Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, September 23, 2019

ውሃ ውስጥ ለፍቅረኛው የአግቢኝ ጥያቄ ያቀረበው ግለሰብ ሰጥሞ ሞተ



ስቲቨን ዌበርImage copyrightKENESHA ANTOINE
አንድ አሜሪካዊ ጎብኚ ታንዛኒያ ውስጥ ለፍቅር ጓደኛው የጋብቻ ጥያቄ ለማቅረብ ወደ ውሃ ውስጥ ገብቶ ሳይመለስ መቅረቱ ተሰምቷል።
ስቲቨን ዌበር የተባለው ግለሰብ እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በታንዛኒያ ፔምባ ደሴት ላይ በሚገኝ ማንታ በተባለ ሪዞርት ነበር ያረፉት። ስቲቨን ለፍቀረኛው ታገቢኛለሽ ወይ የሚለውን መልዕክቱን በወረቀት ላይ ጽፎ ነበር ወደ ውሃ ውስጥ የገባው።
ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በፌስቡክ ገጿ ላይ ባስተላለፈችው ምልዕክት ጥልቅ ወደሆነው ባህር አካባቢ የሄደው ስቲቨን መመለስ ሳይችል መቅረቱን አረጋግጣለች።
የማንታ ሪዞርት አስተዳደር ለቢቢሲ እንደገለጸው ስቲቨን ዌበር ውሃ ጠለቃ በሚደረግበት አካባቢ ገብቶ ህይወቱ ያለፈችው ባሳለፍነው ሐሙስ ከሰዓት ላይ ነበር።
''ባሳለፍነው ሐሙስ በሪዞርታችን በተፈጠረው ክስተት እጅግ ማዘናችንን መግለጽ እንፈልጋለን'' ብሏል ድርጅቱ በመግለጫ።
የሪዞርቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ማቲው ሳውስ እንዳሉት መላው የማንታ ሪዞርት ሰራተኛ በተፈጠረው አደጋ ተደናግጠዋል።
አጭር የምስል መግለጫስቲቨን ዌበር እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን
ስቲቨን ዌበር እና ፍቅረኛው ኬኔሻ አንቱዋን በሪዞርቱ የውሃ ጠለቃ በሚደረግበት የባህሩ ክፍል ለአራት ቀናት ለመቆየት ቀድመው ቦታ አስይዘው የነበረ ሲሆን ቦታው ከባህር ዳርቻ በግምት በ250 ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።

ለቀናት በአካባቢው ሲዝናኑ የቆዩት ጥንዶች በሶስተኛው ቀን ተያይዘው ጥልቀት ወዳለው የባህሩ ክፍል ያመራሉ። ስቲቨን ፍቅረኛው ሳታየው የታገቢኛለሽ ጥያቄውን ለማቅረብ ተዘጋጅቶ ነበር።
የውሃ ውስጥ መነጽሩን እንዳደረገም ስቲቨን ለፍቅረኛ የጋብቻ ጥያቄውን ማቅረብ ጀመረ።
በላስቲክ በተሸፈነ ወረቀትም እንዲህ ሲል ጽፎ ነበር፤ ''የምወድልሽን ነገሮች ሁሉ እንዳልነግርሽ ለረጅም ጊዜ ትንፋሼን መያዝ አልችልም፤ ነገር ግን ስላቺ የምወዳቸውን ነገሮች በሙሉ በእያንዳንዱ ቀን ይበልጥ እወድልሻለው።''
ቀጥሎም የጋብቻ ቀለበቱን ለፍቅረኛው አቅርቦ ነበር።
ስለ አሟሟቱ ዝርዝር መረጃ ባይሰጥም፤ ኬኔሻ አንቱዋን እንደገለጸችው ''ለጥያቄው ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ህይወቱ በማለፉ በጣሙን አዝኛለሁ'' ብላለች።

