሆን ገሚሶቹ በሶማሊያ ጦር ታስረው ወደ ሞቃዲሾ መወሰዳቸውን ነው ለማወቅ የተቻለው።
ገዳሙ አሁን ያለበትን ገጽታ እንዲይዝና ዳግም እንዲሰራ ያደረጉት ቀዳማዊ ሃይለስላሴ እንደሆኑም ተመልክቷል።
በገዳሙ ታሪክ አሳዛኝ ተብሎ የሚጠቀሰው ሌላው ክፉ አጋጣሚ በ1984 ዓም እንደኢትዮጵያ አቆጣጠር በአክራሪ ታጣቂዎች በተወሰደ ርምጃ 16 የገዳሙ መነኮሳት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው እንደሆነም ማስታወስ ተችሏል።
ገዳሙ በተለያዩ ጊዜያት ፈተና ውስጥ የከተቱት አጋጣሚዎች የተፈጠሩ ቢሆንም ሰሞኑን የተከሰተው ግን አደገኛ እንደሆነ ነው ለኢሳት የደረሰው መረጃ የሚያመለክተው።
ሃራ ተዋህዶ የተሰኘው በቤተክርስቲያን ጉዳይ ላይ የሚያተኩረው ድረ ገጽ እንዳተተው የገዳሙ መነኮሳት የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው።
ካለፈው ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ ገዳሙ በታጣቂዎች ተወሯል። በቁጥር 25 የሚሆኑ በነፍሰ ወከፍ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች በገዳሙ ይዞታ በሆነው ደን ውስጥ ድንኳን ተክለው መነኮሳቱ ላይ በመተኮስ እያስፈራሩ ናቸው።
ታጣቂዎቹ የኦነግ ወታደሮች መሆናቸውንና በደን ውስጥ የሚገኙትም የሶማሌ ጦር ወደ ገዳሙ ይገባሉ የሚል መረጃ ደርሶን ነው በማለት ምላሽ ነው መስጠታቸውን ነው የተናገሩት መነኮሳቱ።
ሆኖም የኦነግ ታጣቂ መሆናቸውን የሚናገሩት ወታደሮች ገዳሙን ለቀን እንድንወጣ እያስፈራሩን ነው፣ ከበው በተኩስ እሩምታ ሰላም እያሳጡን ነው ያሉት መነኮሳቱ አቤት የምንልበት አጥተናል ብለዋል።
የሜኤሶ ወረዳ አስተዳዳሪ ለመነኮሳቱ ጥበቃ እንዲደረግ ከምዕራብ ሀረርጌ ዞን ትዕዛዝ ቢተላልፈላቸውም ተግባራዊ ከማድረግ ይልቅ ገዳሙን ከከበቡት ታጣቂዎች ጋር አብረው መነኮሳቱ አከባቢውን ለቀው እንዲሄዱ በማስፈራራት ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
ባለፈው ሰኞ ከምሽቱ 2 እስከ 4 ሰዓት የቀለጠ ድምጽ ይሰማ እንደነበርና በትላንትናው ዕለት ሌሊት ሁለት አብሪ ጥይቶች ወደ ገዳሙ መተኮሳቸውን ገልጸዋል።
መነኮሳቱ የ1984 ዓይነት ዕልቂት እንዳይደገም ስጋት ውስጥ ገብተናል ያሉ ሲሆን ቅዱስ ሲኖዱሱ ለኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እንዲያስታውቅላቸው ጠይቀዋል።
በጉባዔ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ፓትሪያርኩ አቡነ ማቲያስ ካህናትንና ክርስቲያኖችን ማፈናቀልና ማጥቃት ቤተክርስቲያኒቱን ለማዳከም እየተወሰዱ ካሉ ስልቶች አንዱ ነው ማለታቸው ተገልጿል።

በነጭ ሳር ፓርክ ታጣቂዎች ተጣቂዎች ቢያንስ 4 ሰዎችን ገደሉ


በነጭ ሳር ፓርክ ታጣቂዎች ተጣቂዎች ቢያንስ 4 ሰዎችን ገደሉ
  በአርባምንጭ ከተማ ዙሪያ በሚገኘው የነጭ ሳር ፓርክ ውስጥ የመሸጉ ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ 4 ሰዎች ሲገደሉ 3 ሰዎች ደግሞ ክፉኛ መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ጥቃቱን የኦነግ ታጣቂዎች እንዳደረሱት ይናገራሉ
ኢሳት የአካባቢውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካለትም።
በሌላ በኩል የነጭ ሳር ፓርክ ብሄራዊ ጽ/ቤት ለደቡብ እና ኦሮምያ ክልሎች በጻፈው ደብዳቤ “ በፓርኩ ምስራቃዊ ክፍል በፓርኩ ውስጥ የሚኖሩ የጉጂ ማህበረሰብ በተፈጥሮ ሃብቱ ላይ እያደረሱ ያለው ውድመት ከፓርኩ ጽ/ቤት አቅም በላይ ከመሆኑም ባሻገር በጥበቃና ቁጥጥር ሰራተኞቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ጫና ከአቅም በላይ በመሆኑ እንዲሁም ከፓርኩ ጥበቃና ቁጥጥር ሰራተኞች በተሻለ መልኩ በሚገባ የጦር መሳሪያ የታጠቁ አካላት በመሆናቸው ችግሩን አስከፊ አድርጎታል” ብሎአል።
የሚመለከታቸው አካላት በአመት እስከ 4 ሺ የውጭና አገር ውስጥ ጎብኝዎችን የሚያስተናግደውን ፓርክ እንዲታደጉት የፓርኩ ጽ/ቤት ጥሪ አቅርቧል።

Monday, October 15, 2018

የአፋር ልዩ ሃይል የተቃውሞ ሰልፍ ባደረጉ ወጣቶች ላይ ጉዳት አደረሰ


 በአዋሽ ሰባተኛ የአፋር ልዩ ሃይል የተቃውሞ ሰልፍ ባደረጉ ወጣቶች ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸሙ ተገለጸ።
በአፋር ክልል የተጀመረው ህዝባዊ ተቃውሞ በቀጠለበት በዚህን ወቅት ልዩ ሃይሉ አዋሽ ሰባተኛ ላይ የወሰደው ርምጃ ቁጣን ቀስቅሷል።

በርካታ ወጣቶች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአይን እማኞች ገልጸዋል።
የአፋርን ክልል የሚመራው ፓርቲ ለውጥ አደናቃፊ ነው በሚል በክልሉ በአብዛኛው አከባቢ የተጀመረው ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ህወሃት በአፋር ክልል የሚያደርገው ጣልቃ ገብነት የተቃውሞው አንዱ ጥያቄ መሆኑም ይነገራል። አፋሮች ፌደራል መንግስቱ ድምጻችንን ይስማ በማለት ላይ ናቸው።
አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ የአፋር ክልል ገዢ ፓርቲ አብዴፓ ለሁለት መሰንጠቁ ተሰምቷል።
አዋሽ ሰባተኛ ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ በሚወስደው መስመር ላይ የምትገኝ አነስተኛ ከተማ ናት።
ካለፈው ወር ጀምሮ በመላው አፋር ክልል የተነሳው ተቃውሞ አዋሽ ሰባተኛ ዛሬ ሲደርስ የገጠመው ብርቱ የታጣቂ ሃይል ርምጃ ነበር።
የአፋር ክልል አመራሮች ከስልጣን እንዲወርዱ በመጠየቅ የተጀመረው ተቃውሞ በአዋሽ ሰባተኛ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ከሆነ የአዋሽ ሰባተኛው የተቃውሞ ሰልፍ ከወረዳው አስተዳደር ፍቃድ ተነፍጎት ነበር።
ወጣቶቹ ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ አይጠበቅብንም ብለው በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ለማድረግ አደባባይ ሲወጡ የአፋር ክልል ልዩ ሃይል ርምጃ መውሰዱን ነው የደረሰን መረጃ ያመለከተው።
በቆመጥና በመሳሪያ ሰደፍ ከፍተኛ ድብደባ የፈጸመው የአፋር ክልል ልዩ ሃይል የተቃውሞ ሰልፉ እንዲበተን አድርጎታል።
በዚህ ጥቃት ከ20 በላይ ወጣቶች ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መግባታቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ባለፈው ሳምንት በዘጠኝ የአፋር ክልል ወረዳዎች በተካሄደ ተቃውሞ የክልሉ ገዢ ፓርቲ ስልጣን እንዲለቅና በሃገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው ለውጥ ወደ አፋር እንዲገባ ተጠይቋል። መደመርም የአፋርን መሬት ይርገጥ ብለዋል ወጣቶቹ።
አሁን በደረሰን ዜና ደግሞ የአፋር ክልል ገዢ ፓርቲ አብዴፓ ለሁለት ተሰንጥቋል።

