Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, February 27, 2018

የፖለቲካ እስረኛው ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ በእስር ቤት እንዳለ ሕይወቱ ማለፉ ተነገረ።


(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 19/2010)
የፖለቲካ እስረኛው ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ በእስር ቤት እንዳለ ሕይወቱ ማለፉ ተነገረ።
በሽብር ወንጀል ተከሶ የአራት አመት እስር ፍርደኛ የነበረው ገበየሁ ፈንታሁን እስርቤት ውስጥ በሕመም ምክንያት መሞቱ ታውቋል።
እስረኛው ገበየሁ ፈንታሁን ጨለማ ቤት ውስጥ ታስሮ እንደነበርና በቆይታውም ድብደባ ይፈጸምበት እንደነበር ከሐገር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ክሳቸው ተቋርጦ ሊፈቱ ነው የተባሉት የዋልድባ መነኮሳት ምስክር ሊሰማባቸው በፍርድ ቤት ቀነ ቀጠሮ መሰጠቱ ተሰምቷል።
ገበየሁ ፈንታሁን የአንድ ልጅ አባትና ባለትዳር ነበር።ከመታሰሩ በፊት ይተዳደር የነበረውም በሹፌርነት ነው።ከባህርዳር ከተማ ተይዞ በሽብር ወንጀል የተከሰሰው ገበየሁ ፈንታሁን ማዕከላዊ 8 ቁጥር በሚባል ጨለማ ቤት ታስሮ በነበረበት ጊዜ ድብደባና ሰቆቃ ተፈጽሞበት እንደነበር ይነገራል።
በተለይ በአንድ ወቅት ከደረጃ ገፍትረው እንደጣሉትና በዚህም ምክንያት የራስ ሕመም እንደነበረበት ነው የተገለጸው።አቶ ገበየሁ ፈንታሁን በታመመበት ወቅት በቂ ሕክምና እንዳላገኘም አብሮት ታስሮ የነበረው ጓደኛው ይፋ አድርጓል።
በመጨረሻም በእነ እስከዳር ይርጋ የክስ መዝገብ በሽብር ተከሶ የአራት አመት እስራት ተፈርዶበት ቆይቷል።በዚሁ የክስ መዝገብ 1ኛ ተከሳሽ እስከዳር ይርጋ ጥር 9/2010 ሲፈታ እርሱ ግን ወደ ኋላ እንዲቀር ተደርጓል።
ገበየሁ ፈንታሁን በቅርቡ ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ ግን የሞት ዜናው ነው የተሰማው።ተከሳሹ በቂ ሕክምና ሳያገኝ ከደከመ በኋላ ወደ ፖሊስ ሆስፒታል ቢወሰድም ትላንት የካቲት 18/2010 በዚሁ ሆስፒታል ሕይወቱ ማለፉን ከሃገር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም ክሳቸው ተቋርጦ ይፈታሉ ተብለው ሲጠበቁ የነበሩት የዋልድባ መነኮሳት በተከሰሱበት የሽብር ክስ ለመጋቢት 18/2010 ምስክር ይሰማባቸዋል ተብሏል።2ቱ ተከሳሽ መነኮሳት አባ ገ/ኢየሱስ ኪዳነማርያምና አባ ገ/ስላሴ ወ/ሃይማኖት ሲሆኑ እነዚሁም ክሳቸው ተቋርጦ ሊለቀቁ መሆኑን ቀደም ሲል በጠበቃቸው በኩል ተነግሮላቸው የነበሩ ናቸው።

Monday, February 26, 2018

Ethiopia federal forces detain recently released Oromo leaders


Reports from Ethiopia indicate that leading opposition chiefs, Merera Gudina and Bekele Gerba are among a group detained by federal security forces in the country’s west.
The recently released duo who are leaders of the main opposition Oromo Federalists Congress (OFC) were held near the town of Nekemt, OFC’s youth league secretary, Addisu Bulala told the Addis Standard portal.
“After addressing our supporters in other small cities on our way to Nekemt, when we reached Gute, few kilometers outside of Nekemt, we were stopped by federal security forces.
“We have been held for the last four hours and no one is explaining to us what would happen next,” he said in a phone interview.

Ethiopia’s Oromia region erupts as political prisoners return.