Sunday, September 22, 2019

ከ34 ዓመት በፊት በአውሮፕላን ጠለፋ የተጠረጠረው በቁጥጥር ስር ዋለ

https://zethiopians.blogspot.com/2019/09/blog-post_68.htm

የተጠለፈው አውሮፕላን

Image copyrightALAIN NOGUES/GETTY
እ.አ.አ. 1985 በአሜሪካ አየር መንገድ ንብረት በሆነ አውሮፕላን ላይ በተፈጸመው ጠለፋ እጁ አለበት የተባለው የ65 ዓመት ሊባኖሳዊ ግሪክ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።
ስሙ ያልተጠቀሰው ተጠርጣሪ ባሳለፍነው ሐሙስ ነበር ሚይኮኖስ በተባለ ደሴት በቁጥጥር ሥር የዋለው። ተጠርጣሪው በጉዞ ላይ በነበረበት ወቅት ፓስፖርቱ ሲታይ ጀርመን ውስጥ ተፈላጊ እንደሆነ ተደርሶበታል።

'ቲደብልዩኤ' የበረራ ቁጥር 487 የነበረው አውሮፕላን መሳሪያ ታጥቀው በነበሩ ሂዝቦላህ የተባለው ኢስላማዊ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ሆኖ ነበር። ምንም እንኳን ሂዝቦላህ ድርጊቱን አለመፈጸሙን ቢክድም።
ተጠርጣሪው እ.አ.አ. በ1987 ፈጽሞታል በተባለው የጠለፋና ሰዎችን በማገት ወንጀል ነበር በጀርመን ባለስልጣናት ይፈለግ የነበረው። በአሁኑ ሰዓት ተጠርጣሪው ከፍተኛ ጥበቃ በሚደረግለት የግሪክ ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛል።
ወንጀሉን ፈጽሟል ከተባለ ከሁለት ዓመታት በኋላ ጀርምን ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ የነበረ ሲሆን ቤሩት ውስጥ ታግተው የነበሩ ሁለት ጀርመናውያንን ለማስቀቅ ወደ ሊባኖስ በነጻ ተለቆ ነበር።
እ.አ.አ. በ1985 የትራንስ ወርልድ አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን ከካይሮ ተነስቶ በአቴንስ፣ ሮም፣ ቦስተን እና ሎስ አንጀለስ አድርጎ ወደ ሳንዲዬጎ በመብረር ላይ ሳለ ነበር ከአቴንስ ሲነሳ ጠላፊዎቹ አስገድደው ቤሩት እንዲያርፍ ያደረጉት።
153 የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎችና ሰራተኞች ለ17 ቀናት በቆየው አጋች ታጋች ድራማ በአውሮፕላኑ ውስጥ ቆይተዋል። ጠላፊዎቹም በእስራኤል ተይዘው የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሊባኖች ዜጎች ይፈቱልን በማለት ታጋቾቹን በማሰርና በመደብደብ በኋላ እንደሚገድሏቸው ሲያስፈራሩ ነበር።
በእስራኤል የሚገኙት ታሳሪዎች ሳይለቀቁ ሲቀር በአውሮፕላኑ ውስጥ ተሳፋሪ የነበረ አንድ የ23 ዓመት አሜሪካዊ የውሃ ጠላቂ ወታደር ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ሬሳውም ወደ ውጪ ተወርውሮ ነበር።
በመጨረሻ ግን ጠላፊዎቹ ታጋቾቹን ለቀዋል።
እንደ ኤፍቢአይ ከሆነ አውሮፕላኑን በመጥለፍ ወንጀል ውስጥ ቢያንስ አራት ሰዎች ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበራቸው።
እአአ 1986 ላይ የተለቀቀው እና 'ዘ ዴልታ ፎርስ' (The Delta Force) የሚል ስያሜ የተሰጠው ፊልም ይህን የአውሮፕላን ጠለፋ ላይ መሰረት ተድርጎ የተሰራ ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለያዩ ከተሞች ሰልፍ እያካሄዱ ነው



በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍImage copyrightAMMA
አጭር የምስል መግለጫበደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍ
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ሰልፍ እያካሄዱ ነው።
የተቃውሞ ሰልፍ እየተካሄደ ከሚገኝባቸው ስፍራዎች መካከል፤ የአማራ ክልል መዲና በሆነችው ባህርዳር፣ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ወልዲያ እና ምሥራቅ ጎጃም ደብረ ማርቆስ ይጠቀሳሉ።

