Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, November 5, 2019

አንጀሊና ጆሊን ለመምሰል በምታጋራቸው ፎቶግራፎች ዕውቅና ያገኘችው ኢራናዊቷ የኢንስታግራም ኮከብ ታሰረች

ሳሃር ታባር፡ ኢራናዊቷ የኢንስታግራም 'የአንጀሊና ጆሊ የሙት መንፈስ' ታሰረች

የሳሃር ታባር የኢንስታግራም ምስል
Image copyrightINSTAGRAM
አጭር የምስል መግለጫሳሃር ታባር ትኩረት የሳበችው የተዋናይት አንጀሊና ጆሊን 'ዞምቢ'[የሙት መንፈስ] ካጋራች በኋላ ነበር
አሜሪካዊቷን ተዋናይ አንጀሊና ጆሊን ለመምሰል ከፍተኛ ርቀት ተጉዛ በምታጋራቸው ፎቶግራፎች ዕውቅና ያገኘችው ኢራናዊቷ የኢንስታግራም ኮከብ መታሰሯን ሪፖርቶች አመለከቱ።
ሳሃር ታባር የታሰረችው በምትለጥፋቸው ፎቶች በማርከስና በማዋረድ፣ ግጭት በመቀስቀስ እንደሆነ ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
ባለፈው ዓመት በኢንስታግራም ገጿ ላይ የምትለጥፋቸው ፎቶግራፎች በከፍተኛ ሁኔታ በኢንተርኔት የተጋሩ ሲሆን፤ በአለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ መነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር።
ሳሃር ምንም እንኳን ተዋናይቷን ለመምሰል 50 ጊዜ የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና አድርጋለች የሚል ወሬ ቢናፈስም፤ የምታጋራቸው ፎቶግራፎች ግን በደንብ የታደቱ [ኤዲት የተደረጉ] እንደሆኑ ተገልጿል።
የ22 ዓመቷ ሳሃር ታባር የአንጀሊና ጆሊን 'ዞምቢ' (ብዙ ጊዜ በአስፈሪ ፊልሞች ላይ የምናያቸው የሙት መንፈስ ገፅታ) ገፀባህርይ በመላበስ በፎቶግራፍና በተንቀሳቃሽ ምስል በማጋራቷ የዓለምን ሚዲያ ትኩረት መሳብ እንደቻለች የቢቢሲ የመካከለኛው ምስራቅ ምሁር ሰባስቲያን አሸር ተናግረዋል።
ምስሉ የተሰረጎዱ ጉንጮች፣ በጣም የሚያስፈራ ፈገግታ እና በካርቱን አሳሳል ስልት የተሠራ ተጣሞ ወደ ላይ ቀጥ ያለ አፍንጫ ያለው ፎቶግራፍ በመለጠፍ ተዋናይት አንጀሊና ጆሊን ለመምሰል ባደረገችው የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና ሳቢያ የተፈጠረባት እንደሆነች አድርጋ ምስሉን ታጋራ ነበር።
ይሁን እንጂ በኢንስታግራም ገጿ ላይ በሚያስደንቅና በሚያስደነግጥ መልኩ የተከታዮቿ ቁጥር መበራከት ምክንያት የምትለጥፋቸው 'የመንፈስ' አምሳያ ፎቶዎች በሜካፕ እንደሆነና፤ ፎቶዎቹም በጥንቃቄ ኤዲት በማድረግ ራሷን ወደ ጥበብ ስራ መቀየሯን ፍንጭ ሰጥታለች።
ከኢንስታግራም ገፅ ላይ የተወሰደ የሳሃር ታባር ምስልImage copyrightINSTAGRAM
አጭር የምስል መግለጫየሳሃር ታባር የኢንስታግራም ገፅ ተሰርዟል
የፍትህ ባለሙያዎች ሳሃርን እንድትታሰር ያደረጉት የተወሰኑ የማህበረሰብ ክፍሎች በእሷ ላይ ቅሬታ በማቅረባቸው እንደሆነ ታስኒም የዜና ኤጀንሲ አስታውቋል።
ጥፋተኛ የተባለችውም በማርከስና በማዋረድ፣ ግጭት በመቀስቀስ፣ በሕገ ወጥ መንገድ ንብረት በማፍራት፣ የአገሪቷን የአለባበስ ሥነ ስርዓት በመጣስ እና ወጣት ዜጎችን ሙስና እንዲሠሩ በማበረታታት እንደሆነ ተነግሯል።
ይህንንም ተከትሎ የኢንስታግራም ገጿም ተዘግቷል።
ሳሃር በኢራን ከሕጉ ጋር የተቃረኑ ነገር ግን ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና የፋሽን ጦማሪያን ዝርዝር ውስጥ ገብታ ነበር።
እስሯን ተከትሎ በተለያዩ የኦንላይን ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ውዝግብ የፈጠረ ሲሆን ፤ ባለሥልጣናቱንም ማውገዛቸውን ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል። በትዊተር ገጽ ላይ ከተንሸራሸሩት ሃሳቦች መካከልም "ግድያ እና ከፍተኛ ማጭበርበር ልትፈፅም ትችል ነበር" የሚል ይገኝበታል።