ለውጡን በሚደግፉና የነበረውን ስርዓት በሚያስቀጥሉ የፓርቲው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል በተፈጠረ ልዩነት ፓርቲው ለሁለት መከፈሉን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በህወሃት ይደገፋሉ የተባሉት የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ስዩም አወልን ጨምሮ 19ኝ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ለውጡን እንደሚያደናቅፉና በነበረው አመራር ክልሉ መቀጠል አለበት ብለው አቋም የያዙ መሆናቸው ታውቋል።
የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት የሚመሩትና 17 ተጨማሪ አባላት ያሉት ሁለተኛው ቡድን የአፋር ህዝብ ለውጥ ያስፈልገዋል፣ አሁን ያለው አመራር ስልጣን ይልቀቅ የሚል ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ዛሬ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ስዩ አወል ምክትላቸውን ጨምሮ 18ቱን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ዛሬ ማገዳቸው ተሰምቷል።
የአቋም ልዩነት ያሳዩትና ለውጡን የሚደግፉት አባላትም ፕሬዝዳንቱን ማገዳቸው ታውቋል።
የአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ አብዴፓ በህዝቡ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ ምክንያት ለሁለት መሰጠንቁን ተከትሎ የጎሳ ግጭት ይከሰታል የሚል ስጋት እንዳለም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

Sunday, October 14, 2018

ዛሬ በአዳማ( ናዝሬት) የአርበኞች ግንቦት 7 አቀባበል፣









ዜጎች በኩልነት የሚኖሩባትና ዲሞክራሲያዊትና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚታገለውን አርበኞች ግንቦት 7 ለመደገፍ የወጣው የናዝሬት ህዝብ ነው። በኦሮሚያ ክልል ህዝቡ በነቂስ አደባባይ በመውጣት የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮችን በደመቀ ሁኔታ ተቀብሏል።


በአዳማ ስታዲየም በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖች በተገኙበት በተደረገው በዚሁ አቀባበል ላይ የንቅናቄው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተገኝተዋል:: ፕሮፌስሩ በስታዲየሙ ባደረጉት ንግግርም "የብሄር ፓለቲካ የነጻነትና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ዋስትና ቢሆን ኖሮ የሶማሌ ክልል ተወላጆች በገዛ 'ወገናቸው' አብዲ ኢሌ ፍዳቸውን ባልቆጠሩ ነበር። ከእኔው ' ዘር ' ብሄር የሆነ ዕብድ ይጨቁነኝ ብሎ ፓለቲካ አይሰራም ፤ ዜጎች በመላ ሀገሪቱ በነጻነት የሚኖሩበት ስርዐት መገንባት ምርጫ አይደለም ግዴታ ነው።" ብለዋል:: የአዳማ ከተማ ህዝብ ዘረኝነትን በጽኑ የሚያወግዙ መፈክሮችን አንግቦ ኢትዮጵያዊነትን በማወደስ ላይ ነበሩ።