የሰልፉ ተሳታፊዎች በቤተክርስቲያኗ፣ በኃይማኖት አባቶች እና በምዕመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ይቁም የሚል መልዕክት ይዘው ወጥተዋል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ እየተሰሙ ካሉ ድምጾች መካከል፤ ''በቤተ-ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸሙት ጥቃቶች ይቁሙ፣ ጥፋተኞች ለሕግ ይቅረቡ'' የሚሉ ይገኙበታል።
በወልዲያ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍImage copyrightAMMA
አጭር የምስል መግለጫበወልዲያ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የተቃውሞ ሰልፍ
በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ ያለውን ሰልፍ ከሚያስተባበሩት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ በሪሁ ተስፋዬ "እጅግ በርካታ ሰዎች እየተሳተፉ የሚገኙበት ሰልፍ ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው" ብለዋል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ እየተሰሙ ካሉ መፈክሮች መካከል ''የቅዱስ ሲኖዶስ ድምጽ ይሰማ'' እና ''የቤተክርሰቲያን እና የኦሮቶዶክሶዊያን መገደል ይቁም'' የሚሉት ጎልተው እንደሚሰሙ አቶ በሪሁ ተናግረዋል።

የዛሬ ሳምንት ዕሁድ በተመሳሳይ መልኩ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደው ነበር።
በደሴ፣ ደብረ ታቦር እና ጎንደር ከተማ በተካሄዱት እና በሰላም በተጠናቀቁት ሰላማዊ ሰልፎችም ''በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቤተ-ክርስቲያን ያቀጠሉ እና ምዕመናንን የገደሉ ለፍርድ ይቅረቡ፣ መንግሥት ቤተ-ክርስቲያንን ሊያከብር ይገባል'' የሚሉ ተመሳሳይ የተቃውሞ ድምጾች ነበር የተሰሙት።

ኢትዮጵያ ውስጥ የተያዙት የአል ሸባብና የአይ ኤስ አባላት ማንነት ይፋ ሆነ



ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ማንነት እና ስለተያዙበት ሁኔታ በዝርዝር ገልጿል።Image copyrightFANA
አጭር የምስል መግለጫብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ማንነት እና ስለተያዙበት ሁኔታ በዝርዝር ገልጿል።
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ሥፍራዎች የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ዝግጅት ላይ የነበሩ የተባሉ የአል-ሸባብና የአይ ኤስ ቡድን አባላት መያዛቸው ተገለጸ።
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ቅዳሜ ምሽት ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው አልሸባብ እና አይ ኤስ ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃት በመፈፀም በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ በዝግጅት ላይ እንዳሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል።

የአገር መከላከያ ሠራዊት፤ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ የጽንፈኛው እስላማዊ ቡድን-አይኤስ አባላትን በቁጥጥር ሥር አዋልኩ ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል።
የኢታማዦር ሹሙ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ኮለኔል ተስፋዬ አያሌው ከአንድ ሳምንት በፊት የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ናቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎች ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ ሞያሌ እና ዶሎ ከተማዎችን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ውስጥ መያዛቸውን ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።
በቁጥጥር ሥር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሶማሊያ፣ የሶሪያ እና የየመን ዜጎች እንደሚገኙበት ኮለኔል ተስፋዬ ተናግረዋል። "አብዛኞቹ ተጠርጣሪዎች አማርኛ ቋንቋ ተምረው የተላኩ ናቸው" ሲሉም አክለው ነበር።
ህዝብ የሚበዛባቸውን ቦታዎች እንዲሁም የሀይማኖት ክብረ በዓል የሚካሄድባቸውንና የተለያዩ ሆቴሎችን የመለየትና የፎቶግራፍ መረጃዎችን የመሰብሰብ ጥናት ካደረገ በኋላ ጥቃት ለመፈጸም በጅቡቲ በኩል ወደ አዲስ አበባ የገባው አንደኛው የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባል ሙሐመድ አብዱላሂ ዱለት፤ ክትትል ሲደረግበት ቆይቶ በአዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ መያዙን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ገልጿል።
ከግለሰቡ በተጨማሪ ሌሎች ተባባሪዎች ለተለያዩ የጥቃት ተልዕኮዎች ከጅቡቲና ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውንና ከሃገራቱ የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በቁጥጥር ስር እንደዋሉም ተነግሯል።
ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ማንነት እና ስለተያዙበት ሁኔታ በዝርዝር ገልጿል።Image copyrightFANA
አጭር የምስል መግለጫብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ማንነት እና ስለተያዙበት ሁኔታ በዝርዝር ገልጿል።
ከአል-ሸባብ በተጨማሪ የአይ ኤስ የሽብር ቡድን አባላት ከቦሳሶ በሶማሌላንድ ሃርጌሳ በኩል ወደ አዲስ አበባ በመግባት የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ በብሔሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በአዲስ አበባና በአዋሽ አካባቢ መያዛቸው ተገልጿል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የቡድኖቹ አባላት በተጨማሪ የሚጠቀሙባቸው የግንኙነት መሳሪያዎችና ሌሎች ቁሳቁሶች መያዙም ተጠቅሷል።

ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በቁጥጥር ስር የዋሉትን ግለሰቦች ማንነት እና የት በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት፤
የአል-ሸባብ የሽብር ቡድንን የሚመራው ሙሐመድ አብዱላሂ ዱለት በሀሰተኛ ስሙ ያህያ አሊ ሃሰን በጅቡቲ በኩል ወደ አዲስ አበባ ከገባ በኋላ ቦሌ አካባቢ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የሙሐመድ አብዱላሂ ዱለት ግብረ አበሮች የሆኑት አብደክ መሃመድ ሁሴን፣ ሬድዋን መሃመድ ሁሴን እና በቅፅል ስሙ ስመተር መሀመድ ኢማን ዩሱፍ በመባል የሚታወቀው ጅቡቲ ውስጥ በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
ከደቡባዊ ሶማሊያ በመነሳት ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ዝግጅት ሲያደርጉ የነበሩት ይሳቅ አሊ አደን እና አደን ሙሃሙድ መሃመድ በቅፅል ስሙ አደን ቦራይ ሱማሊላንድ ውስጥ ተይዘዋል። ይሳቅ አሊ አደን ከሶማሌ ክልል ቦህ ወረዳ ጨርቃን ቀበሌ የተሰጠ የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ የተገኘ ሲሆን፤ አደን ሙሃሙድ መሃመድ የሚባለው ተጠርጣሪ ደግሞ በስሙ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 2.5 ሚሊዮን ተቀማጭ ብር ተገኝቷል።
መካከል ዒድ መሃመድ ዓሊ የተባለ ተጠርጣሪ በሶማሌ ክልል ጨርጨር ዞን አራርሶ ወረዳ፣ በሽር ዑስማን አብዲ በሶማሌ ክልል ፊቅ አከባቢ እንዲሁም ዑስማን አሊ ሁሴን በኦሮሚያ ክልል በሞያሌ ከተማ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የአይ ኤስ አባል የሆነው ፋዕድ አብሽር የሱፍ ከቦሳሶ ሶማሊያ በሃርጌሳ ፑንትላንድ በኩል አድርጎ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ አዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሙህመድ ጉሀድ ቡዲል የተባለው ተጠርጣሪ ደግሞ ሶማሌ ክልል በአፍዴር ዞን ምዕራብ ኢሚ ወረዳ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
ሌላ የአይ ኤስ የሽብር ቡድን አባል የሆነ ሰይድ ዑመር ሸበሺ የተባለው ተጠርጣሪ በፀጥታ አካላት በአዋሽ አካባቢ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል።
የሸብር ቡድኖችን በመከታተል በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ለማድረግ በተካሄደው የኦፕሬሽን የጁቡቲ፣ የሶማሊላንድ፣ የፑንትላንድ፣ የአሜሪካ፤ የጣሊያን፣ የፈረንሳይና የስፔን የመረጃ ተቋማት እገዛ ማድረጋቸውን ብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት በመግለጫው አሳውቋል።
ከዚህ ቀደም አይኤስ በአማርኛ ቋንቋ የጽሑፍ መልዕክቶችን በቴሌግራም አማካኝነት ማስተላለፍ እንደሚጀምር ማስታወቂያ አሰራጭቶ እንደነበረ ይታወሳል።
የኢታማዦር ሹሙ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮለኔል ተስፋዬ "የአገራችን የደህንነት ጥበቃ ጠንካራ ስለሆነ ወደ ኢትዮጵያ ዘልቀው መግባት ባለመቻላቸው፤ ፕሮፖጋንዳ ብቻ ነው የሚነዙት። ድንበር አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ጥበቃ እያደረግን ነው" ብለው ነበር።