He further disclosed that the detained party includes other recently released prisonsers like Gurmesa Ayano, the youth league chair and Dejene Taffa, deputy secretary general who were released along with Bekele Gerba on February 13, 2018.
The country is currently under a state of emergency which the government imposed to curb spreading violence and insecurity. The measure among other things prohibits hampering activities of law enforcement bodies, and staging unauthorized demonstrations and meetings.
The country currently has a Prime Minister on his way out after tendering his resignation weeks back. Hailemariam Desalegn is occupying the post till the ruling coalition elects his successor latest by next week.
According to him, his resignation was to bolster political reform efforts announced in January 2018 which situation led to mass prisoner release at the federal and regional state levels


እንግሊዛዊቷ የኢትዮጵያ የአካባቢ ተፈጥሮ ተንከባካቢ ሱ ኤድዋርድስ


የአረንጓዴ ጀግናዋ ሱ ኤድዋርድስ




የተፈጥሮ ይዞታቸው ተበላሽቶ የነበረ የትግራይ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ በተከናወኑ ተግባራት፤ የአካባቢ ተፈጥሮ ክብካቤ ላይ የሚሠሩ የተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲቋቋሙ ባደረጉት አስተዋፅኦ ስማቸው ይነሳል። ለአርሶ አደሮች እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኘው የኅብረተሰብ ክፍል ባሳዩት ቀረቤታ ብዙዎች እናታችን ይሏቸዋል።



ለአካባቢ ተፈጥሮ ሲቆረቆሩ ለሀገራዊ ዕዉቀት ትኩረት ሲሰጡ ኖረዋል፤


ሱዛን በርኔል ኤድዋርድስ እንግሊዛዊቷ የአካባቢ ተፈጥሮ ተቆርቋሪ እና የሀገር በቀል እዉቀቶች አድናቂ የነበሩት ሱ ኤድዋርድስ ሙሉ መጠሪያ ነው። በቅርበት የሚያዉቋቸው እንደሚናገሩት ግን እሳቸው ትዳር መስርተው ወልደው ከብደው ከ40 ዓመታት በላይ በኖሩባት ኢትዮጵያ፤ ስማቸው ኢትዮጵያዊ ይዘት እንዲኖረው ስለሚሹ ሶስና ኤድዋርድስ መባልን ይመርጡ ነበር። እንግሊዛዊቷ ወይዘሮ ወደኢትዮጵያ በሄዱበት በ19 60ዎቹ መባቻ ገደማ አንስተው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በባዮሎጂ መምህርነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በዚህ አጋጣሚም እንደእሳቸው ሁሉ ለአካባቢ ተፈጥሮ ልዩ ትኩረት የሚሰጡ እና ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ባለቤታቸው ጋር መተዋወቃቸውን ለመረዳት ችለናል። በባዮሎጂ የትምህርት ክፍል በማስተማር ላይ ሳሉ በቀጣይ የሠሯቸውን የዘላቂ ልማት መካነ ጥናት የፕሮግራም ኃላፊ አቶ ግዛው ገብረ ማርያም መለስ ብለው እንዲህ ይዘረዝራሉ፤


«በባዮሎጂ ዲፓርትመን እያስተማሩ እያሉ በ1976ዓ,ም ወደ አስመራ ዩኒቨርሲቲ ከአዲሱ የትዳር አጋራቸው ጋር ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር ጋር በመሄድ አስመራ ዩኒቨርሲቲ ላይ የመጀመሪያው ሥራቸው የነበረው የማሪን ባዮሎጂ ዲፓርትመንትን ማቋቋም ነበር። ይሄም ተሳክቶላቸዋል። ከዚያ በመቀጠል በኢትዮጵያ ትልቁ ፈር ቀዳጅ የሆነው ሥራ የሠሩት የኢትዮጵያን የዕፅዋት ብዝሃ ሕይወት በመመዝገብ፣ በማጥናት እና አከታትሎም የዚያን የጥናት ዉጤት ዋና አርታኢ በመሆን ሠርተዋል።»

በ1983ዓ,ም ከተካሄደው የመንግሥት ለውጥ በኋላ ከባለቤታቸው ጋር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርነታቸው የተመለሱት ወ/ሮ ሱዛን ኤድዋርድስ፤ በ1989ዓ,ም ከመኖሪያ ቤታቸው አንዷን ክፍል ለቢሮነት በመጠቀም ዘላቂ ልማት መካነ ጥናትን ከባለቤታቸው ከዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር ጋር አቋቋሙ። እንደተረዳነው ይህ ድርጅት አሁን 21ኛ ዓመቱን አገባዷል። ዘላቂ ልማት መካነ ጥናትን ያቋቋሙበትን መነሻ የድርጅቱ የፕሮግራም ኃላፊ አቶ ግዛው ሲገልፁ፤
በጤፍ እርሻ ዉስጥ