ከአፍሪካ በዘረኝነት (በህግ አልባነት) ቀዳሚው አየር መንገድ #የኢትዮጵያ አየር መንገድ (

ከአፍሪካ በዘረኝነት (በህግ አልባነት) ቀዳሚው አየር መንገድ #የኢትዮጵያ አየር መንገድ (በዛዊት ዳኛቸው) July 2018
ከዚህ በፊት በማህበራዊ ሚድያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስር ቤት እንዳለው ይፋ የወጣበትን ጽሁፍ ሳነብ እኔም ከዚህም በላይ በዘረኝነት እና ኢፍታሀዊነት እንደተዘፈቀ የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቀው ዘንድ እንሆ ብያለሁ።
ከአየር መንገዱ (የኢትዮጵያ የሚለውን የክብር ስም ከፊቱ ለማድረግ እቸገራለሁ) ለአመታት ካገለገልኩ በኋላ ምክንያቱን ባላወኩት ሁኔታ ከስራ እባረራለሁ። እኔም ይህንኑ በመቃወም ክስ ፍ/ቤት መስርቼ ለሁለት አመታት እስከ ሰበር ችሎት ከተከራከርኩ እና ከፍተኛ አንግልት ከደረሰብኝ በኋላ ወደስራ ገበታዬ እንድመለስ ውሳኔ አገኘሁ። ከዚህ በኋላ ነው ታሪኩ የሚጀምረው ።
ፍርድ ቤቱ በውሳኔው መሰረት ወደ ስራ እንድመለስ ትእዛዝ መስጠቱን ተከትሎ አየር መንገዱ ወደ ስራዬ መመለስ እንደማልችል እና በምክንያትነትም ለሀገር ደህንነት የማሰጋ በመሆኑ ወደስራ ለመግባት የሚያስችል የይለፍ መታወቂያ (security pass) የኤርፖርት ደህንነት ቢሮ እንደማይሰጠኝ አሳውቆናል የሚል ደብዳቤ ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል። ፍርድ ቤቱም ከደህንነት መስሪያ ቤቱ እና ከህግ በላይ ከሆነው አየር መንገድ ጋር በመወገን ለአመታት የተንከራተትኩበት መብቴ ላይ ውሀ በመቸለስ መዝገቡን ዘግቶ አሰናብቶኛል።
እኔ አልፎ አልፎ በማህበራዊ ሚዲያ ከምለቃቸው ለፖለቲካ የቀረቡ ጽሁፎች በስተቀር ምንም አይነት እንቅስቃሴ የማላደርግ በመሆኑ ነገሩ በከፍተኛ ሁኔታ ህሌናዬን ስለቆረቆረው አንድ አመት የፈጀ በግሌ ጥናት አድርጌ የደረስኩበት እንሆ ውጤቱ። በመጀመሪያ ደረጃ ከስራ የተሰናበትኩት በማህበራዊ ሚድያ በፃፍኩት ጽሁፎች መሆኑን በአሁኑ ጊዜ በተለያየ ምክንያት ከስራ የተሰናበቱ የአየር መንገዱ የ SECURITY ክፍል የቀድሞ ባልደረቦች አረጋግጠውልኛል። እነዚህ ሰዎች በማስረጃ አስደግፈው እንዳብራሩልኝ በአየር መንደጉ SECURITY ክፍል የሰራተኞቹን የማህበራዊ ሚድያ እንቅስቃሴ የሚከታተል (MONITOR) የሚያደርግ እና በተወልደ የሚመራ ግብረሀይል ከ Zone 9 ክስተት በኋላ ተቋቁሞ እንደነበረ (የዞን ዘጠኝ አንዱ አባል ማለትም አቤል ዋበላ የአየር መንገዱ ሰራተኛ የነበረ በመሆኑ) እና በዚህ ግብረሀይል አማካኝነት ማንኛውም በማህበራዊ ሚዲያ የመንግስትን ስም በመጥፎ የሚያነሳ ወይም እንደ ጃዋር እና ኢሳት የመሳሰሉትን የሚከታተል(Like ያደረገ) ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲባረር መመሪያ ወርዶ የነበረ በመሆኑ እና በዚህ መሰረትም እኔን ጨምሮ ከ 30 ያላነሱ ሰራተኞች የተለያየ ምክንያት እየተለጠፈባቸው መባረራቸውን ለማወቅ ችያለሁ።
በዚህ ህገወጥ ግብረሀይል ሰራተኞች እንዲባረሩ ከተደረጉ በኋላ እንደ እኔ ደፍሮ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት አቅርቦ ውሳኔ የሚያገኝ ካለ ደግሞ ተወልደ ለፍትህ እና ለህግ ካለው ንቀት የተነሳ 25 ኪሎግራም ወርቅ በመስረቅ ተጠርጥሮ ነገርግን እንደሌሎች ተጠርጣሪዎች ክስ ሳይቀርብበት በጡረታ እንዲገለል ከተደረገው የቀድሞው የአየር መንገዱ SECURITY ክፍል ሀላፊ ከነበረው አቶ ብርሀነ መልካ በትግል ስሙ ወዲ ራያ ( በነገራችን ላይ ይህ ሰው የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሀላፊ የነበረ እና በሌብነት እና ጉቦ ተገምግሞ ከተሰናበተ በኋላ በግል ከተወልደ ጋር ባለው ትውዉቅ በአየርመንገዱ የተቀጠረ ነው) ጋር በመሆን የኤርፖርት ደህንነትን በማነጋገር ፋይል ቁጥር ያልያዘ ደብዳቤ ለፍርድ ቤት security pass እንደማይሰጥ በመጻፍ ከፍተኛ የሆነ አሻጥር እንደሚፈጸም እና ፍርድ ቤቱም ይህን እያወቀ ወይም በግዴለሽነት ከ10 በላይ ሰራተኞች ጉዳይ በዚህ ሁኔታ መዝጋቱን ለማረጋገጥ ችያለሁ።( በነገራችን ላይ አሁን በዶክተር አብይ አስተዳደር የአየር መንገዱ የህውሀት አባላት ሰራተኞች ለምሳሌ ካለ ብቃቱ manager HR customer service የሆነው እንደርታ መስፍን በአብይ አስተዳደር ላይ ለስራ የተሰጠ ነጻ ኢንተርኔት እና ዴስክ ቶፕ በመጠቀም የሚጽፉትን የጥላቻ እና የፕሮፓጋንዳ መልእክት ሳይ አይ ይች ሀገር አብዛኛው የእንጀራ ልጅ ጥቂቱ የእናት ልጅ የሆነባት ያሰኘኛል)።
በነገራችን ላይ አየር መንገዱ የደህንነት መስሪያ ቤቱን እና የአየር መንገዱን SECURITY ክፍል ለህገወጥ profiling መጠቀም የጀመረው ከ 2011 እ.ኤ.አ ጀምሮ (ማለትም ተወልደ ዋና ስራ አስፈጻሚ ከሆነ ጊዜ) ነው። ማንኛውም የአየር መንገዱ ተቀጣሪ የጽሁፍ እና የቃለመጠይቅ ፈተና ማለፉ ከተነገረው በኋላ አይደለም በኢትዮጵያ በአለም ላይ የሌለ ሴኩሪቲ ቼክ የሚባል አሰራር ዘርግቷል። ይህም የተቀጣሪው የዘር ማንነት እና የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ የሚፈተሽበተ ሲሆን ፣ ተቀጣሪው በዚህ የግብዞች መለኪያ ካላለፈ ቅጥሩ ውድቅ ይደረጋል። በዚህ ሁኔታ ስንቶች ስራ አገኘን ካሉ በኋላ የውሀ ሽታ ሆኖባቸዋል።
በሌላ በኩል ፍርድ ቤቶች የአየር መንገዱን ጫና ተቋቁመው የተባረረ ሰራተኛ ወደስራ እንዲመለስ ከገፉበት እና ሰራተኛው የሚሰራበት ክፈል security pass የማያስፈልገው ከሆነ አየር መንገዱ ፍርድ ቤት ቀርቦ ሰራተኛውን መልሻለሁ ብሎ ምሎ ከተገዘተ በኋላ በ 3ኛ ው ቀን ሰራተኛው የብሄር ማንነቱ እየተጣራ ስራውን ለመቀጠል ወደሚቸገርበት ቦታ እና የስራ መደብ ማዛወር በጣም የተለመደ ነው ። ለምሳሌ ኦሮሞ ከሆነ ወደ ሶማሌ ክልል አማራ ከሆነ ወደ ትግራይ ወይም አፋር ይመደባል። ይህ አሰራረ ያልተጻፈ ግን ያለማዛነፍ የሚተገበር መሆኑን እያንዳንዱ በፍርድ ቤት የተመለሰ ሰራተኛ ባለፉት 5 አመታት ወደ ቀድሞ የሰራ ገበታው ያልተመለሰ መሆኑን ማንም ሰው መለስተኛ ጥናት በማድረግ ማረጋገጥ ይችላል።
አየር መንገዱ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚታወቅ እና ማስቲካ በስራ ላይ አላመጥክ፣ ጸጉርህን አከክ እያለ ሰራተኛ እንደሚያባርር ይታወቃል። ነገር ግን ይህ የሚሰራው ከተወልደ ጋር አንድ አይነት ዘር የሌለህ ብቻ ከሆነ መሆኑን የሚከተሉት ማሳያዎች ፍንትው አድርገው ያረጋግጣሉ።
በቅርቡ ካለሽፍቱ ስራ ገብቶ እና አጭበርብሮ ለትግራይ ልማት ማህበር ስብሰባ ነው የምሄድ የምትል ሰው በነጻ ወደ መቀሌ ያሳፈረ ሰራተኛ ከስራ በተሰናበተ በሳምንቱ ተወልደ ከፍተኛ ተግሳጽ እና ቅጣት ባባረሩት የስራ ክፍል ሀላፊዎች ላይ በማድረስ ወደስራው ተመልሷል።
ከ 2 አመት በፊት በ ሰው ሃብት ቅጥር ክፍል የተመደበ ጀማሪ ሰራተኛ በአየር መንገዱ የጥገና ክፍል የሚሰራ ሌላ ማንነቱ ከወደ መቀሌ የሚመዘዝ ሰራተኛ ዘመዱን ለማስቀጠር በጉቦ መልክ ገንዘብ ሰጥቶኛል በማለት ለአለቃው ያሳውቃል። ብታምኑትም ባታምኑትም ይህ ሰራተኛ ከስራ ሲሰናበት ጉቦ ሰጭው በስራው ላይ ቀጥሏል።
የአክሱም ትኬት ሽያጭ ቢሮ ሰራተኛ የነበረ እና ከስልጠና ጊዜ ጀምሮ ሌሎች ሰልጣኞችን በመደባደብ እውቅና ያተረፈ ከአለቆቹ አቅም በላይ በመሆኑ እና ለተከታታይ 7 ቀናት ያለ አለቃው ፍቃድ ከስራ በመቅረቱ በማባረሩ ለተወልደ አቤቱታ አቅርቦ የይስሙላ አጣሪ ኮሜቴ በማቋቋም ወደስራው ለመመለስ በሂደት ላይ እያለ የአየር መንገዱ ሰራተኞች የያዘ መኪና ላይ ከ4 ወር በፊት ቦምብ አፈንድቶ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ በእስር ላይ የሚገኝ ሲሆን( አንዳንዶቹ ተፈትቶ ወደስራ ተመልሷል ይላሉ) ጉዳዩ ወደህዝብ ጆሮ እንዳይደርስ አየር መንገዱ አፍኖ መያዙ ለምንድ ነው?
በአጠቃላይ አየር መንገዱ ከቅጥር ጀምሮ እስከ ማሰናበት ድረስ መለኪያው ዘር እና ኢፍታሀዊነት መሆኑን ባደረኩት ጥናት ያረጋገጥኩ ሲሆን፣ ለዚህ እንዲረዳውም ተወልደ ከተሾመበት 2011እ.ኤ.አ ጀምሮ በምንም መመዘኛ የአየር መንገዱን መስፈርት የማያሟሉ ከአድማስ ኮሌጅ እና መሰሎቹ በተመረቁ በአብዛኛው የአንድ ብሄር ተወላጆች የቅጥር ክፍሉ እንዲመራ እየተደረገ ይገኛል( ከ2012- 2014 ደሳለኝ ከ 2014 -2017 እምባየነሽ አርአያ በአሁኑ ጊዜ ገብረዮሀን ወ ገብርኤል)።
ከ 7 ወይም 8 አመት በፊት የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች VP and CXO የሚባሉት የሚያዙት ብቃት እና ብቃትን ብቻ መሰረት አድርጎ ነበር። በአሁኑ ጊዜ ግን ከ 15ቱ አመራር 7ቱ የአንድ ብሄር አባላት ( ተወልደ ፣ ፍጹም MD Cargo( የተወልደ ተተኪ)፣ ኢሳያስ VP International Services፣ ዘላለም MD MRO( እጅግ በሙያው የተከበረውን አቶ ዘመነን በearly retirement በማባረር የተተካ)፣ ሚካኤል VP Customer services፣ ተክሌ MD Ground services እና አክሊሉ MD Catering)፣ ቴዎድሮስ (Airport enterprise) የተሰገሰጉበት እና አንድም የኦሮሞ ብሄር የሌለበት ስብስብ ሆኗል።
የአየር መንገዱ የቦርድ አባላትም ይህን እያወቁ ተወልደን በመፍራት እንዳላዩ በመምሰል አንድም ጊዜ ከሰራተኛው ጋር ተወያይተው የማያውቁ እና በየወሩ በመሰብሰብ እያጨበጨቡ አበል የሚበሉ የቀን ጅቦች ሆነዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴም አየር መንገዱ ከህግ በላይ ይመስል በታሪኩ አንድም ጊዜ እንኳን የአየር መንገዱን የስራ አፈጻጸም ገምግሞ አያውቅም። በመሆኑም አዲሱ የአብይ አስተዳደር በአፋጣኝ ጥልቅ ምርመራ በማድረግ ይህን ግፍ እና ዘረኝነትን ከፍ አድርጎ የሚያበር አየር መንገድ አደብ ሊያስይዘው ይገባል።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት መ/ቤት በተሰጠ ትእዛዝ ከስራ የተሰናበትንበት ደብዳቤ !