BBC "የተሰረቅኩ ህፃን መሆኔን ያጋለጠው ሰልፊ" የ21 ዓመቷ ወጣት


የ21 ዓመቷ ሚቺና እህቷ ካሲዲ
ከ17 ዓመታት በፊት በደቡብ አፍሪካዋ ኬፕታውን የሆነ ነበር፤ የነርስ ልብስ የለበሰች ሴት ከጎሮቲ ሹር ሆስፒታል የሦስት ቀን ህፃንን በእቅፏ አድርጋ የወጣችው።
ህፃኗ እንቅልፍ ከጣላት እናት የተሰረቀች ነበረች። የዚያን ጊዜዋ የሦስት ቀን ህፃን የዛሬዋ የ21 ዓመት ወጣት ሁለት እናቶቿን፤ ከሆስፒታል የሰረቀቻትንና ትክክለኛ ወላጅ እናቷን ልታውቅ የቻለችው በአጋጣሚ ተነስታ በማህበራዊ መገናኛ መድረክ ላይ በለጠፈቸው በሞባይሏ እራሷ ባነሳችው (ሰልፊ) ፎቶግራፍ እንደሆነ ትናገራለች።
በኬፕታውኑ ዝዋንስያክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነቸው የ21 ዓመቷ ሚቺ ሶሎሞን ማንነቷን የገለጠውን ሰልፊ ፎቶ የለጠፈችው እንደ አውሮፓዊያኑ በ2015 አዲስ የትምህርት ዓመት መጀመሩን በማስመልከት ነበር።
ሚቺ ፎቶውን እንደለጠፈች ተማሪዎች ግር ብለው መጥተው ከእሷ በሦስት ዓመት የምታንስ ነገር ግን ቁርጥ እሷን የሆነች ካሲዲ ነርስ የምትባል አዲስ ተማሪ እንዳለች ይነግሯታል።
መጀመሪያ ላይ ሚቺ ነገሩን ችላ ብትለውም አንድ ቀን ከተባለችው ልጅ ጋር አንድ ቦታ ላይ ሲተላለፉ ልተገልፀው የማትችለው ስሜት ይሰማታል።
"የማውቃት ያህል ነው የተሰማኝ ለምን እንደዛ እንደተሰማኝ አላውቅም። በጣም አስደንጋጭ አጋጣሚ ነበር" ትላለች ሚቺ ከማታውቃት እህቷ ጋር በተላለፉበት ቅፅበት የተሰማትን ስትገልፅ።
ከዚያም እህትማማቾቹ አብረው ጊዜ ማሳለፍ ጀመሩ፤ ከዚያም አንድ ላይ የተነሱትን ሰልፊ ሁለቱም ለጓደኞቻቸውና ለወላጆቻቸው አሳዩ።
ሚቺ ሶሎሞንImage copyrightMPHO LAKAJE
አንዳንድ ጓደኞቿ ለሚቺ "ምናልባት ለወላጆችሽ የማደጎ ልጅ እንዳትሆኚ?" የሚል ጥያቄ አነሱ።
የካሲዲ ወላጆም ሚቺን መጠየቅ የሚፈልጉት ነገር እንዳለ ለልጃቸው ካሲዲ ነገሯት። ካሲዲም የተወለድሽው በዚህ ቀን በዚህ ዓመት ነው ወይ? ስትል ሚቺን ጠየቀቻት። "ፌስቡክ ላይ ስትሰልይኝ" ነበር በማለት መጀመሪያ በነገሩ በስጨት ብትልም በትክክልም በተባለው ጊዜ እንደተወለደች ሚቺ አረጋገጠች።
ከሳምንታት በኋላ ሚቺ የትምህርት ቤታቸው ዳይሬክተር ቢሮ ተጠርታ ከ17 ዓመታት በፊት በኬፕታውኑ የጎሪቲ ሆስፒታል የሦስት ቀን ህፃን መሰረቅን የሚያመለክት ታሪክ በህበራዊ ሰራተኞች ይነገራታል።
'ይህን ታሪክ ለእኔ የሚነግሩኝ ለምንድን ነው?' በሚል ግራ ስትጋባ እሷ ያቺ ህፃን ለመሆኗ ማስረጃዎች መኖራቸው ተገለፀላት።
ሚቺም የተወለደችው ሌላ ሆስፒታል እንደሆነና የልደት ሰርተፊኬቷን ማየት እንደሚቻል በመግለፅ ለመከራከር ብትሞክርም እሷ የጠቀሰችው ሆስፒታል ስለመወለዷ ሆስፒታሉ ምንም ማስረጃ እንደሌለው አስረዷት።
በመጨረሻ የዲኤንኤ ምርመራ ማድረግ ግድ ሆነ። ሚቺና ከ17 ዓመታት በፊት ከጉሪቲ ሆስፒታል ልጇ የተሰረቀችባት ዜፋኒ ነርስ (የካሲዲ እናት) ምርመራውን አደረጉ። በማያጠራጥር ሁኔታ የምርመራ ውጤታቸው አንድ አይነት ሆነ።
"ባሳደገችኝ እናቴ ላይ ትልቅ እምነት ነበረኝ። በተለይም ስለማንነቴ በፍፁም ዋሽታኝ አታውቅም ብዬ አስቤ ምርመራው በጭራሽ ሊመሳሰል አይችልም ብዬ እርግጠኛ ሆኜ ነበር" ብላ ነበር ሚቺ።
ነገሮች እንዳላሰበችው ሆነው እሷ ያሳዳጊዋ ሳትሆን በድንገት ያወቀቻት የካሲዲ እናት ልጅ ሆኗ ራሷን አገኘችው።

Monday, November 4, 2019

የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ታዳጊዎች ኳስ በቴስታ እንዳይመቱ ሊያግድ ነው