«ዘላቂ ልማት መካነ ጥናትን ለማቋቋም ያነሳሳቸው አንዱም በተፈጥሮ የተቸራቸው የተፈጥሮ አፍቃሪ እና ለማኅበረሰብ ለውጥ እጅግ በጣም የተጉ ለአካባቢ ጥበቃ በጣም የተጉ፤ ሰው በመሆናቸው፤ በተለይ ኢትዮጵያ ከርሃብ እና ከኋላ ቀርነት እንድትላቀቅ የአካባቢ ጥበቃ ላይ የተንተራሰ ምርት እና ምርታማነት እንዲጨምር ትልቁ መሠራት ያለበት ብለው እሳቸው የሚያምኑት በአነስተኛ ደረጃ የሚያመርቱትን የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች አቅም ማጎልበት ነው። ከአርሶ አደሮች ጋራ በቅርበት መሥራትን መረጡ የአርሶ አደሩ እውቀት ከዘመናዊ እውቀት ጋራ ተቀናጅቶ ሀገራችን በዘላቂነት ከምግብ ልመና ራሷን ትችላለች የሚለው እምነት እንዲሰርጽ ነው እንግዲህ ሲታገሉ የነበረው ማለት ነው።»

ሃሳቡ መልካም ቢሆንም ሥራው ግን ቀላል እንዳልነበረ አቶ ግዛው ያስታውሳሉ።

«የተጀመረው ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የትግራይ ፕሮጀክት በሚል ነበር። ምክንያቱም የ17ቱን ዓመት የተካሄደውን በጣም ከፍተኛ በአካባቢ እና በሰው ሕይወት ላይ ከፍተኛ ውድመትን ያስከተለውን ጦርነት ተከትሎ፤ እንደሚታወቀው አካባቢው የተራቆተ፤ አፈሩ ለምነቱን ያጣ፣ ኅብረተሰቡ ምግብ ፍለጋ ከተራቆተው አካባቢ ለቆ ለመሄድ የሚገደድበት ወቅት ስለነበር የአካባቢዉም ማኅበረሰብን በተመረጡ አካባቢዎች በማወያየት አካባቢዉ በመጀመሪያ መልሶ እንዲያገግም የተሸረሸረው አፈር እንዲያገግም እና አርሶ አደሮች ማምረት እንዲችሉ የአርሶ አደሮቹም እውቀት እንዲካከት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ነው ሀ ብለው የእርሻውን ሥራ ከአርሶ አደሮቹ ጋር መደገፉ ላይ ያነጣጠረ ሥራ መሥራት የጀመሩት ማለት ነው። »

ይህ የትግራይ ፕሮጀክት ስነምህዳርን የጠበቀ የአስተራረስ ስልትን መሠረት ያደረገ እንደሆነ እና ይህም የአርሶ አደሩን ነባር እውቀት አካቶ አርሶ አደሩም አምኖበት ተቀብሎት ሥራ ላይ የዋለ እንደሆነም አቶ ግዛው ያስረዳሉ። ዓላማውም በዚሁ ተፈጥሯዊ ስልት ምርት እንዲጨምር እና የአካባቢ ጥበቃውንም ማበረታታት ነው። ይህ ስልት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይወሰን በአፍሪቃ ደረጃም እንዲስፋፋ መደረጉንም እንዲሁ።
እሳቸው በሚከተሉት የእርሻ ስልት የተመረተ የማሽላ ማሳን ሲመለከቱ፤



«ማኅበረሰቡ የራሱን የአካባቢ ሕግ አውጥቶ የወደመውን አካባቢ መልሶ እንዲያቋቁም መደገፍ አብሮ መሥራት የሚለውን ከክልሉ የግብርና እና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ቢሮ ጋር በመሆን ነው የተጀመረው እና ቀስ እያለ ይኼ ፕሮግራም በዚህ ሃያ ዓመት ጉዞ ውስጥ ከፍተኛ እውቅናን በማግኘቱ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ሌሎች የአፍሪቃ አገሮችም ተመሳሳይ ድርጅቶች የሚያከናዉኗቸው ይሄ የተፈጥሮ የእርሻ ዘዴን የማበረታታቱ ጉዳይ ተቀባይነት በማግኘቱ የኢትዮጵያዉን ምዕራፍ የሚመራው ዘላቂ ልማት በተለይም የወ/ሮ ሱ እና የዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር አስተዋፅኦ በጣም ከፍተኛውን ድርሻ የሚወስድ ስለሆነ ከሌሎች የአፍሪቃ አገሮች ጋራ ልምዱ ተቀናጅቶ በአፍሪቃ ደረጃ «ኤኮሎጂካል ኦርጋኒክ አግሪካልቸር አኒሺየቲቭ ፎር አፍሪካ» በአፍሪቃ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ቀርቦ እንደ አውሮጳዉያን አቆጣጠር በዲሴምበር 2011 ተቀባይነት እንዲኖረው ተደርጎ የጸደቀ ነው።»