No automatic alt text available.
No automatic alt text available.
No automatic alt text available.Image may contain: 2 people, selfie and closeup

በቡራዩ ነጋዴዎች የንብረት ካሳ አለማግኘታቸውንና ስራም አለመጀመራቸውን ገለጹ


በቡራዩ ነጋዴዎች የንብረት ካሳ አለማግኘታቸውንና ስራም አለመጀመራቸውን ገለጹ
ባለሆቴሎቹ ለኢሳት ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ለደረሰው የንብረት ውድመት የከተማው መስተዳድር የወደመውን ንብረት ምዝገባ እና ግምት ቢያካሂድም እስካሁን ወደስራ እንዲመለሱ ለማድረግ ይህ ነው የሚባል ተግባር አላከናወነም፡፡
የቡራዩ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሃላፊ በበኩላቸው የወደመውን ንብረት የመመዝገቡ ስራ በቀጣዩ ሳምንት እንደሚጠናቀቅ ገልፀዋል፡፡
ለተፈናቃዮቹ ማቋቋሚያም ሆነ ለደረሰው የንብረት ውድመት ካሳ ተብሎ የተሰበሰበው ገንዘብ ለታለመለት አላማ እንዲውል ከሚመለከተው አካል ጋር በቅርበት እየሰሩ መሆናቸውንም አስታውቀዋል፡

በግፍ የተባረረውን የአቶ ወረታው ዋሴ እና የአየር መንገድን ክርክር ተመልከቱ!
…………………………………………
ዜጎችን በፖለቲካ አመለካከታቸውና በዘራቸው ምክንያት አልበደልኩም የሚለው "የኢትዮጵያ አየር መንገድ"

......
በዘራቸውና በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት በብዙ ዜጎች ላይ በደል ሲፈፅም የምናውቀው "የኢትዮጵያ አየር መንገድ" ሰሞኑን ደግሞ አዲስ ርዕስ ሆኖ ስለመጣ "አንተም ሰለባ ነበርክና እስኪ የምታውቀውን ለህዝብ አድርስ" በማለት ብዙ ጓደኞቸ ስለጠየቁኝ በሌሎች የስራ ባልደረቦቸ ላይ የደረሰውን ለሌላ ጊዜ ላቆየውና እኔን ያጋጠመኝን በአጭሩ ከሰነዶች ጋር አያይዤ ላቅርብ።
....
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ" "ዜጎችን በዘራቸው እየለየ እና የፖለቲ ቁንጮውን ህወሃትን የሚቃወሙትን እየሰለለ ልዩ ልዩ በደል ያደርሳል" እየተባለ ለሚቀርብበት ክስ ለማስተባበል "በሰራተኞቹ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች በህግና በደንብ መሰረት ብቻ እንደሆነ እየነገረን ይገኛል። ይህ ማስተባበያ ሃሰት እንደሆነ ለማሳየት በእኔ የደረሰውን እንደ አንድ ማስረጃ መውሰድ ይቻላል።
......
እ.ኤ.አ በ2011 "ለአባይ ግድብ ገንዘብ የምናዋጣበትን ሁኔታ ለመወያየት በስብሰባ እንድትገኙ" የሚል መልዕክት ድርጅቱ በሰጠኝ "ኢ-ሜይል ደረሰኝ። እኔ ስብሰባ መሳተፍ እንደማልፈልግ፣ ገንዘብም ካለእኔ ፈቃድ ከደመወዜ እንዳይቆረጥ ይህን ካደረጋችሁ በህግ እንደምጠይቅ ጠቅሼ በዚያው መልዕክቱ በመጣልኝ ኢ-ሜይል ምላሽ ፃፍኩ። ይህም "የኢንዱስትሪ ሰላም ለማናጋትና ሰራተኛውን ለማሳመፅ" የሚል ታርጋ ተሰጥቶት ያለምንም ማስጠንቀቂያ ከስራ የሚያባርር ደብዳቤ አመጣልኝ። ከሁለት ዓመት በላይ ክርክር በስር ፍርድ ቤት የተረታው "አየር መንገድ" እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ይግባኙን ውድቅ አድርጎ ወደ ስራዬ እንድመለስ ተወሰነ። ነገር ግን በፍርድ ቤት ያልሆነላቸውን ለመበቀል ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በማቀድ ቀድሞ ስሰራበት ወደነበረው ክፍል ሳይሆን ፈፅሞ ከእኔ ስራ ግንኙነት ወደሌለው ክፍል "ሱፐርቫይዘር" ሆነህ ተመድበሃል የሚል ደብዳቤ ተሰጠኝ። ወደ ስራ ተመልሸ በአየር መንገዱ በቆየሁበት አንድ አመት ከአምስት ወር ውስጥ በርካታ ትንኮሳዎችና ተማርሬ በራሴ ለቅቄ እንድሄድ የሚያደርጉ ሸፍጦች አጋጥመውኛል። በመጨረሻም "ከስርህ የሚሰራ ሰራተኛ ጥፋት አጥፍቶ እያለ አፋጣኝ እርምጃ አልወሰድክም" ተብዬ ከስራ ለሁለተኛ ጊዜ ተባረርኩ። አሁን እንዴት በህግና በደንብ መስረት እንደተሰራ እንመልከት።
.......
1ኛ. የእኔ ጥፋት ሆኖ የተቆጠረው ሰራተኛው እ.ኤ.አ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ጥፋት አጥፍቶ እያለ እስከ ጥቅምት 20 ቀን ድረስ እርምጃ አልወሰድክበትም" ነው። (አንደኛውን ደብዳቤ ተመልከቱ)
2ኛ. ነገር ግን ጥፋት አጠፋ የተባለው ሰራተኛ እ.ኤ.አ ከጥቅምት 2 ቀን 2014 ጀምሮ ከስራ ታግዶ እንደቆየና ጥፋቱም ተመርምሮ ከስራ የሚያባርረው ባለመሆኑ ወደስራው መመለሱን ያሳያል። (ሁለተኛውን ደብዳቤ ተመልከቱ)
3ኛ. አቶ ተወልደ ገ/ማርያም እኔን ለማባረር ሰራተኛው ያጠፋው ጥፋት ትልቅ እንደነበርና በድርጅቱም ላይ ጉዳት እንዳደረሰ ቢገልፅም (ሶስተኛውን ማስታወሻ ተመልከቱ) ሰራተኛው አጠፋ የተባለው ግን ተጣርቶ ቀላል እንደነበር በራሱ በአየር መንገዱ ተወስኖ ሰራተኛው ወደ ስራው እንዲመለስ ተደርጓል። (ሁለተኛውን ደብዳቤ ተመልከቱ)
4ኛ. አቶ ተወልደ "ሰራተኛችን በዘራቸውና በፖለቲካ አመለካከታቸው አናጠቃቸውም" ቢሉም የፖለቲካ ተሳትፏችን እየተሰለለ ለማባረሪያነት ይጠቀሙ እንደነበረ አየር መንገዱ እኔን አስመልክቶ ሳያፍር ለፍርድ ቤቱ የፃፈውን አራተኛውን ደብዳቤ ተመልከቱ።
በአጠቃላይ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ" ምን ያህል በተበላሸ፣ በወንጀለኞችና በአናሳ የህወሃት የስለላ መዋቅር የሚገዛና ይህንን አገዛዝ ይቃወማሉ ያሏቸውን ሰዋች በስራ እድገትና ምደባ ከመበደል አልፈው እስከማሳሰርና ማባረር ድረስ ግፍ የሚፈፀምበት ተቋም እንደሆነ በርካታ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል።
Image may contain: text
No automatic alt text available.
No automatic alt text available.