ኳስ በጭንቅላቱ የሚመታ ልጅImage copyrightGETTY IMAGES
የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ከአንጎል ጤንነት ጋር በተያያዘ የወጣ ሪፖርትን ተከትሎ ከ12 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ኳስ በቴስታ እንዳይመቱ እገዳ ለመጣል እያሰበ መሆኑ ተነገረ።
በግላስጎው ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ባለሙያዎች እንደደረሱበት የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋቾች አንጎልን እያዳከመ ለሞት በሚያበቃ የአንጎል በሽታ የመጋለጥ እድላቸው ከሦስት ጊዜ በላይ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የስኮትላንድ እግር ኳስ የበላይ አስተዳዳሪ ከህክምና ባለሙያዎች ጋር ከተነጋገረ በኋላ ያሉ አማራጮች ላይ ውሳኔ እንደሚሰጥ ተነግሯል።
አሜሪካ ውስጥ ከአምስት ዓመት በፊት ጀምሮ ታዳጊ ህጻናት ኳስ በጭንቅላታቸው እንዳይመቱ እገዳ ተጥሏል።
በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ በጭንቅላት (በቴስታ) ኳስ መምታት በአንጎል ደህንነት፣ በተለይም በህጻናት ላይ የሚኖረውን ውጤት በተመለከተ ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክር ተከትሎ ስኮትላንድ ውስጥ ክልከላ ሊቀመጥ እንደሚችል እየተነገረ ነው።
አንድ ውስጥ አዋቂ እንዳሉት "ጉዳዩ ታዳጊዎች በእግር ኳስ ጨዋታ ወቅት ኳስ በጭንቅላታቸው የመግጨት አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን በልምምድ ወቅት በተደጋጋሚ ኳስን በጭንቅላት መምታትን ይመለከታል" ብለዋል።
የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ዋና የህክምና አማካሪ የሆኑት ዶክተር ጆን ማክሊን ባለፈው ሳምንት ለቢቢሲ ኳስን በጭንቅላት በመምታት በታዳጊ ተጫዋቾች ላይ የሚፈጠረውን ጫና ለመቀነስ እርምጃ እንዲወሰድ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
ዶክተሩ እንዳሉት "ከስኮትላንድና ከአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ጋር በመሆን ተቀባይነት ያለው መመሪያ ለማዘጋጀት ሥራ ጀምረናል። "
"ለምሳሌም ለታዳጊዎች የሚሰጠውን ኳስ በጭንቅላት የመምታት ልምምድ የተወሰነ እንዲሆንና አንጎላቸው ለማገገም እንዲችል በሳምንት የሚሰጣቸው ስልጠና አንድ ጊዜ ብቻ እንዲሆን ማድረግን የመሰለ ቀላል እርምጃ ሊሆን ይችላል" ብለዋል።
የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ውስጥ አዋቂ እንዳሉት የማህበሩ አመራር ቡድን ታዳጊዎች ኳስ በጭንቅላታቸው መምታትን በተመለከተ የቀረበውን የባለሙያ አስተያየት ይደግፈዋል ብለዋል።
በግላስጎው ዩኒቨርስቲ ለተደረገው ጥናት መነሻ የሆነው የቀድሞው ዌስት ብሮም አጥቂ ጄፍ አስቴል ለህልፈት የተዳረገው በተደጋጋሚ በጭንቅላቱ ላይ በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ነው የሚል አስተያየት ከተሰነዘረ በኋላ ነው።
በ2002 (እኤአ) አስቴል ከሞተ በኋላ፣ በጥናቱ መዘግየት ቤተሰቦቹ ቁጣቸውን በመግለጻቸው፣ በእግር ኳስ ማህበሩና በፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር አነሳሽነት ጥናቱ ተደርጓል።
የሟቹ እግር ኳስ ተጫዋች ሴት ልጅ የሆነችው ዳውን ጥናቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ በውጤት "እንደደነገጠች" ተናግራለች።

Sunday, November 3, 2019

የሮናልድ ሬገን ቤተ መጻሕፍትን ከካሊፎርኒያ እሳት የታደጉት ፍየሎች


ቡናማ ፍየል
Image copyrightGETTY IMAGES
ለቀናት በሰደድ እሳት የተለበለበችው ካሊፎርኒያ ከወራት በፊትም ተመሳሳይ መጥፎ እጣ ደርሶባት ነበር።
የተራቡ 500 ፍየሎች ባይታደጉት ኖሮ የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬገን ፕሬዘዳንታዊ ቤተ መጻሕፍትም ካሊፎርኒያን ካቃጠላት ሰደድ እሳት አይተርፍም ነበር።
የቤተ መጻሕፍቱ ዙሪያ ተቀጣጣይ በሆኑ ደረቅነት ባህሪ ባላቸው ተክሎች የተከበበ በመሆኑ በሰደድ እሳቱ ለመበላት የተዘጋጀ ቦታ ስለነበር ባለፈው ግንቦት ላይ የተራቡ 500 ፍየሎች እነዚህን ተክሎች እንዲበሉ ቦታው ላይ ተሰማሩ።
ፍየሎቹ ተቀጣጣይ አትክልቶቸን ለመብላት ሥራ የተሰማሩት ከአንድ ፍየል አርቢ ኩባንያ በቅጥር መልክ ነበር።
ሰደድ እሳቱ ቤተ መጻሕፍቱ ላይ ደርሶ የነበረ ቢሆንም የተራቡት ፍየሎች ከስር ከስር ተቀጣጣይ አትክልቶቹን መብላታቸው ቦታው ላይ ለተሰማሩት የእሳት አደጋ መከላከል ሠራተኞች እሳቱን ለመቆጣጠር ጊዜ ሰጣቸው።
የእሳት አደጋ ሠራተኞቹ ፍየሎች ሥራቸውን እጅግ እንዳቀለሉላቸው እንደተናገሩ የቤተ መጻሕፍቱ ሥራ አስኪያጅ ሜሊሳ ጊለር ለሮይተርስ ተናግረው ነበር።
መጀመሪያ 13 ኤክር መሬት እየበሉ ለማፅዳት የተቀጠሩት 805 ፍየሎች ነበሩ።
ፍየሎቹ የመጡበት ኩባንያ ባለቤት ስኮት ሞሪስ በአንድ ኤክር መሬት ለፍየሎቹ ስራ አንድ ሺህ ዶላር እንደሚከፈል ገልፀዋል።
ካሊፎርኒያ በሰደድ እሳት መቃጠል ከቀጠለች የፍየሎቻቸውን ቁጥር መጨመር እንደሚኖርባቸውም ገልፀዋል።