ይህም የ20 ዓመታት የትግል ዉጤታቸው እንደሆነ ነው ለማስረዳት የሞከሩት። የክብር ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ትውልደ እንግሊዛዊቷ ወ/ሮ ሱዛን ኤድዋርድስ በኤኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች በኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት እንዲመጣ ሳይታክቱ የሠሩ የአካባቢ ጥበቃ አቀንቃኝ እንደነበሩ በቅርበት የሚያዉቋቸው ይናገሩላቸዋል። በሥራ አጋጣሚ ከሚያዉቋቸው አንዱ በተለይ የአካባቢ ተፈጥሮ ላይ አተኩሮ ይሠራ የነበረው ጋዜጠኛ አርጋዉ አሽኔ በግሉ ስለብዝሀ ሕይወት ምንነት በዝርዝር እንዲያዉቅ መንገድ ከከፈቱለት ምሁራን አንዷ ናቸው ይላቸዋል።
ሴት አርሶ አደሯን በማሳዋ ተገኝተው ሲያበረታቱ



«ቢያንስ ለ10 እና 11 ዓመታት በአካባቢ ጥበቃ ሥራ ውስጥ ያደርጉት የነበረውን አስተዋጽኦ በቅርብ መታዘብ ችያለሁ። እኔ ራሴም ከእሳቸው አንዳንድ ነገሮችን ለመማር ዕድል ያገኘሁበት ጊዜ ነበር። በተለይ ወደ አካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ዉስጥ በገባሁበት የመጀመሪያው ጊዜያት ላይ ይህንን የተለያይነት ወይም የባዮዳይቨርሲቲ ጉዳይ ፈፅሞ ብዙም የማላውቀው ርዕሰ ጉዳይ በነበረበት ጊዜ የመጀመሪያውን ስልጠና እንዲሁም ለሌሎች ሰዎች አይፈቀድም ነበር በጊዜው ለክልል እና ለፌደራል መንግሥት የተወሰኑ የተመረጡ ሠራተኞች የሚሰጥ ስልጠና ነበር እና ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ደብዳቤ ጽፈውልኝ ሄጄ በዚህ ስልጠና እንድካፈል እና ነገሩ እንዲገባኝ በማድረግ በመጀመሪያ በዚህ ነው የምንተዋወቀው።»

እሳቸው በተገኙባቸው በሀገር ዉስጥም ሆነ ከሀገር ዉጭ በተለያዩ ስብሰባዎች የመሳተፍ አጋጣሚው እንደነበረው የሚናገረው ጋዜጠኛ አርጋው ወይዘሮዋ ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል፤ በገጠርም ከአርሶ አደሮች ጋር ዝቅ ብለው እና ተቀራርበው መሥራት ይወዱ እንደነበረም አስታውሷል። በእነዚህ ሥራዎቻቸውም ጥሩ ዉጤት ተገኝቷል ባይ ነው።
በአንድ ትምህርት ቤት ተገኝተዉ ዛፍ ሲተክሉ



«ለምሳሌ የጤፍ ተለያይነትን ወይም የጤፍ ባዮዳይቨርሲቲ አይነቶችን ለመለየት እና ለማስተዋወቅ በተደረገው ጥረት ውስጥ በጣም ቁልፍ ሚና የነበራቸው ሴት ናቸው። በደብረዘይት ያለ የጤፍ ምርምር ተቋም ውስጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ይካፈሉ የነበሩ ሰው ናቸው። ከዚያ ዉጭ በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ አካባቢ አሁን የክልሉ መንግሥት እጅግ እንደ ትልቅ ስኬት አድርጎ የሚያነሳውን የተራቆተ አካባቢን መልሶ የማልማት ሥራ በተሠራበት ወቅትም ቀላል የማይባል አስተዋፅኦ አድርገዋል። ከዚህ በፊት በረሃማ የነበሩ ድንጋያማ የነበሩ እጽዋት በቅለውባቸው ዉኃ ምንጭ ፈልቆባቸው ለምለም አካባቢ እንዲሆኑ ሲደረግ በአጭር ጊዜዉ ዉስጥ በዓይናችን ያየንበትንም እንቅስቃሴ ዉስጥ ቀዳሚ ተሳታፊም ነበሩ። ይህንንም አውቃለሁ ከዚያ ዉጪ ወጣቶችን ወደአካባቢ ጥበቃ ሥራ እንዲገቡ ለማድረግ በጣም ብዙ ብዙ ጥረቶችንም አድርገዋል። ይህንንም አይቻለሁ።»