Ethiopia: Scaffolding on Lalibela rock-hewn churches damages structure

by Engidu Woldie
ESAT News (October 9, 2018)
Scaffolding erected ten years ago at the site of UNESCO heritage rock-hewn churches of Lalibela is causing structural damages to the historic site, priests and residents of the tourist town said.
The priests and residents of Lalibela who took to the streets on Sunday to vent their concern said the scaffolding that was put together for the purpose of protecting the historic site from natural disasters was actually causing more damages to the rock-hewn churches.
The residents say they have communicated their concerns to authorities but nothing has been done to reverse the damages being done on the churches.
Experts have warned repeatedly that the scaffoldings would do more harm than good to the site.
The rock-hewn churches of Lalibela have been a main attraction to tourists travelling to Ethiopia but residents of the town and priests at the church say authorities have not given due attention to the structure that is cracking from the weight of the scaffolding.
The eleven monolithic churches were carved in the 13th century and are listed as one of UNESCO World heritage sites.

Friday, October 12, 2018

የቅዱስ ላሊበላን ገዳማት እድሳት በተሟላ መልኩ ለማከናወን 3 መቶ ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ የላሊበላ ገዳም አስተዳዳሪዎች እና የከተማው መስተዳደር አስታወቁ፡፡

No automatic alt text available.

ከ 10 ዓመት በፊት በአውሮፓ ህብረት እና በተባበሩት መንግስታት የሳይንስ እና የባህል ተቋም-ዩኔስኮ ድጋፍ የተሰራው ጊዚያዊ መጠለያ በተገቢው መንገድ በሚነሳበት እና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ጥገና የሚካሄድበት መንገድ ጥናቱ መደረጉን የላሊበላ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ለኢሳት ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ባሏት ቅርሶች ልክ የጥበቃ ፣የደህንነትም ሆነ የጥገና ባለሙያዎችን የሚያፈሩ ኮሌጆችንም ሆነ ዩኒቨርስቲዎችን- በቤተክርስቲያኗም ሆነ በመንግስት ደረጃ ማቋቋም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ምሁራን ያስገነዝባሉ።


Image may contain: one or more people, people standing and outdoor


No automatic alt text available.

Thursday, October 11, 2018

ከቤንሻንጉል የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ70ሺህ በለጠ

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ70ሺህ መብለጡ ተገለጸ።

የሞቱት ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ40 በላይ መድረሱ ታውቋል።
ሁለት ነፍሰጡሮች በሽሽት ላይ እያሉ መንገድ ላይ መውለዳቸውም ተመልክቷል።
የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ካማሼ ዞን አመራሮች ከምዕራብ ኦሮሚያ አስተዳደር ጥምር ኮሚቴ ጋር የነበራቸውን ስብሰባ አጠናቀው ሲመለሱ በተሰነዘረባቸው ጥቃት አራት አመራሮች መገደላቸው ለግጭቱ መቀስቀስ ምክንያት እንደሆነም ተመልክቷል።
መስከረም 16 ቀን 2011 አራት የካማሼ ዞን ባለስልጣናት በታጣቂ ሃይሎች መገደላቸውን ተከትሎ ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ማሻቀቡን  የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት ገልጸዋል።
በአብዛኛው የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች በተፈናቀሉበት በዚህ ክስተት ሁለት ነፍሰ ጡር እናቶች መንገድ ላይ መገላገላቸውም ተመልክቷል።
በአጠቃላይ የተፈናቃዮቹ ቁጥር 70ሺ መድረሱም ታውቋል።
የካማሽ ዞን ባለስልጣናት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከስብሰባ ሲመለሱ መገደላቸውን ተከትሎ በሰላማዊ ነዋሪዎች ላይ በደረሰው የአጸፋ ጥቃት ከ40 ሰዎች መገደላቸውን የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደርና ጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ታከለ ቶኩማ ለመገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።
ለ70ሺ ሰዎች መፈናቀሉ ምክንያት በሆነውና ከ40 በላይ ሰዎች በተገደሉበት በዚህ ጥቃት ከ200 በላይ ቤቶች መቃጠላቸውም ተመልክቷል።
በሎይ ጅጋንፍ ወረዳ ዳለቻ እና ታንኮና የተባሉ ቀበሌዎች ችግሩ በዋናነት የተፈጠረባቸው እንደሆኑም ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም በተፈጠረው ቀውስ የተፈናቀሉ 70ሺ ዜጎችን ለመታደግ የባንክ ሒሳብ መከፈቱን የኦሮሚያ ክልል የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክና በኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ተፈናቃዮቹን ለማቋቋም የባንክ ሒሳብ መከፈቱ ይፋ ሆኗል።


 

አቶ ሌንጮ ለታ ወጣቱ በባዶ እጁ ታንክ ፊት በሚጋፈጥበት ጊዜ የኦነግ ሰራዊት የት ነበር አሉ

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር ሊቀመነበር አቶ ሌንጮ ለታ ኦነግ ትጥቅ አልፈታም ማለቱ ተገቢ አይደለም አሉ።
ወጣቱ በባዶ እጁ ታንክ ፊት በሚጋፈጥበት ጊዜ የኦነግ ሰራዊት የት ነበር ሲሉ አቶ ሌንጮ ለታ በሀገር ውስጥ ከሚሰራጨው አሀዱ ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ ገልጸዋል።
ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት ከፈለግን በሀገር ውስጥ መኖር ያለበት ሰራዊት የመንግስት ብቻ መሆን አለበት ያሉት አቶ ሌንጮ ለታ የኦነጉ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ የተናገሩት ግራ የሚያጋባ ነው ብለዋል።
የኦነግ ሰራዊት የት ነበር? በማን ነው የሚታዘዘው? የሚሉ ጥያቄዎችን ያነሱት አቶ ሌንጮ ለታ ሰራዊቱ አለ ከተባለም ትጥቅ አልፈታም ማለት አይችልም ሲሉ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
ኦነግ ትጥቅ አልፈታም የሚለው ማንን ለመውጋት ነው ሲሉ ይጠይቃሉ አቶ ሌንጮ ለታ።

በአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንማር ይፈቀድልን ያሉ የራያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቆሙ። በአድማው 23 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።


በአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንማር ይፈቀድልን ያሉ የራያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቆሙ። በአድማው 23 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።
 በዘንድሮ የ2011 ዓ.ም አዲሱ የትምህርት ዘመን ወደ ትምህርት ገበታቸው መግባት የነበረባቸው የራያ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋችን ካልሆነ አንማርም ማለታቸውን ተከትሎ ከ1ኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ያሉ ትምህት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ዝግ ሆነዋል። ሕዝቡ በህገመንግስቱ የተሰጠን መብት የትግራይ ክልል ሊከለክለን አይገባም ብለዋል። አላማጣ ከተማን ጨምሮ እስከ 23 የሚደርሱ ትምህርት ቤቶች በሕዝቡ አቋም እንዲዘጉ መደረጋቸውን የራያ ሕዝብ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሊቀመንበር አቶ አዘዘው ሕዳሩ ገልጸዋል።
በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ልጆቻችን በአፍ መፍቻ ባልሆነ ቋንቋ አንማርም ማለታቸው ያስቆጣቸው የትግራይ ክልል ባለስልጣናት ተማሪዎችን እና ወላጆችን የማባበል ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ይህ ያስቆጣቸው የዞን ባለስልጣናት የትምህርት ቤቶችን ርዕሰ መምህራንን እና ምክትል ርዕሰ መምህራንን በመጥራት እናንተ የማግባባት እና በማኅበረሰቡ ላይ ጫና መፍጠር ባለመቻላችሁ ምክንያት የተፈጠረ አድማ ነው በማለት ማስፈራሪያና ተግሳጽ ተሰጥቷቸዋል። የትምህርት ቤቶቹ አስተዳዳሪዎቹ በበኩላቸው ከአሁን በኋላ ሕዝቡን ማስገደድ እንደማይችሉ እና እራሳችሁ ከፈለጋችሁ ማስገደድ ትችላላችሁ ሲሉ ለዞኑ ባለስልጣናት ምላሽ ሰጥተዋል።
ሕዝቡ በአንድ ላይ በቋሙ ስለጸና ትምህርት ቤቶቹ አልተከፈቱም። ከዚህ በኋላም በማኅበረሰቡ አቋም ምክንያት አይከፈትም ሲሉ አቶ አዘዘው ሕዳሩ አክለው አስታውቀዋል። የራያ ህዝብ በትግራይ ክልል የሚደርስባቸውን የመብት ጥሰቶች መፍትሔ እንዲያገኙ የማንነት ኮሚቴ አዋቅረው ሕጋዊ ጥያቄያቸውን ቢያቀርቡም እስካሁን ድረስ እልባት ማግኘት አልቻሉም። ማኅበረሰቡ ከትግራይ ክልል ነጻ ለመውጣት የሚችልበትን
ፒቲሽን በመፈረም ሕጋዊ የፖለቲካ ጥያቄ በማቅረቡ በትግራይ ክልል ልዩ ኃይል እና ፖሊስ የሚደርስባቸው ተለያዩ የመብት ጥሰቶችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው። ሕዝቡን ከጅምላ እልቂት ለመታደግ እንዲቻል የማንነት አስመላሽ ኮሚቴው መከላከያ ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ በአካባቢው እንዲገቡ ለጠቅላይ ሚንስትር ቢሮ ጥያቄ ቢያቀርቡም እስካሁን ምላሽ ማግኘት አልቻሉም።