Saturday, November 2, 2019

አልኮል የማይሸጥባቸው መጠጥ ቤቶች Bars which dont sell Alchohol



Image copyrightGETTY IMAGES
ወደ አንድ ግሮሰሪ ገብተው 'እስቲ የሚጠጣ ነገር?' ብለው ሲጠይቁ አልኮል አንሸጥም ብትባሉ ምን ይሰማችኋል? በአሁኑ ወቅት እንደ ኒውዮርክና ለንደን ባሉ ከተሞች ግን አልኮል የማይሸጥባቸው መጠጥ ቤቶች እየተለመዱ መጥተዋል።
ለብዙዎች አልኮል የማይሸጥበት መጠጥ ቤት ልክ አሳ እንደሌለው የአሳ ገንዳ አልያም ዳቦ የማይሸጥበት ዳቦ ቤት ይመስላል። ነገር ግን መጠጥ ቤቶች ለብዙ ሰዎች እንደ ሁለተኛ ቤታቸው በሚያገለግልበት ዘመን ምን ያክል ሰዎች በዚህ ሃሳብ ይስማሙ ይሆን?
ሳም ቶኒስና ጓደኛው ረጂና ዴሊያ 'ጌትዌይ' የተባለ አልኮል የማይሸጥ መጠጥ ቤት በኒውዮርክ ከተማ ከፍተዋል። ሳም እንደሚለው የዚህን አይነቱን መጠጥ ቤት ለመክፈት ሃሳብ የመጣለት ከሦስት ዓመታት በፊት ነበር።
ሳምና ወንድሙ መጠጥ የማይሸጥበት መዝናኛ ቤት ፍለጋ ኒውዮርክን ቢያስሱም አንድ ቤት እንኳን ማግኘት እንዳቃታቸው ያስታውሳል።
''ወጣ ብለን ምንም አይነት አልኮል ሳንጠጣ መዝናናት ብንፈልግም እጅግ ከባድ ነው። ለብዙ ሰዎችንም ይህንን ጥያቄ ሳቀርብላቸው በሚያስገርም ሁኔታ አልኮል መጠጣት የማይፈልጉ እንዳሉ ተረዳሁ።''
ከዚህ ልምዳቸው በመነሳት ሳምና ጓደኛው ምንም አይነት አልኮል የማይሸጥበት አነስተኛ ግሮሰሪ ከፍተዋል። ሌላው ቢቀር የአልኮል መጠናቸው እጅግ አነስተኛ የሆኑ መጠጦች እንኳን በዚህ ግሮሰሪ አይሸጡም።
በአሜሪካ ህግ መሰረት 0.5 በመቶና ከዚያ በታች አልኮል መጠን ያላቸው መጠጦች ከአልኮል ነጻ ተብለው ነው የሚተዋወቁት። ነገር ግን የሳምና ጓደኛው ግሮሰሪ ለእንደዚህ አይነቶቹ መጠጦች እንኳን ቦታ የላቸውም።
''ከእኔ ልምድ በመነሳት አልኮል መጠጣት አይደለም የአልኮል ሽታ እንኳን የሚረብሻቸው ሰዎች ብዙ ናቸው። ምክንያታቸው ግላዊም ሊሆን ይችላል፤ ሃይማኖታዊም ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የእነሱንም ፍላጎት መጠበቅ ተገቢ ይመስለኛል'' ብሏል ሳም።
ጌትዌይ ባርና ግሮሰሪ ልክ እንደማንኛውም መጠጥ ቤት ምሽት ላይ የሚከፈተው ሲሆን መብራቶቹም ቢሆኑ ደብዘዝ ያሉ ናቸው። ስለዚህ ወደውስጥ የሚገባ ሰው ከሌሎች መጠጥ ቤቶች ምንም የተለየ ነገር አይመለከትም።
እንደ ጌትዌይ ወዳሉ መጠጥ ቤቶች የሚሄዱ ደንበኞች ሁሉም አልኮል ከነጭራሹ የማይጠጡ አይደሉም። ምናልባት በቀጣይ ቀን ሥራ ኖሮባቸው ቀለል ያለ ምሽት የፈለጉ ሊሆኑ ይችላሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ከስካር መንፈስና ከሰካራሞች ራቅ ብለው መዝናናት የሚፈልጉ ናቸው።
ሰክራ የተኛች ሴትImage copyrightGETTY IMAGES
ሎሬሊ ባንድሮቭስኪ የ32 ዓመት ወጣት ነች። ኒውዮርክ ውስጥ ከአልኮል ነጻ የሆኑ መጠጥ ቤቶችን ለብዙ ጊዜ ስታበረታታ እንደቆየች የምትናገረው ሎሬሊ እንደ 'የጌትዌይ' ያሉ መተጥ ቤቶች መከፈት ለብዙዎች ደስታን ይፈጥራል።
''መጠጥ ቤቶች መዝናኛ ነው መሆን ያለባቸው። ሁሌም ቢሆን መዝናኛ ሲባል መጠጥና መስከር ይያያዛሉ። የማናስታውሳቸውና ብዙ ጊዜ የምንጸጸትባቸው ነገሮችን የምናደርገው አልኮል ስንጠጣ ነው። ይህንን ማስቀረት ከተቻለ ለእኔ ተመራጭ ነው'' ትላለች።
በቅርቡ እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በመላው ዓለም ያሉ ወጣቶች የአልኮል ፍጆታቸውን እየቀነሱ ነው። የእንግሊዙ ስታትስቲክስ ቢሮ በሰራው የዳሰሳ ጥናት መሰረት ጥያቄው በቀረበላቸው ወቅት ለአንድ ሳምንት ያክል አልኮል ያልጠጡ ወጣቶች ቁጥር 56.9 በመቶ ደርሶ ነበር።
በተመሳሳይ መልኩ በአሜሪካ የሚገኙ ጎልማሶች ላይ በተሰራ ሌላ ጥናት 52 በመቶ የሚሆኑት ሰዎች የአልኮል መጠናቸውን እየቀነሱ አልያም ለመቀነስ እያሰቡ እንደሆነ ተናግረዋል።
ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ከአልኮል ነጻ የሆኑ መጠጦች መለመዳቸውና አልኮል የማይሸጥባቸው መጠጥ ቤቶች መበራከት የሚያስተላልፈው መልዕክት ያለ ይመስላል።
ሰዎች ለመዝናናት ግድ አልኮል መተጣት የለባቸውም የሚለው ሃሳብም ተቀባይነት እያገኘ ነው።