እንደጋዜጠኛ አርጋዉ ሁሉ በርካቶች የአካባቢ ተፈጥሮን በሚመለከት ከእሳቸው የማያልቅ ዕውቀት ለመቅሰም ችለዋል። ከእሳቸው ጋር የጀመሩትን የአካባቢ ተፈጥሮ ክብካቤ እንቅስቃሴ አሳድገው በየግል በዚሁ ተግባር ላይ የተሠማሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችንም ያቋቋሙም አሉ። ለአካባቢ ተፈጥሮ ጥበቃ በሙያው ረገድ ከሚያደርጉት አስተዋፅኦ እና ድጋፍ በተጨማሪ በግል አኗኗራቸውም ይህንኑ ያንፀባርቁ እንደነበርም አርጋው ያስታዉሳል፤

«አንደኛው ነገራቸው የሚበሉት የሚጠጡት የሚጠቀሙባቸው ቅሳቁሶች በሙሉ ከሚያምኑበት ከአካባቢ ጋር የተስማማ ወይም ከእንደዚህ አይነት ነገሮች ጋር የተስማማ እንዲሆን ነው ለምሳሌ ወደሥራ ሲመጡ ዕቃዎቻቸውን የሚይዙበት ቦርሳ፤ በየስብሰባዎቹ ላይ ለምሳሌ ብዙ ጊዜ እንደውም ከፍተኛ ተቃዉሞ ያቀርቡ የነበሩት በፕላስቲክ የታሸገ ውኃ መቅረቡ፤ ሌሎች ሌሎች ነገሮችም አያስደስቷቸውም ነበር አንዳንዶቹንም ነገሮች አይጠቀሙም ነበር። ምግብ ላይም እንደዚሁ ናቸው በጣም ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ተመርቶ የመጣ ምግብ ነው መመገብ ያለብን የሚል አቋም ነበራቸው። ይህንን አቋም በሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባርም ያሳዩ ነበረ።»
ወ/ሮ ሱ ከባለቤታቸው ጋር የአረንጓዴ ጀግና ሽልማት ሲቀበሉ



ይህንን የወይዘሮ ሶስና ኤድዋርድስን ለአካባቢ ተፈጥሮ የሚደረግ ልዩ ጥንቃቄ የሥራ ባልደረባቸው አቶ ግዛው ገብረ ማርያምም በሚገባ አስተውለውታል። የወይዘሮ ሶስና ሰብዕና ለሰዎች በመራራት ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ለፍጥረታት ሁሉ የተረፈ እንደሆነም ምሳሌ ጠቅሰው ያብራራሉ።

የዘላቂ ልማት መካነ ጥናት መሥራች እና ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉት ወይዘሮ ሱዛን ኤድዋርድስ የበርካታ ሽልማቶችም ባለቤት ለመሆን በቅተዋል። በዋናነት ከሚጠቀሱት መካከልም፤ በያዝነው ዓመት መስከረም ወር መቀመጫዉን እዚህ ጀርመን ሀገር ካደረገው ኢንተርናሽናል ፌደሬሽን ኦፍ ኦርጋኒክ አግሪካልቸራል ሙቭመንት፤ በተፈጥሮ ግብርና ላበረከቱት አስተዋጽኦ ከባለቤታቸው ጋር ዋን ዎርልድ የተሰኘ የሕይወት ዘመን ሽልማት አግኝተዋል፤ ለዘላቂ ልማት ላበረከቱት አስተዋፅኦም እንዲሁ በ2004ዓ,ም ከስዊድን ሀገር የጉተምበርግን ሽልማት ተቀብለዋል፤ በ1999ዓ,ም ደግሞ በኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ላበረከቱት የዓመቱ የአረንጓዴ ልማት ጀግና ተብለው ሽልማት ተቀብለዋል።

source – ሸዋዬ ለገሠ ኂሩት መለሰ

Google und die Bundesnetzagentur streiten

Google-Logo | Bildquelle: dpaProzess in MünsterStreit um Googles Gmail

Google und die Bundesnetzagentur streiten, ob Gmail ein Telekommunikationsdienst ist. Das Oberlandesgericht in Münster verwies den Fall nun an den Europäischen Gerichtshof.
Von Antraud Cordes-Strehle, WDR
Seit Jahren streiten Google und die Bundesnetzagentur darüber, ob Gmail ein Telekommunikationsdienst ist. Wenn ja, müsste Google zum Beispiel Nutzerdaten etwa bei Polizeiermittlungen weitergeben. Das Oberlandesgericht in Münster setzte heute das Verfahren dazu aus und verwies den Fall an den Europäischen Gerichtshof (EuGH).
"Im Rechtsstreit mit Google geht es um die Anwendbarkeit von deutschem Recht", erklärt Fiete Wulff, Pressesprecher der Bundesnetzagentur. Denn für sogenannte Telekommunikationsdienste gilt das Telekommunikationsgesetz. Und dieses gibt Richtlinien vor, wie etwa die Einhaltung des Fernmeldegeheimnisses und von Datenschutzbestimmungen, außerdem besondere Regeln zum Kundenschutz und zur Transparenz.