ላሊበላ፡ የመፍትሔ ያለህ የሚለው ብሔራዊ ቅርስ


ላሊበላ፡ የመፍትሔ ያለህ የሚለው ብሔራዊ ቅርስ
Image copyrightBILDAGENTUR-ONLINE

ይህ ግን ለሃይማኖታዊ አገልግሎት ብቻ አይደለም። ከአገልግሎቱ ጎን ለጎን ቅርሱን እያስጎበኙ ኑሯቸውን ስለሚመሩ ጭምርም ነው።
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት በ12ኛው ክፍለ ዘመን ከአንድ አለት ተፈልፍለው የተሠሩ ናቸው።
በቁጥር 11 የሆኑት አብያተ ክርስቲያናት፤ በ1970 ዓ. ም. በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የዓለም ቅርስ ተብለው ተመዝግበዋል።
ዲያቆን ፈንታ እነዚህን ድንቅ ቅርሶች ሲያስጎበኙ ከጊዜ ወደ ጊዜ አደጋ ላይ እየወደቁ መሆኑን መገንዘብ ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል።
"ዕድሜ ተጨምሮበት፣ በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያትም እየተጎዱ ነው" ይላሉ።

በዚህ ሀሳብ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ጽጌሥላሴ መዝገቡም ይስማማሉ።
"ከ800 ዓመት በላይ ዕድሜ በማስቆጠራቸው እርጅና ይታይባቸዋል። አልፎ አልፎም ተሰነጣጥቀዋል። ችግሮቹ ሁለት ናቸው። አንዱ በእድሜ ምክንያት የደረሰባቸው ጫና ሲሆን ሁለተኛው ሰው ሠራሽ ጉዳት ነው" ይላሉ።
ችግሮቹን ለመቅረፍ ሲባል በተለያዩ ወቅቶች የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል።
"የተለያዩ ባለሙያዎች ሊጠገኑት ሞክረዋል። በግብጻዊያን እና በጣልያናዊያን መሃንዲሶች የተሠሩ ሥራዎች አሉ። አንዳንዶቹ ጥሩ ሲሆኑ፤ ሌሎቹ ደግሞ ችግሮቹን ያባባሱ ናቸው" ሲሉ አባ ጽጌሥላሴ ያስረዳሉ።
ቤተ ገብርኤል የተሻለ እድሳት እንዳገኘ የሚገልጹት ዲያቆን ፈንታ፤ በዕድሳቱ ምክንያት ተጨማሪ ጉዳት የደረሰባቸው አብያተ ክርስትያናት መኖራቸውንም ይጠቁማሉ።

ቤተ አማኑኤል የተቀባው ቀለም ከፍተኛ ሽታ በማምጣቱ፤ ቀለሙን ፍቆ ለማስለቀቅ የተደረገው ሙከራ የህንጻው ግድግዳ ላይ ጉዳት አድርሷል። ቤተ ጎልጎታ ደግሞ፤ የዝናብ ውሃ ለማውረድ ጣራው ላይ በተለያዩ አቅጣጫዎች ቦይ መሳይ ማፍሰሻ ቢሠራለትም፤ በአራት በኩል ተሰባስቦ የሚወርደው ውሃ ታችኛውን የቅርሱን አካል በመቦርቦር ላይ ይገኛል።
እሳቸው እንደሚሉት፤ ከዚህ ሁሉ በላይ አሳሳቢ የሆነው የአብያተ ክርስትያናቱ መጠለያ ነው።
በ2000 ዓ. ም. አብያተ ክርስትያናቱን ከአደጋ ለመከላከል ሲባል መጠለያ እንዲሠራላቸው ተደርጎ ነበር። ይህ መጠለያ ደግሞ ቅርሶቹ ላይ ጫና በማሳደሩ የብዙዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል።
"እነዚህ ቅርሶች ህልውናችን ናቸው" የሚሉት የላሊበላ ከተማ ነዋሪው አቶ ተገኘ ዋሲሁን፤ "ቅርሶቹ ለእኛ ሃብታችን እና ህልውናችን ናቸው። ሰማያዊ ስጦታ፤ ምድራዊ ርስታችን ናቸው። በተወሰነ የጊዜ ገደብ ለቅርሱ ተብሎ መጠለያ ቢሠራለትም፤ እስካሁን ባለመነሳቱ ለከፋ አደጋ ሊያደርሰው ይችላል" ሲሉ ስጋታቸውን ለቢቢሲ አስርድተዋል።