የፕሬዘዳንቱን ፊት ቆርጦ በሱ ፎቶ ላይ በመለዋወጡ ተይዞ የነበረው ቀልደኛ (ኮሜድያን) ተለቀቀ


ቀልደኛው ኢድሪስ ሱልጣን እና ፕሬዘዳንት ጆን ማጉፉሊ ፊታቸው ተቀያይሮ የሚያሳየው ምስልImage copyrightIDRIS SULTAN/ TWITTER
አጭር የምስል መግለጫቀልደኛው ኢድሪስ ሱልጣን እና ፕሬዘዳንት ጆን ማጉፉሊ ፊታቸው ተቀያይሮ የሚያሳየው ምስል

ፎቶውን ከታንዛንያው ፕሬዘዳንት ጆን ማጉፉሊ ጋር በመለዋወጡ ተይዞ የነበረው ቀልደኛ (ኮሜድያን) ኢድሪስ ሱልጣን በዋስ ተለቀቀ።
ታንዛንያዊው ኮማኪ ዘና ብሎ ከተነሳው ፎቶ ላይ የፊት ገጽታውን ቆርጦ በመውሰድ፤ ፕሬዘዳንቱ ኮስተር ብለው የሚያሳይ ፎቶግራፍ ላይ አስቀምጦታል። የፕሬዘዳንቱን ፊት ቆርጦም በሱ ፎቶ ላይ በሚታየው ፊቱ ተክቶታል።

ኮሜድያኑ፤ እሱና ፕሬዘዳንቱ ፊት ተለዋውጠው የሚያሳየውን ፎቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ማጋራቱን ተከትሎ ለምርመራ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ ነበር።
የኢድሪስ ጠበቃ ኢሊያ ሪዮባ፤ በአገሪቱ የመረጃ ደህንነት ሕግ መሰረት እንደተያዘ ገልጸዋል። በሕጉ ሰዎችን ማስመሰል የተከለከለ ነው። ቀኝ ዘመም የመብት ተሟጋቾች ሕጉ የመናገር ነጻነትን ይገድባል ሲሉ ተችተዋል።
ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉት ኢድሪስ ፎቶውን ሲለቅ "ፕሬዘዳንቱ ልደታቸውን በሰላም እንዲያከብሩ ከእኔ ጋር ሚና ተለዋውጠዋል" ሲል በስዋሂሊ ጽፏል።
ፎቶውን ከለጠፈ በኋላ የዳሬ ሰላም ፖሊስ ኮሚሽነር ፖል ማኮንዳ "ሥራው ምን ድረስ የተገደበ እንደሆነ አያውቅም" ብለዋል።
ፕሬዘዳንቱ 60ኛ ዓመት ልደታቸውን ያከበሩት ባለፈው ማክሰኞ ሲሆን፤ ቀልደኛው ለምርመራ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ የነበረው እሮብ ነበር።

ወንድሟን ለማስታመም በሰላሳ ሳንቲም ብቻ የኖረችው ቻይናዊት


ቻይናዊቷ ዉ ሁያን ላለፉት አምስት ዓመታት የኖረችው በቀን ሰላሳ ሳንቲም ብቻ እያወጣች ነበር
Image copyrightFENG VIDEO
አጭር የምስል መግለጫቻይናዊቷ ዉ ሁያን ላለፉት አምስት ዓመታት የኖረችው በቀን ሰላሳ ሳንቲም ብቻ እያወጣች ነበር
ቻይናዊቷ ዉ ሁያን ላለፉት አምስት ዓመታት የኖረችው በቀን ሰላሳ ሳንቲም ብቻ እያወጣች ነበር። ሕይወቷን በሰላሳ ሳንቲም (ሁለት ዮዋን) ትገፋ የነበረው ቆጣቢ ስለሆነች ሳይሆን ታማሚ ወንድሟን የማስተዳደር ግዴታ ስለወደቀባት ነበር።
ሰላሳ ሳንቲም (በአሜሪካ ዶላር ምንዛሬ) በቂ ምግብ ሊገዛላት ያልቻለው የ24 ዓመጠቷ ቻይናዊት፤ በምግብ እጥረት ሳቢያ ሆስፒታል ገብታለች። ዜናውን የሰሙ ቻይናዊያን ወደ አንድ ሚሊዮን ዮዋን (114,000 ዶላር) አሰባስበውላታል።
ዉ ሁያን የኮሌጅ ትምህርቷን እየተከታተለች ጎን ለጎን ወንድሟን ለማስታመም ትጥር ነበር። በያዝነው ወር መባቻ ላይ መተንፈስ ሲያቅታት ወደ ሆስፒታል የሄደችው ቻይናዊት፤ ክብደቷ 20 ኪሎ ግራም ብቻ ደርሶ ነበር።
ባለፉት አምስት ዓመታት በቂ ምግብ ባለማግኘቷ የልብና የኩላሊት ችግር እንደገጠማት ሀኪሞች ተናግረዋል።
የዉ ሁያን እናት የሞቱት የአራት ዓመት ልጅ ሳለች ነበር። አባቷ ደግሞ ተማሪ ሳለች ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። እሷና ወንድሟን ከሚረዷቸው ዘመድ አዝማዶች የሚገኘው ገንዘብ ባጠቃላይ የአዕምሮ ህመም ላለበት ወንድሟ ህክምና ይውላል።
ስለዚህም ቻይናዊቷ በቀን ማውጣት የምትችለው ሰላሳ ሳንቲም ብቻ ነበር። በሰላሳ ሳንቲም ቃርያ እና ሩዝ ገዝቶ ከመብላት ውጪ አማራጭ አልነበራትም።
ዉ ሁያን እና ወንድሟ የተወለዱበት የቻይናው ጉዋንዡ ግዛት በርካቶች በድህነት የሚማቅቁበት እንደሆነ ይነገራል።
በምግብ እጥረት ምክንያት ሆስፒታል ስትገባ ብዙዎች መንግሥት ተገቢውን ድጋፍ ሊያደርግላት ይገባ ነበር ብለው ቁጣቸውን ገልጸዋል። ቻይና የኮምኒስት ፓርቲ አገዛዝን 70ኛ ዓመት ለማክበር አላስፈላጊ ወጪ ማፍሰሷን በማጣቀስ መንግሥትን ያብጠለጠሉም አልታጡም።
የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዉ ሁያን የምትማርበት ኮሌጅ ለምን አልደገፋትም? ሲሉም ወቅሰዋል። የክፍል ጓደኞቿ ወደ 40,000 ዩዋን (5,700 ዶላር) የደጎሙ ሲሆን፤ ከትውልድ ቀዬዋም ድጋፍ ተሰጥቷታል።
የቻይና መንግሥት በየወሩ ከ300 እስከ 700 ዩዋን እንደሚለግስ አስታውቋል። አሁን በድንገተኛ አደጋ ድጋፍ 20,000 ዩዋን እንደሚሰጣትም ተገልጿል።
ምንም እንኳን የቻይና ምጣኔ ኃብት ቢመነደግም ድህነት ሙሉ በሙሉ አልተወገደም። አገሪቱ እኩልነት የሰፈነባትም አይደለችም።
ከሁለት ዓመት በፊት የወጣ መረጃ እንደሚያሳየው፤ 30.46 ሚሊዮን ቻይናውያን ከድህነት ወለል በታች ይኖራሉ።
ቻይና በ2020 ድህነትን እቀርፋለሁ ብትልም፤ ከገቢ አንጻር በዜጎቿች መካከል የሰማይና የምድር ልዩነት ያለባቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ ትገኛለች።