http://www.tagesschau.de/inland/bundesnetzagentur-google-101.html

ለሚገባችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋናዬ ከክብሮትና ፍቅር ጋር ይድረሳችሁ…. (አንዱዓለም አራጌ)


ለሚገባችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋናዬ ከክብሮትና ፍቅር ጋር ይድረሳችሁ…. (አንዱዓለም አራጌ)



“ከኢሕአዴግ ፈርጣማ መዳፍ የሚታደግ እንደሌላ እያወክ ድህረት ከየት አመጣኸው ?” እያሉ ብዙዎች ይጠይቃሉ። መልሱ ግን ቀላል ነው። የድፍረቴ ምንጭና ተስፋዬ ፣ በእስር ቤት ትቢያ ላይ ስጣል ለአፍታ እንኳን ያልተለየኝ ፣ በመከራ ሁሉ እግሮቼ እንዳይናወጡ ትልቁ ጽኑ አለት የሆነኝ እግዚአብሄር ነው። ለርሱ ክብር ምስጋና አምልኮ ይድረሰው።


የምወዳችሁ ልጆቼ ሩህና ኖላዊ፣ በሕጻንነት አይምሯችሁ ምህዋር ላይ ሲጉላሉ የነበሩ ጥያቄዎቻችሁን መመለስ ባለመቻሌ ፣ እኔን ለመጠየቅ በተመላለሳቹህባችሁ አመታት ለወደቃችሁ፣ ለተነሳችሁት፣ ለደማችሁት ፣ እንዲሁም በጣም በማስፈልጋችሁ ሰዓት ከሕይወታችሁ በግፍ በመጉደሌ በጣም አዝናለሁ።ይቅርታ ታደረጉልኝም ዘንድ እጠይቃለሁ። ምን አልባት አንድ ቀን ለምን ቤተሰባችን አሁን ባለፈበት ሁኔታ ማለፍ እንደተገደደ በዉል እንደምትረዱ፣ አሁን እንደ ቤተሰብ ካለፍንበት የአፈር ሰርጥ የምንጽናናበት ጊዜ እንደሚመጣ ተስፋ አደርጋለሁ። በዉል በማታወቁት አለም፣ ሰሙንና ገጽታዉን እንኳን በበዉል የማትለዩትን አባታችሁን ባልጠና እግራችሁ ተመላልሳችሁ ስለጠየቃችሁኝ፣ ሳልሰጣችሁ ስለሰጣችሁን በተትረፈረፈ ንጹህ ፍቅር በጣም አመሰግናቹሃለሁ።

አያሌዎች የኢትዮጵያ ሕዝብ የዲሞክራሲያው ስርዓት ባለቤት ይሆን ዘንድ በዋጋ የማይታመነውን ክብር ሕይወታቸውን እንኳን ሳይነፍጉ ሰጥተዋል። በኩራት በክብርና በሰላም የምትኖር ኢትዮጵያ ትፈጠር ዘንድ እኔም የበኩሌን ትንሿን አስተዋጾ ለማበርከት ባደረኩት ጥረትና በከፈልኩት ዋጋ በጣም ነው ደስታ የሚሰማኝ። እራሴን እንደተባረከ አድርጌ ነው የምቆጥረው።

“ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል” እንዲሉ ቀደም ሲል በ”ነውጠኛው ቅንጅት” ወደ ሁለት አመት ገዳማ፣ አሁን ደግሞ በ”አሸባሪነት” ስድስት አመት ተኩል በድምሩ ከስምንት አመት በላይ የሕወሃት ወግ ማእረግ የምናይባቸውን አፍላ አመታት በግፍና በዉሸት በተደረቱ የአገዛዙ የአፈና ተግባራቶች ተነጥቀናል። ከአጠገብሽ ባልነበሩካብቸው በነዚህ ሁሉ አመታት ፣ በጽናት ከጎኔ ስለቆምሽው፣ የኔንም ሚማ ጭምር በመወጣት ልጆቻችን በማሳደግ ለከፈልሽው ዋጋ፣ ላደረግሽልኝ ትልቅ ድጋፍ ሁሉ ባለቤተ ሰላም አስቻለ ልባዊ ምስጋናዬ ይድረስሽ።