ሌላው የአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አቶ ቀለሙ ገላው በበኩላቸው፤ "የተሰቀለው ብረት ካለው ክብደት እንጻር ስጋት ደቅኗል። በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ምላሽ አላገኘም" ይላሉ።
እሳቸው እንደሚሉት፤ ከብረት የተሠራው መጠለያ በአምስት ዓመት ውስጥ ይነሳል ቢባልም ለ12 ዓመታት ያህል አልተነሳም። "ብረቱ ካለመነሳቱ በተጨማሪ ብረቱ ያረፈበት ከቤተክርስትያናቱ መሠረት ጋር ተመሳሳይ መሆኑም ስጋት ፈጥሯል" ይላሉ።
ዲያቆን ፈንታ በበኩላቸው ብረቱ ላይ ፍተሻ እንዳልተደረገ ይናገራሉ።
እሳቸው እንደሚሉት፤ ከ10 ሜትር በላይ የሚረዝመው ብረት የቆመው ከህንጻው በላይ ነው። ለምሶሶነት የሚያገለግለው ብረት መሬት ውስጥ ተቆፍሮ የተቀበረ መሠረት የለውም። ስለዚህም ብረቱ ቢንቀሳቀስ ቅርሱ ላይ ቢወድቅ ይችላል። "ዓለም ሁለተኛ ሊሠራው ይቅርና እንዲህ ተብሎ ተሠራ ለማለት የሚከብደውን ቅርስ አደጋ ላይ ጥሏል" ይላሉ።
በተለይ ቤተ አማኑኤል ላይ ያለው መጠለያ፤ ሸራው በስብሶ፣ ቀዳዳ በመፍጠሩ ዝናብ ሰርጎ እየገባ ቅርሱ ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።
"ቤተ መስቀል መሃል ለመሃል ተሰንጥቋል። ቤተ መድኃኒዓለም ጣርያው አፈር ብቻ ሆኗል። ውስጡ ላይም ጉዳት አድርሶበታል" ይላሉ ዲያቆን ፈንታ ስለችግሩ ሲያስረዱ።