ያላሉትን እንዳሉ የሚያስመስለው የዋትስአፕ መተግበሪያ Whatsapp

የዋትስአፕ መለዕክትዎን የሚበረበረው መሣሪያ

Image copyrightREUTERS
ደህንነቱ የተጠበቀ ነው ሲባልለት የነበረውን ዋትስአፕን ሰብሮ የሚገባና የተጠቃሚዎችን መልዕክት በመለወጥ ያላሉትን እንዳሉ አድርጎ የሚያቀርብ አዲስ መተግበሪያ [አፕ] እንዳለ ተደረሰበት።
የመረጃ መረብ ደህንንት (ሳይበርሴኪዩሪቲ) ባለሙያዎች፤ አንድ መተግበሪያ የዋትስአፕ መልዕክትን በመበዝበር ተጠቃሚዎች ያላሉትን ነገር እንዳሉ በማስመሰል ማጭበርበር እንደሚችል ደርሰንበታል እያሉ ነው።
ኦዴዎ ቫኑኑ የተሰኙ ባለሙያ ለቢቢሲ ሲናገሩ መሣሪያው ተጠቃሚዎች ዋትስአፕ ላይ የተላላኩትን መልዕክት አጭበርባሪዎች እንደሚፈልጉት ማጣመም እንዲችሉ ዕድል ይሰጣል ይላሉ።
ለምሳሌ እርስዎ ለወዳጅ ዘመድዎ የላኩትን የሰላምታ መልዕክት ወደ ሐሰተኛ ዜና በመቀየር ለሌላ የዋትስአፕ ተጠቃሚ ወይም ቡድን መላክ ያስችላል።
ላስ ቬጋስ ላይ በተካሄደ አንድ የሳይበርሴኪዩሪቲ ምክክር ላይ ይፋ የተደረገው ይህ መዝባሪ መሣሪያ 'የኮምፒውተር መዝባሪዎች የዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን መልዕክት እንዳሻቸው እንዲሾፍሩ ያስችላል' ተብሎለታል።
የዋትስአፕ ባለቤት የሆነው ፌስቡክ ስለጉዳዩ አስተያየት እንዲሰጥ ቢጠየቅም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል።
«ሰዎች ዋትስአፕ ላይ የፃፉትን የትኛውንም መልዕክት መቀየር ይቻላል» ይላሉ ኦዴዎ። አልፎም የእውነተኛውን ዋትስአፕ ተጠቃሚ ማንነት መቀየር እንዲሚያስችል ባለሙያው ይናገራሉ።
አንድ መሰል አጭበርባሪ መተግበሪያ ደግሞ ለሰው 'ኢንቦክስ' ያደረጉትን መልዕክት አስተያየት [ኮሜንት] በማስመሰል ያወጣ ነበር። ነገር ግን ፌስቡክ ይህንን መተግበሪያ ማስወገድ መቻሉን ባለሙያው ይናገራሉ።
ይህኛውን የዋትስአፕ መልዕክት ቀማኛ ለመከላከል ግን ፌስቡክ አቅሙ የለኝም የሚል ምላሽ እንደሰጣቸው የመረጃ መረብ ደህንንት ባለሙያው ኦዴዎ ይገልፃሉ።
ይህንን መሣሪያ የፈጠሩት ሰዎች ዓላማ ምን ይሆን? ተብለው የተጠየቁት ባለሙያው ዋነኛው ሃሳብ ዋትስአፕ ተጋላጭ መሆኑን ለማሳየትና ደህንነቱን የበለጠ ሊያጠናክር እንደሚገባ ለማሳሰብ ነው ይላሉ።
«ዋትስአፕ ከዓለም ሕዝብ 30 በመቶ ያህሉን ያገለግላል። እኛ ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን። ሐሰተኛ ዜና [ፌክ ኒውስ] ትልቅ አደጋ ጋርጦብናል። ሁለን እርግፍ አድርገን ምንም እንዳልተፈጠረ ማስመሰል የለብንም።»
ዋትስአፕ የሐሰተኛ ዜና ማስፋፊያ አንዱ መድረክ እንደሆነ ይነገርለታል፤ በተለይ ደግሞ በሕንድ እና ብራዚል። የሃሰተኛ መረጃዎቹ ሥርጭት ግጭት ከማስነሳት አልፎ የሰው ሕይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል።
ዋትስአፕ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ መላዎችን ቢያቀርብም አደጋው ሙሉ በሙሉ የተቀረፈ አይመስልም።