Lenco Latta concerned OLF remains armed as Dawud Ibsaa persists


Lenco Latta

A leading Oromo political figure said he was baffled by the position of the Oromo Liberation Front (OLF) to remain armed.
In an interview with a local radio station, Lenco Latta, who is the chairman of the Oromo Democratic Front (ODF) said the recent statement by Dawud Ibssa, Chair of the OLF, which showed refusal to disarm his soldiers was perplexing.
Mr. Ibssa has doubled down on the issue yesterday saying he has armed soldiers in the south and west of the Oromo region. In an interview with the VOA, Ibssa refused to put figures as to the size of the soldiers.
Mr. Ibssa reiterated his earlier position that in his deal with the government, before returning home from his base in Eritrea, it was his understanding that one party would not disarm the other. “There is no such thing as one party would disarm the other,” he told the VOA. He had also made similar statements in his earlier interview with a local media.
“If we wish to build a democratic system, then we only need the government’s army,” Mr. Lenco Latta meanwhile said.
“Where were the OLF soldiers when the Oromo youth was fighting government tanks with empty hands?” Lenco Latta asks and added “whom are they [OLF] going to fight?”
“If there are OLF soldiers still armed, then they should not refuse to disarm,” Lenco told Ahadu Radio.
Dawud Ibssa says the OLF is of the position that the current Ethiopian army is an army of the ruling EPRDF. He said there are what he called “criminals and operatives of the intelligence security of the ruling party” with in the Ethiopian army; a concern he said the OLF had communicated with the government. Ibssa said he expect the government to identify the “criminals and operatives of the ruling party” with in the army and take appropriate measures.
Ethiopian government spokesperson yesterday called on the Oromo Liberation Front (OLF) to immediately disarm its combatants that were still carrying weapons.
The statement by the the minister of government communication affairs, Kasahun Gofe, was made in response to the statement by the leader of OLF, Dawud Ibssa. But Ibssa said the statement by the government does not help bring peace to the country.
The OLF and a number of other armed opposition groups have returned to Ethiopia from their base in Eritrea after they had reached a peace deal with the government. The deal involves that the opposition lay down arms and their soldiers check into camps, according to the government.
Gofe said in his statement it would be tantamount to crossing the “red line” if any opposition group decides to keep arms.
The Prime Minister, Abiy Ahmed, also weighed in on the issue saying opposition groups “do not need to be armed with weapons but ideas.”

Wednesday, October 10, 2018

Ethiopian air Lines leaders are all from only one tribe Tigray

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚባለው ይሄ ነው ይህ ከአየር መንገዱ ሰራተኞች የወጣ ማስረጃ ነው:: የሚያሳዝነዉ ተወልደ የሚባል እንዲህ በጎጥ ሲያደራጅ በጣም ይገርማል፡፡
'Ethiopian' airline Leadership positions
1. Tewolede G/Mariam CEO (Tigrie)-THIS ONE DOESN't MATTER.
2. Miretab Tekilay Director digital---most traveling staff in the airlines (Tigire)
3. Zelalem Tesfaye Managing director MRO – (Tigire)
4. Essayas Wolde Mariam- Managing director international (Tigirie)
5. Bisirat Yared – Rome area manager (Tigire)
6. Micheal Yared VP customer service – (በቁጥር አምስት ላይ የተቀመጠዉ የBisirat Yared ወንድም) Tigrie
7. Tekle G/yohanis Managing director- ground service – (Tigire)
8. Fistum Abady-VP CGO- (Tigire)
9. Genete Zerihun-Director Add sales (Tigire)
10. Rahel zerihune managing director Cabin crew-(በቁጥር 9 የተጠቀሰችዉ የገነት ዘሪሁን እህት) (Tigire)
11. Zeresenay Belay-MGR premier (Tigire)
12. Daniel Ermias G/Mariam- Forman MRO (Tigire)
13. Ephrem Laik-MGR MRO (Tigire)
14. Gebireegizabiher Alemu-Mgr customer service (Tigire)
15. Bilen Arefiane Mgr HR- ready for foreign assignment (Tigire)
16. Solomon Abriha- Mgr Marketing- junior but ready for sweedne assignement (Tigire)
17. Embayanesh Areya Mgr recruitment –now on leave ordered by auditor…played a role to hire Tigrieans in bulk (Tigire)
18. Habtom Nazgi- Mgr catering (Tigire)
19. Akililu Habitu Director catering- (Tigire)
20. Haile Gebirel Kidane-TL MRO (Tigire)
21. Haile Tesfaye-Director MRO (Tigire)
22. Gebiremarim Haile-Mgr system security (Tigire)
23. Gebireyohanis woldegiorgies-Mgr Ricrutmenet-replaced Embayenesh Areya..this position is only for Tegaru (Tigire)
24. Elzabethe Hailu-MGR Ticket offices (Tigire)
25. Enderita Mesifine- MGR HR and fiannce (Tigrie)
26. Kfilie Merisa-director CGO (Tigire)
27. Alem Desita-Attoreny (Tigire)
28. Brenesh Kbreab -attorney (Tigire)
29. Hailu Asibiha-Mgr (Tigire)
30. Anely eshetu Mgr PR-her husband is a well known EPRDF (Tigire)
31. Mesifine Ashebir-Mgr loyality (Tigire)
32. Fissiha Kidane-Mgr HR and finance at the catering (Tigrie)
33. Rahel Mesifine-VP (Tigire)
34. Mesay Shiferaw-A/VP corporate HR(Tigire)
35. Solomon Debebe-MDR aviation (Tigire)
36. Haile Melekot Mamo- in Malawi Head (Tigire)
37. Teshome Gebiresilassei-Abidjan station manager- (Tigire)
38. Redi Yusuf -managing director international service (Tigire)
39. Khartum head (Tigire)
40. Chicago (Tigirie)
41. Bahrian (Tigire)
42. Beyrut (Tigire)
43. Bamako (Tigirie)
44. Dareselam
45. Djibuti
46. Kanoo
47. Stockholm
48. Oslo
49. Los angeles- Sasahulish Laeke, Traffic and Sales Manager who is also የተወልደ ገ/ማሪያም ዉሽማ፡፡ ሎስ አንጀለስ ጣቢያ 16 ሰራተኞች ሲኖሩት 15ቱ ትግሬወች ናቸዉ፡፡
50. Cabine crew recruitment number 191-215 (all tigreans)-እያንዳንዱ ተቀጣሪ ባች የአዲግራት ባች፤ የአክሱም ባች፤ የመቀሌ ባች፤ በመባል ይታወቃል (68 % employees)
Non-Tigrinas
1. Busra Awol CCO- (Silitie)
2. Mesifine Tasew COO (Amahara)
3. Meseret Bitew VP (Oromo/Amhara)
4. Yinessu x/vp now in Luwanda -demoted after used (Amahara)
5. Aziza Mohamed x/vp now Director…demoted after used (Addis Abeba and mix)