በዚህ ሐሳብ አባ ጽጌሥላሴም ይስማማሉ። አሁን ያለው መጠለያ ለአራተኛ ጊዜ የተቀየረ መሆኑን ይናገራሉ።
"የብረቱ እግር የቆመው ዋሻ ወይም ቤተ መቅደስ ላይ ነው። መጠለያው ሲሠራ የነበረው የንፋስ መጠን አሁን በእጥፍ ጨምሯል። ንፋስ ሲኖር ብረቱ ይንቀሳቀሳል። ከባድ ንፋስ ቢመጣና ብረቱ ቢወድቅ ቤተክርስትያኑን ያፈርሰዋል። እግሩ ቢሰምጥም ከስር ያለው መቅደስ ላይ ሊወድቅ ይችላል" ሲሉ ስጋታቸውን ያስቀምጣሉ።
የአማራ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ግዛት አብዩ፤ "ከዕድሜ እና ከአያያዝ ጋር በተያያዘ ጉዳት እየደረሰ በመሆኑ ጊዜያዊ መፍትሔ ሲሰጥ ነበር። አሁን ሲባባስ ከፍተኛ ርብርብ ተደርጓል" ብለዋል።
ጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲያገኝ መስከረም 27፣ 2011 ዓ. ም. ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጎ ነበር። ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ልዑካንም ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ሄደው አቤት ብለዋል።
ችግሩን ቦታው ድረስ በመሄድ የተመለከቱት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ፤ ጉዳዩን ለፈረንሳይ መንግሥት አቅርበው ድጋፍ በጠየቁት መሠረት አዎንታዊ ምላሽ አግኝተዋል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንም ቅርሱን ጎብኝተዋል። በጎ ምላሽም ሰጥተዋል።
"የፈረንሳይ መንግሥት ለቅርሱ ጥበቃ አድርገው መሥራት እንደሚችሉ ቃል ገብተዋል። ሙሉ ለሙሉ የፈረንሳይ መንግሥት የሚሰራው ሲሆን፤ የአገር ውስጥ እና የፈረንሳይ ባለሙያዎችን ያካተተ የቴክኒክ ቡድን ኮሚቴ ተዋቅሯል" ብለዋል አቶ ግዛት።
አባ ጽጌሥላሴ ከዚያ በኋላ ተስፋ እንዳላቸው ይናገራሉ። "ጉዳዩን የሚከታተል ኮሚቴ አለ። የተለያዩ ባለሙያዎች ተካተውበታል። ከመስከረም ጀምሮ ጥናቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል። እኛም ጥገና ይካሄዳል የሚል ተስፋ ነው ያለን" ብለዋል።
ለሥራው የፈረንሳይ መንግስት ከአንድ ሚሊዮን ዩሮ በላይ መድቧል። አቶ ግዛት አብዩ፤ ከመስከረም ጀምሮ የቴክኒክ ሥራ እንደሚጀመር፣ የአማራ ክልልን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ገንዘብ በመመደብ ከቅርሱ ውጭ ያሉ ነገሮች እንደሚሠሩም ገልጸዋል።
ዲያቆን ፈንታ እንደሚሉት፤ እንደ ላሊበላ አይነት ቅርስ ባለመኖሩ ባለሙያዎች ቅርሱን ለመጠገን ሲቸገሩ ይስተዋላል።
"ቅርሱ ከምድር ውስጥ አለት ተፈልፍሎ ዓለም ከሚሠራው ጥበብ በተለየ ነው የተሠራው። ይህን ለመጠገን ባለሙያዎች ሲጨነቁ እናያለን። ጥበቡን ግለጽላቸው ነው የምንለው። እንደዚህ ዓይነት ሥራ በሌላው ዓለም ስለሌለ አንዳንዶቹ ቅርሶቹን መሞከሪያ ነው የሚያደርጓቸው። አንዱ መጥቶ ሠርቶ ይሄዳል፤ ሌላው መጥቶ ትክክል አይደለም በሚል ያንን ያነሳል፤ የራሱን ይቀይራል። በዚህ መልኩ በአብዛኛው ሰው ሠራሽ ችግር ነው የጎዳው" ይላሉ።

አባ ጽጌሥላሴ እንደሚሉት፤ በቤተ መድኃኒዓለም እና በቤተ አማኑኤል ትልቁ ጉዳት አንዱ ባለሙያ መጥቶ የሠራውን ሌላው መጥቶ በመዶሻ እና መቆርቆሪያ ማንሳቱ ነው።
አቶ ግዛት እንደሚናገሩት፤ ቅርሶቹ ላይ መጠለያው ስጋት ቢደቅንም፤ ማንሳቱ የሚወስነው በባለሙያዎች የተቋቋመው የቴክኒክ ቡድን ነው።
"ጉዳት የማያደርስ ከሆነ ይቆያል። የሚጎዳ ከሆነ ደግሞ ያነሳል" ሲሉ ያስረዳሉ።
ዲያቆን ፈንታ "ባይናገር እንኳን እንደ መምህር የሚያስተምር፣ እንደዳቦ እየተቆረሰ የተሠራ፣ በዚህ ዘመን ማንም ሰው ሊሠራው የማይችል ድንቅ ጥበብ በመሆኑ፤ እንጠግናለን ተብሎ የተጀመረው ሃሳብ በአጭር ጊዜ ውስጥ መከናወን አለበት። አንዴ ከፈረሰ ከሃዘን ውጭ የሚጠቅመን ነገር የለም" ይላሉ ።
የዲያቆን ፈንታ ሕልም ሁለት ነው። አንድም ጥንታዊ የሆነውን ቅርስ መጠበቅ። በሌላ በኩል ደግሞ ቅርሱን በማስጎብኘት የሚያገኙትን ጥቅም ማስቀጠል

wanted officials