በገጠር በከተማባ በዉጭ ሀገር የምትገኙ ቤተሰቦቼ በሙሉ በተለይም ፍሬሕይወት እንዳለ፣ ሚኪያስ እንዳለ፣ ዜና ደሳለኝና ዳግም ደሳለኝ ለፍቅራችሁና ለጥያቂያችሁ በጣም አመሰግናለሁ።

በድንገት ከአጠገባችሁ ተነጥዪ ብታሰርም በመንፈስ አብራችሁኝ ለታሰራችሁ እኔንም ለማስፈታትና የታሰርኩበት አላማ ዳር ለማድረስ ስላደረጋችሁት ተጋድሎ የፓርቲዬ የቀድሞ አንድነት ለዲሞክራሲ ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) አመራርቾንም አባላትን ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አብሬ ለመስራት በመቻሌ ደስ የሚለኝ በሰሜን አሜሪካ የቀድሞ አንድነት ፓርቲ የድጋፍ ሰጭ ኮሚቴዎች አባላት ሁሉ ላደረጋችሁት ትግልና ላደረጋችሁልኝ ድጋፍ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

ጠበቆቼ አቶ ደርበው ተመስገንና አቶ አበበ ጉታ ብዙዎች እንኳን ጥብቃን ሊቆሙልኝ ቀርቶ በሩቁ በሚሸሹን ሰዓት ፣ ሊደርስባችሁ የሚችለውን ሁሉ ሳትፈሩ የነጻ ያህል በሚቆጠር ክፍያ በከፍተኛ ፍርድ ቤት እስከ ሰበር ሰሚች ችሎት ድረስ አብራችሁን ስለተንከራተታችሁና ስላደረጋችሁት ጥረት እግዚአብሄር ዉለታችሁን ይክፈላችሁ።

በመላው አለም በተለይም በሰሜን አሜሪካ እስራኤልና አዉሮፓ የምትገኙ የኢትዮጵያ የዳያስፖራ አባላት በተለይም ትግሉ ለማገዝ ለአመታት ባለመታከት እየሰራችሁ ያላችሁ አክቲቪስቶች ፣ የአየር መለዋወጥና አስቸጋሪው የሕይወት ዉጣ ዉረድ፣ የአሁኑ ዘመን መርዝም ሳያዝላችሁ ከጎኔ ስለቆማችሁ እንዲሁም የታፈነውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጩኸት ከፍ አድርጋችሁ ለአለም በማሰማት ስለምታደረጉት አስተዋጾ የላቀ አክብሮትና ምስጋናዬን ላቀርብላችሁ እወዳለሁ።

በሀገርም በዉጭም የምትገኙ ጋዜጠኞች ፣ ብሎገሮች፣ ድረ-ገጾችና የመገናኛ ብዝሃን ተቋማት እዉነቱን ለሕዝብ ለማሳወቅ ስለሰራችሁ ስራ ሁሉ በጣም እያመሰገንኩ በተለይም ኢሳት ቴሌቭዥንና ዘሃበሻ ድህረ ገጽን እንዲሁም የዞን ዘጠኝ አባላትንና ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እጅግ አድርጌ አመሰግናለሁ።

በአገርም ውስጥ ሆነ በዉጭ ሃገር የምትግኙ በተቃዉሞው ጎራ የተሰለፋችሁ ሃይሎች ሁሉ ያሉን የፕሮግራምና የ ስትራተጂ ልዩነቲች ሳይገድበን የዲሞራሲና የመበት መገፈፍ ጉዳይ የሁላችንም በመሆኑ በአንዱ ላይ የሚደረሰው በሁላችንም ላይ እንደደረሰ ይቆጠራል ብላችሁ ላሰማችሁት የይፋታ ጥሪ በጣም አመሰግናለሁ።

የአለም አቀፍ ማህበረሰብ አባላት “ Injustice anywhere is a threat to justice everywhere” ብላችሁ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው አፈና እንዲቆም ስለምታደረጉት ጥረት እኔም እፈታ ዘንድ በራሳችሁ መንገድ ስላደረጋችሁት ጥረት አመሰግናለሁ።

በመጨረሻ ለዘመናት በተንሰራፋው የአገዛዙ ማነቆ ታንቆ የጭቆናንና የጭንቅን አመታትን እየገፉ የሚገኘው የኢትዮዮጵያ ሕዝብ፣ በዉል የሚገባው የግፍ ስቃይ በእኔና በቤተሰቤ ላይም ሲደርስ፣ ፍርድ ወደማያዛበው ፈጣሪ ችሎት አቤት በማለትና በልዩ ልዩ መንገዶች ድጋፉን በመግለጽ እንዲሁም ፍጹም የማይገባኝም ፍቅርና አክብሮት በመለገድ ለእነኤ ብቻ ሳይሆን ለቤተሰቦቺም ትልቅ ሞራልና ስንቅ ሆኗል። ለኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ ሁሉ፣ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እራሴን ዝቅ አድርጌ ከልቤ የሚቀዳዉን ምስጋናና ፍቅር አቀርባለሁ።