በሳኡዲ ቆንስላ ገብቶ በዚያው የቀረው ጋዜጠኛ ጀማል ጉዳይ ዐለምን እያነጋገረ ነው።

የቱርክ ሚዲያዎች ጋዜጠኛው ከሪያድ በመጡ ደህንነቶች መጠለፉን የሚጠቁም ቪዲዮ ይፋ አድርገዋል።

በሳኡዲ ቆንስላ ገብቶ በዚያው የቀረው ጋዜጠኛ ጀማል ጉዳይ ዐለምን እያነጋገረ ነው። የቱርክ ሚዲያዎች ጋዜጠኛው ከሪያድ በመጡ ደህንነቶች መጠለፉን የሚጠቁም ቪዲዮ ይፋ አድርገዋል።
የዛሬ አስር ቀን አካባቢ ነበር የሳኡዲ ዜግነት ያለው አንጋፋው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ በቱርክ ኢስታምቡል በሚገኘው የሳኡዲ ቖንጽላ ጽህፈት ቤት እንደገባ በዚያው የቀረው።
ከጋብቻ ጋር በተያያዘ ጉዳይ ለማስፈጸም እጮኛውን ከውጭ አቁሞ ወደ ቆንጽላ ጽህፈት ቤቱ ቅጥር ግቢ የዘለቀው ጋዜጠኛ ጀማል ፣የሳኡዲ ንጉሳውያን ቤተሰቦችን አሰራር የሚተች ጽሁፍ በተደጋጋሚ በዋሽንግተን ፖስትና በሌሎች ታላላቅ ጋዜጦች ላይ ይጽፍ ነበር።
እነሆ የሳኡዲ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ጀማልን ከዋጠው አስረኛ ቀን በተቆጠረበት በዛሬው ዕለት የቱርክ ሚዲያዎች ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ በሳኡዲ ደህንነቶች መጠለፉን የሚጠቁም ቪዲዮ ይፋ አድርገዋል።
መገናኛ ብዙሀኑ ይፋ ያደረጉት ቪዲዮ ጀማል ቆንጽላ ጽህፈት ቤቱ የገባ ዕለት የሳኡዲ ደህንነቶች ኢስታምቡል አውሮፕላን ማረፊያ ሲገቡ እና የዚያኑ ዕለት ወደ ሪያድ ሲመለሱ የሚያሳይ ነው።
በቆንጽላው ዙሪያ የተገጠመው የደህንነት ካሜራም በዕለቱ ከግቢው ውስጥ መስተዋቱ ዙሪያውን የማያሳይ ጥቁር መኪና ሲወጣ ያመለከተ ሲሆን፣ ጋዜጠኛው ታፍኖ የወጣው በዚሁ መኪና ሳይሆን እንዳልቀረ ተገልጿል።
ጀማል ከተሰወረበት ዕለት አንስቶ እስካሁን ድረስ የቱርክ ባለሥልጣናት ጋዜጠኛው በሳኡዲ መንግስት እንደተገደለ እየገለጹ ነው። ሪያድ በበኩሏ ክሱን ማስተባበሏን ቀጥላለች።
“ሳባህ” የተባለው የቱርክ ታዋቂ ጋዜጣ ጋዜጠኛ ጀማልን አፍኖ በመውሰዱ ሴራ አስራ አምስት ያህል የሳኡዲ ደህንነቶች መሳተፋቸውን አስነብቧል።
ዓለማቀፍ ህግን በተጻረረ መልኩ የጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ከቆንጽላ ጽህፈት ቤት የመታፈኑና የመሰወሩ ዜና ፤ ዓለማቀፉን ማህበረሰብ እያነጋገረ ነው።
የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ሴክሬታሪ ዛሬ ለሳኡዲ አረቢያ ባስተላለፉት መልዕክት ሀገራቸው ብሪታኒያ የጀማል ካሾጊን ጉዳይ አስመልክቶ ከሳኡዲ ፈጣን ምላሽ እንደምትጠብቅ አሣስበዋል።
የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጀርሚ ኸንት -ለሳኡዲው አቻቸው ለአደል አል ጁቢየር ባስተላለፉት በዚሁ የስልክ መልዕክት ሀገራቸው ከሳኡኢ ጋር ያላት ግንኙነት የሚቀጥለው በጋራ ሰብዓዊ እሴቶች ላይ ሲመረኮዝ እንደሆነ አስጠንቅቀዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁን ከሳኡዲ ባለሥልጣናት ጋር እንዳልተነጋገሩ በመጠቀስ፣ ሆኖም በነገሩ ላይ ዝም እንደማይሉ ለሪፖርተሮች ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፖ ፣በጋዜጠኛ ጀማል ጉዳይ የሚደረገውን ምርመራ ለመደገፍ አሜሪካ ዝግጁ መሆኗን ለሳኡዲ አስታውቀዋል።.
የመንግስታቱ ድርጅት ኤክስፐርቶች በበኩላቸው በጀማል መሰወር ዙሪያ ዓለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ፈጣን እና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
የሳኡዲው መሪ ልኡል መሀመድ ቢን ሰልማን ባለፈው ሳምንት በጋዜጠኛ ጀማል ላይ በሆነው ነገር እንዳዘኑና ሀገራቸው በፍለጋው ለመተባበር ዝግጁ እንደሆነች ለብሉምበርግ መናገራቸው ይታወሳል።
በሳኡዲ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ገብቶ በዚያው ከቀረ አስረኛ ቀኑ የተቆጠረው የአንጋፋው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ታሪክ መጨረሻ ምን ይሆን? የሚለው የብዙዎችን ትኩረት ሰቅዞ እንደያዘ ነው።

Ethiopia: Soldiers show up unannounced at National Palace, PM orders pushups


by Engidu Woldie
ESAT News (October 10, 2018)
A group of soldiers showed up unannounced at the National Palace and demand to speak with the Prime Minister, who punished them with some pushups. The soldiers reportedly wanted the PM to address salary and benefit issues.
Wild speculations filled the Ethiopian social media today as a group of about 240 members of the defense force suddenly came to the National Palace and demand to speak with the Prime Minister, who ordered them to do some pushups, apparently for showing up at his office without notice.
The commotion at the National Palace has led many to speculate that some form of mutiny or coup was in the making. The Federal Police Commissioner, Zeinu Jamal, told the VOA that the soldiers first demanded that they enter the premises of the Palace armed with their weapons. There was boost up of security at and near the Palace out of an abundance of caution, according to the Commissioner, who said the soldiers were let in after they had been disarmed.
The soldiers have reportedly discussed salary and benefits issues with the Prime Minister, Abiy Ahmed and the Deputy Prime Minister, Demeke Mekonnen, according to the Federal Police Commissioner, Zeinu Jemal, who spoke to the VOA.
According to a post on the Facebook page of the Deputy Prime Minister, the soldiers have discussed on wide range of issues with Mekonnen, who promised that the nationwide reforms would also be implemented within the national defense force.
Later, the soldiers also met and discussed with the Prime Minister. But Abiy Ahmed has something in store for them. He ordered the soldiers to do some pushups as a form of punishment for showing up at his office without prior appointment.
But he also got down to the ground and did the pushups with the soldiers.

Tuesday, October 9, 2018

በማንነቴ በደረሰብኝ ጥቃት አየር መንገዱን ለቅቄ ወደ ግብርና ገብቼአለሁ በሚል በአማራ ቴሌቪዥን ለተናገሩት ግለሰብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምላሽ ሰጠ።


በዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ተወለደ ገብረማርያም ፊርማ በተሰጠ ምላሽ የአማራ ቴሌቪዥን አየር መንገዱን ይቅርታ እንዲጠይቅም ያሳስባል።
ከባርነት ነጻነት ሞትን እመርጣለሁ በሚል ርዕስ በአማራ ቴሌቪዥን በቀረበው ዘገባ ካፒቴን ዮሀንስ ተስፋዬ በማንነቱ የሚደርስበት በደልና ስቃይ ከፍተኛ በመሆኑ መቀጠል ባለመቻል ስራውን መልቀቁን ይገልጻል።
አየር መንገዱ በጻፈው ደብዳቤ የአማራ ቴሌቪዥን ያቀረበው ዘገባ ሚዛናዊ ያልሆነና የሀሰት መረጃ የቀረበበት ነው ሲል ይከሳል።
ባለፈው ማክሰኞ ምሽት ፕሮግራሙ የአማራ ክልል ቴሌቪዥን ስለአንድ የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባልድረባ ዘገባ ያቀርባል።
ዘገባው ካፒቴን ዮሀንስ ተስፋዬ የተባሉ የመስሪያ ቤቱ ባልደረባ በማንነቴ በሚደርስብኝ በደልና ጭቆና ስራዬን በገዛ ፍቃዴ ለቅቄ ወደ ግብርና ስራ ገባሁ የሚል ነበር።
ለ1200 ሰዓታት እንደበረሩ የሚገልጹት ካፒቴን ዮሀንስ የሀገር ውስጥን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ በተለያዩ ሀገራት እንደበረሩ የሚገልጹት ካፒቴን ዮሀንስ በአየር መንገዱ ውስጥ የሚፈጸመውን ማንነት ላይ ያተኮረ በደል በዝርዝር ያስረዳሉ።
ካፒቴን ዮሀንስ እንደሚሉት በአየር መንገድ ውስጥ በነበራቸው ቆይታ በአማራ ማንነታቸው ከፍተኛ በደል ተፈጽሞባቸዋል።
በማንነት ላይ የሚደርሰው አሸማቃቂ የሆኑ ነገሮችን ለመሸሽ በሚል ስራውን ትተው ወደ ትውልድ ቦታቸው ጎጃም መሄዳቸውንና በግብርና ስራ መሰማራታቸውን ነው ለአማራ ክልል ቴሌቪዥን የገለጹት።
ከአየር መንገዱ ይልቅ በግብርናው ላይ ነጻነት ይሰማኛል ያሉት ካፒቴን ዮሀንስ ከባርነት ሞትን እመርጣለሁ ሲሉ በአየር መንገዱ የደረሰባቸውን በደል በምሬት ይናገራሉ።
በአሁኑ ጊዜም በጎጃም ደጀን በግብርና ሙያ ተሰማርተው እየሰሩ እንደሚገኙ በዘገባው ተገልጿል።
የካፒቴን ዮሀንስ ታሪክ በአማራ ቴሌቪዥን ከቀረበ በኋላ ከፍተኛ መነጋጋሪያ ሆኖ ነው ያለፉትን ሁለት ቀናት የቆየው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቲውተር ገጹ ጉዳዩን ያስተባበለ ሲሆን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚም ለአማራ ቴሌቪዥን የተቃውሞ ደብዳቤ ልኳል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም በጻፉት ደብዳቤ የአማራ ቴሌቪዥን ላቀረበው ሚዛናዊ ያልሆነ ዘገባ ይቅርታ እንዲጠይቅ አሳስበዋል።
አቶ ተወልደ በደብዳቤአቸው ካፒቴን ተሾመ ረዳት አብራሪ እንጂ ዋና አብራሪ ባለመሆኑ ካፒቴን ተብሎ የተገለጸው ሀሰት ነው ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ረዳት አብራሪ በሚል የገለጿቸውን የድርጅታቸውን የቀድሞ ሰራተኛ በአቅም ማነስና ስልጠና ላይ ድክመት በማሳየት ተደጋጋሚ ችግር የተከሰተባቸው መሆኑን አቶ ተወልደ በደብዳቤአቸው ይገልጻሉ።
በማንነቴ በደረሰብኝ የሚለው ክስ ተገቢ አይደለም ያሉት አቶ ተወልደ የአማራ ቴሌቪዥን የአየር መንገዱ ስምና ዝና በሚያጎድፍ ዘገባ ላይ በመሰማራቱ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል ብለዋል።
አየር መንገዱ የካፒቴን ዮሀንስን የስልጠና ውጤት የተመለከቱ የግል ማስረጃዎችን በፌስ ቡክ ገጹ ላይ የለጠፈ ሲሆን ይህ የግልሰብ ማስረጃን በአደባባይ ማውጣት ተገቢ አይደለም የሚል ተቃውሞ እየተሰማ ነው።
ኢሳት በየጊዜው ከአየር መንገዱ የሚለቁ ሰራተኞችን በተመለከተ በርካታ ባለሙያዎችን ያነጋገረ ሲሆን አብዛኞቹ ድርጅቱን የሚለቁት በአየር መንገዱ ባለው ስር የሰደደ ማንነት ላይ ያተኮረ ጥቃት የሚፈጸም በመሆኑ ነው።
ከዚህ ቀደም በድርጅቱ በሚፈጸም ማንነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ምክንያት የሚያበረውን አውሮፕላን አቅጣጫ በማስቀየር ጄኔቫ ያሳረፈው ካፒቴን ሃይለምድህን አበራን በተመለከተ በወቅቱ አየር መንገዱ የሰጠው ምክንያት የአእምሮ ችግር ያለበት ነው ማለቱ የሚታወስ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአንድ ወገን መለያ ሆኖ ከ20 ዓመታት በላይ መቆየቱን የሚገልጹት ሰራተኞች በተርሚናል ውስጥ የሚገኙት መደብሮች በአንድ አከባቢ ተወላጆች ቁጥጥር ስር መሆናቸውንም ለኢሳት ከውስጥ የደረሰው መረጃ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ላቀረቡት ክስ የአማራ ቴሌቪዥን እስከአሁን የሰጠው ምላሽ የለም።
በዚህ ጉዳይ ካፒቴን ዮሀንስ ተስፋዬን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረትም አልተሳካም።

ኦነግ በምዕራብ ወለጋ የመንግስት ታጣቂዎችን ትጥቅ እያስፈታ ከመሆኑም በላይ ያገታቸው ነጋዴዎች መኖራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።

 ማንነታቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት “በኡላ ኖሌ” ወረዳ የኦነግ ታጣቂዎች መንግስት ያስታጠቃቸውን የአካባቢ ሚሊሺያዎችን ትጥቅ በማስፈታት የጦር መሳሪያዎችን ወስደዋል። የኦነግ ታጣቂዎች በዚሁ ወረዳ ጌጡ ገበየሁ የሚባል ታዋቂ ነጋዴን አፍነው የወሰዱ ሲሆን፤ ነጋዴው እስካሁን የደረሰበት አልታወቀም።

ከኖሌ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጉይ ከተማ ደግሞ የፖሊስ ጽ/ቤትን በመስበር የጦር መሳሪያ መውሰዳቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። በዚሁ አካባቢ ወጣቶችን እየመለመሉ ወታደራዊ ትምህርት በመስጠት እና በማስታጠቅ ላይ መሆናቸውን እንዲሁም አካባቢው ከጋምቤላና ከኢሊባቡር ጋር የሚዋሰን በመሆኑ በዚሁ አካባቢ የጦር መሳሪያ እያስገቡ መሆኑንም ንዋሪዎቹ ጨምረው ገልጸዋል።
በዚሁ አካባቢ ከ2 ሳምንት አፊት ተብሎ በሚጠራ አካባቢ አንዲት ፖሊስ ተገድላ እንደነበርም የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
በቡሌ ሆራ ወረዳ ደግሞ የኦነግ ታጣቂዎች በርጅ ማህበረሰብ አባላት ላይ የሚፈጽሙትን ጥቃት አጠናክረው መቀጠላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚሁ ከተማ ከሳምንት በፊት አንድ የፖሊስ ባልደረባ የነበረች ሴት በእነዚህ ታጣቂዎች መገደሏንም የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል።
መንግስት የኦነግ ታጣቂዎች ትጥቅ እንዲፈቱ ያቀረበው ጥሪ እስካሁን ተግባራዊ እንዳልሆነ የሚደርሱን ሪፖርቶች ያሳያሉ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ኦነግ ትጥቁን የማይፈታ ከሆነ መንግስት ትጥቅ የማስፈታቱን ስራ እንደሚሰራ በትናንትናው ዕለት ማስጠንቀቅቃቸው ይታወቃል።። ጠ/ሚ አብይ አህመድ በበኩላቸው ኦነግ ትጥቅ አልፈታም አለ የሚባለው የአፍ ወለምታ ይሆናል የሚል ግምት እንዳላቸው በመግለጽ፣ ከድርጅቱ መሪዎች ጋር ሰሞኑን ሲገናኙ በጉዳዩ ዙሪያ እንደሚነጋገሩ ተናግረዋል።
የቀድሞው የኦነግ አመራር የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ ደግሞ ” ኦነግ ትጥቅ አልፈታም ማለቱ እንዳስገረማቸው ለአሃዱ ሬዲዮ ተናግረዋል። አቶ ሌንጮ በሬዲዮው በነበራቸው ቆይታ ፦ “የኦነግ ታጣቂዎች ወጣቱ ከታንክ ጋር ሲጋፈጥ የት ነበሩ? አሁንስ ማንን ሊወጉ ነው ትጥቅ አንፈታም የሚሉት?” በማለት ጠይቀዋል።
አቶ ዳውድ ኢብሳ ትናንት ምሽት ለአሜሪካ ድምጽ ሲናገሩ የኦነግ ታጣቂዎች በመከላከያ ስር ታቅፈው እንዲቀጥሉ ከመንግስት ጋር ስምምነት የነበረ መሆኑን ጠቅሰው፣ መንግስት ቃሉን አፍርሶ ማስፈራሪያ መስጠቱን ተቃውሞዋል። ኦቦ ዳውድ አክለውም በስምምነታቸው መሰረት አንዱ ሌላውን ትጥቅ የሚያስፈታበት ሁኔታ እንደሌለ በመግለጽ፤ቀደም ብለው ለዋልታ ቴሌቪዥን የሰጡትን ቃል አጠናክረዋል።

wanted officials