ፌስቡክ ሐሰተኛ ዜናዎችን መለየት ሊጀምር ነው facebook to identify fake news

ፌስቡክImage copyrightAFP
ፌስቡክ የሚሠራጩ ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል ያለመ አዲስ ስልት ሊተገብር መሆኑን አስታወቀ።
አንጋፋው የማህበራዊ ሚዲያ መድረክ የሆነው ፌስቡክ፤ በመግለጫው ላይ እንዳለው በፌስቡክና በኢንስታግራም ላይ የሚሠራጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን ሦስተኛ ወገንን በመጠቀም ጥሬ ሐቁን ሊያጠራ እንደሆነ ገልጿል።
ፌስቡክ በቅርቡ ጥሬ ሐቅ አረጋጋጭ ፕሮግራሙን ከሰሃራ በታች ባሉ 10 አገራት ያስፋፋ ሲሆን እነዚህም ኢትዮጵያ፣ ዛምቢያ፣ ሶማሊያ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኒ እና ጋና ናቸው።
የአፍሪካ ፖሊሲ ዋና ኃላፊ ኮጆ ቦክይ እንዳሉት ፕሮግራሙ እንደ አፍሪካ ቼክ፣ ፔሳ ቼክ፣ ዱባዋ፣ ፍራንስ 24 እና ኤ ኤፍ ፒ ፋክት ቼክ ካሉ አጋር ድርጅቶቻቸው ጋር በጋራ በመሆን ይተገበራል።
እነዚህ ድርጅቶች በፌስቡክ ላይ የሚሠራጩ ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመቆጣጠር በጨረታው ተሳትፈዋል።
"በፌስቡክ ላይ የሚሠራጩ ሐሰተኛ መረጃዎችን መዋጋት ትኩረት የምንሰጠው ጉዳይ ነው። ሐሰተኛ ዜና ምን ያህል ችግር እንደሆነ እናውቃለን፤ በመሆኑም ችግሩን ለመፍታት እነዚህ እርምጃዎች ወሳኝ ናቸው" ብለዋል ኃላፊው።
ኮጆ ቦክይ አክለውም ሦስተኛ ወገን ጥሬ ሐቅ አረጋጋጭ ብቻውን ለችግሩ መፍትሔ ባይሆንም፤ ሰዎች ፌስቡክ ላይ የሚያዩዋቸውን መረጃዎች ጥራት ለማሻሻል ከሚያከናውኗቸው በርካታ ተግባራት መካከል ይህ አንዱ ነው።
"በርካታ ሥራዎችን አከናውነናል፤ አሁንም ፌስቡክ የበርካታ ሃሳቦች መንሸራሸሪያ እንዲሆን ለማረጋጋጥ እንጂ የሀሰተኛ መረጃዎች መናሃሪያ እንዲሆን አንፈልግም" ብለዋል።።

በፌስቡክ የሐሰት ዜና ለማሰራጨት ሲል ፖለቲካኛ ለመሆን ያሰበው ግለሰብ

አድሪዬል ሃምፕተንImage copyrightADRIEL HAMPTON/ WIKIMEDIA
በማህበራዊ ሚዲያዎች የሀሰት ዜና ማሰራጨት ትፈልጋላችሁ? እንግዲያውስ ፖለቲካኛ ብትሆኑ ያዋጣችኋል፤ ይላል አሜሪካዊው አክቲቪስት አድሪዬል ሃምፕተን። ፖለቲካዊ ማስታወቂያዎች ላይ ፌስቡክ ያለውን አቋም መፈተሽ እፈልጋለው ብሏል አድሪዬል።
ሳንፍራንሲስኮ የሚገኘው አድሪዬል ሃምፕተን ፌስቡክ ፖለቲካዊ ቅስቀሳዎችን ምንም ማጣራት ሳያደርግ እንዲተላላፉ ይፈቅዳል፤ የሌሎች ሰዎችን መልዕክት ግን አብጠርጥሮ ይመለከታል ሲል ይከሳል።
ለሃሳቡ ማጠናከሪያ እንዲሆነው ደግሞ በ2022 ለሚካሄደው ምርጫ በካሊፎርኒያ ተፎካካሪ ለመሆን አስቧል። በዚያውም ሐሰተኛ ፖቲካዊ መልዕክቶቹን በፌስቡክ ያስተላልፋል።
''የዚህ ሃሳብ ዋነኛው ግብ ፌስቡክ በፖለቲካዊ መልዕክቶች ላይ የሚያደርገውን ቁጥጥር መመርመርና እንደ ዶናልድ ትራም ያሉ ፖለቲከኞች ሐሰተኛ መልዕክታቸውን ሲያስተላልፉ ዝም እየተባሉ ሌሎች ላይ እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግ ማሳየት ነው'' ብሏል አድሪዬል።
ፌስቡክ በበኩሉ ይህ ሰው ይህንን በማለቱ በራሱ ሐሰተኛ ዜና እያስተላለፈ ነው ጉዳዩንም በቀላሉ አልተወውም ብሏል።
ፌስቡክ የምትጠቀም ሴትImage copyrightPA MEDIA
ማህበራዊ ሚዲያን ከሚጠቀሙ ሰዎች መካከል 99 በመቶ የሚሆኑትን እንወክላለን የሚለው የበይነ መረብ ሊግ አባል የሆነው አድሪዬል፤ ግባችን አጥባቂ ፖለቲከኞች በማህበራዊ ሚዲያዎች እንዴት ጡንቻቸውን እንደሚጠቀሙ ማሳየትን መከላከል ነው ይላል።
''ከሩሲያ የኢንተርኔት ምርምር ኤጀንሲ እስከ ትራምፕ 'ዲጂታል ብሬይን ትረስት' ድረስ ፖለቲከኞች በማህበራዊ ሚዲያ ቀውስ በመፍጠር ነው የሚታወቁት። እኛ ደግሞ እነሱን እየተዋጋን ነው'' ይላል አድሪዬል።
አክሎም ''ማህበራዊ ሚዲያ በጣም ትልቅ አቅም አለው። ፌስቡክ በራሱ የምርጫ ሂደቶችን ማስቀየር ይችላል'' ብሏል።
የአድሪዬል ውሳኔ የፌስቡክ 200 ሰራተኞች ለዋና ሥራ አስኪያጁ ማርክ ዙከርበርግ ድርጅቱ ፖለቲካዊ መልዕክት ያላቸው ማስታወቂያዎችን በተመለከተ ስላለው ፖሊሲ ይፋዊ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ የመጣ ነው።
''ነጻ ንግግርና የተከፈለባቸው ንግግሮች እኩል አይደሉም'' ይላል ሰራተኞቹ የጻፉት ደብዳቤ። ''በፖለቲካዊ ሃላፊነቶች ላይ ያሉ ሰዎችና ለስልጣን የሚወዳደሩ ፖለቲከኞች ስለሚያስተላልፉት መልዕክት ቁጥጥር አለመደረጉ ከፌስቡክ ዓላማ ጋር ይጣረሳል'' ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አድሪዬል ሃምፕተን ለፖለቲካዊ ስልጣን እወዳደራለሁ ማለቱን ተከትሎ ፌስቡክ የመረጃ ማጣራት ካደረግኩ በኋላ ፖለቲካዊ መልዕክቶቹን አጠፋቸዋለው ብሏል። ጉዳዩ ደግሞ ወደ ፍርድ ቤት ሊያመራ እንደሚችል እየተዘገበ ነው።
የፌስቡክ ቃል አቀባይ ለሲኤንኤን በሰጡት መግለጫ ''ይህ ሰው በእኛ ፖሊሲዎች ላይ እንከን ለማግኘት ሲል እንደ አንድ የፖለቲካ ተፎካካሪ ተመዝግቧል፤ ይህ ደግሞ መልዕክቶቹን በፌስቡክ ማስታወቂያ በኩል ሊያስተላልፍ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ሌላ ሦስተኛ ወገን እንዲያጣራው እናደርጋለን'' ብለዋል።
አድሪዬል ሃምፕተን ደግሞ የእኔ ጉዳይ ተለይቶ በሦስተኛ ወገን እንዲጣራ የሚያደርጉ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ፍር ቤት ለመውሰድ እያሰበ እንደሆነ አስታውቋል

በህንዷ ዴልሂ በአየር ብክለት ምክንያት 5 ሚሊየን ማስኮች እየተከፋፈሉ ነው

የአፍ መሸፈኛ ያደረጉ ተማሪዎችImage copyrightGETTY IMAGES
በህንዷ ዋና ከተማ ዴልሂ ባጋጠመ የአየር ብክለት ምክንያት ሃላፊዎች የማህበረሰብ ጤና ድገተኛ አደጋ አዋጅ ለማወጅ ተገደዋል። በተጨማሪም በከተማዋ ለሚገኙ 5 ሚሊየን ተማሪዎች አፍ መሸፈኛ ማስክ ሲያከፋፍሉ ውለዋል።
በዚህ ምክንያት እስከ መጪው ማክሰኞ ድረስ ትምህርት ቤቶች የተዘጉ ሲሆን በዴልሂ አየር ላይ የሚገኙት በካይ ንጥረ ነገሮች የዓለማቀፉ የጤና ድርጅት ካስቀመጠው ቁጥር በ 20 እጥፍ ይበልጣል ተብሏል።

በከተማዋ የሚካሄዱ ግንባታዎችም ቢሆን ሳምንቱን በሙሉ ሲስተጓጎሉ ነበር ተብሏል። ከመኪናዎች የሚወጣውን ብክለት ለመቀነስም በጣም የተመረጡና ልዩ ፈቃድ ያላቸው መኪናዎች ብቻ በጎዳናዎች ላእ እንዲሽከረከሩ የሚያስገድድ ጊዜያዊ ሕግም ተግባራዊ ተደርጓል።
የዴልሂ ዋና አስተዳዳሪ ሚኒስትር አርቪንድ ኬጅሪዋል እንዳሉት ከተማዋ ''ወደ ጋዝ ማከማቻ ተቀይራለች።''
ለተማሪዎችና ለቤተሰቦቻቸው የተከፋፈሉት 5 ሚሊየን አፍ መሸፈና ማስኮችንም ዜጎች በተቻለ መጠን ሁሌም እንዲጠቀሟቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የዓለማቀፉ የጤና ድርጅት ባስቀመጠው መለኪያ መሰረት ጎጂ ጥቃቅን አካላቱ በአንድ ቀን ውስጥ ከ 25 ማይክሮግራሞች መብለጥ የሌለበት ሰሆን በዴልሂ ኤር ውስጥ ግን 533 ማይክሮግራሞች የበለጠ ጎጂ ንጥረነገር ወደ ሳንባ ይገባል።
አንዳንድ የመንግስትና የግል ድርጅት ሰራተኞች ለጊዜው ስራቸውን በቤታቸው ሆነው እንዲያከናውኑ የተነገራቸው ሲሆን ዜጎች ከዓመት ዓመት በተመሳሳይ ችግር መጠቃታችን ተገቢ አይደለም፤ መንግስት የሆነ መፍትሄ ይፈልግ ሲሉ ምሬታቸውን በማህበራዊ ሚዲያዎች እየገለጹ ነው።
የአየር ብክለት በጤናችን ላይ ምን ያስከትላል?
እ.አ.አ. በ2017 የህንድና የስሪላንካ የክሪኬት ብሄራዊ ቡድኖች ጨዋታቸውን እያደረጉ በቦታው በነበረው ከፍተኛ ብክለት ምክንያት የስሪላንካ ተጫዋቾች ሜዳ ውስጥ ሲያስመልሱ እንደነበር ይታወሳል።
በዴልሂ እንደዚህ ላስቸገረው የአየር ብክለት ምክንያት ነው የሚባለው ከወርሃ ጥቅምት እስከ ታህሳስ ድረስ በጎረቤት ግዛቶች ፑንጃብ እና ሃርያና የሚገሡ ገበሬዎች ማሳቸውን ለአዲስ የግብርና ዓመት ለማዘጋጅ በጣም ሰፋፊ እርሻዎችን ስለሚያቃጥሉ ነው ተብሏል።

wanted officials