እኔና ጥቂት ኢትዮጵያዉያን ከክፉ እስር መፈታታችን ለብዙዎች በተለይም ለቅርብ ቤተሰብ አባሎቻችን እፎይታን ቢሰጥም እዉነታኛዉና ዘላቂው እፎይታ የሚመጣው ግን ኢትዮጵያ ከዘመን ጠገቡ የአገዛዝ ቀንበር ተፈታ፣ ዴሞክራሲያዊነት ሀገር መሆን ስትችል ብቻ ነው። አንድ ህዝብም ሆን ሀገር በትክክል ታላቅ ነው የሚባለው በሰራው ድልድይ ወይንም መንገድ ሳይሆን የሉዓልዊ ስልጣን ባለቤት ሲሆን ነው። ይህ እስኪሆን ድረስ እጅ ለእጅ ተያይዘን የጸና ሰላማዊ ትግል ከማድረግ ዉጭ የቀረን አማራጭ የለም።

በዚህ ሂደት ፍጹም ከእኛ ልናርቀው የሚገባው ነገር ካለ የመጀመሪያው ዘረኝነት ነው። ለእኔ ሰውን በዘሩ ምክንያት ከመጥላት ብሎም ከማጥቃት በላይ ኢሰባአዊነት የለም። በምንም አይነት መንገድ ወደዚህ ደረጃ እንዳንወርድ ልንጠነቀቅ ይገባል። ይልቅስ ቀንበሩ የተጫነው ሁላችንም ላይ ነዉና እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ልንታገል ይገባናል።

ነጻነት እንደ ቀትር ጸሃይ፣ ወንድማማችነት እንደ ጉንጉን አበባ፣ ፍትህ እንደ ሃይለኛ ጅረት በኢትዮጵያ ላይ ይንገስ።

አንዱዓለም አራጌ

“ጎንደር እረጭ እንዳለች ነው” ወጣቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው ተባለ፤








ጎንደር የተጠራው የስራ ማቆም አድማ ዛሬ ለሁለተኛ ቀን ተደርጓል። የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አልነበረም። ወሃ ገዝቶ ለመጠጣት እንኳን አልተቻለም። በከተማዋ የጋሪ አገልግሎት በተከለከለ ቦታ ሳይቀር ስራ ላይ ውሏል። ባለጋሪዎቹ ለስራ የወጡት ለፈረሶቻቸው ቀለብ መግዣ ስለሚያስፈልጋቸው እንደሆነ ተነግሯል።



በጎንደር ከተማ የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ ዛሬም ለሁለተኛ ቀን ቀጥሎ መዋሉን ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ አድማው ነገም እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ሰኞ ዕለት የስራ ማቆም አድማ የተካሄደባት ባህርዳር ከተማ ከትላንት አመሻሽ ጀምሮ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሳለች ተብሏል፡፡

ከአድማው ጋር በተያያዘ ወጣቶች ታስረዋል ተብሏል


በአማራ ክልል ከሰኞ ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ እንዲደረግ በማህበራዊ ድረገጾች መልዕክቶች መሰራጨታቸውን ተከትሎ በጎንደር ከተማ ትላንት የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ ዛሬም ለሁለተኛ ቀን መቀጠሉን የከተማይቱ ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ በከተማይቱ የአገልግሎት ሰጪዎች ዛሬም ተዘግተው መዋላቸውን፣ ትራንስፖርትም እንደሌለ ገልጸዋል፡፡

ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ የከተማይቱ ነዋሪ የንግድ ድርጅቶችም ሆነ ሌሎች አገልግሎት ሰጪዎች ተዘግተው መዋላቸውን ተናግረዋል፡፡ የህዝብ ማጓጓዣዎች በመንገድ እንደማይታዩ የገለጹት እኚሁ ነዋሪ ባሉበት አካባቢ ያስተዋሉትን እንዲህ ይገልጹታል፡፡

“አሁን መሀል ከተማ ፒያሳ እምብርቱ ላይ ነው ያለሁት፡፡ መስቀል አደባባዩ ላይ ማለት ነው፡፡ ባለሁበት ቦታ የስራ ማቆም አድማው እንደቀጠለ ነው፡፡ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የለም፡፡ ሰዎች ጥግ ይዘው ተቀምጠዋል፡፡ ከፖሊሶች ጋር ተፋጠዋል፡፡ ሊከፍት ፍቃደኛ የሆነ ምንም ዓይነት ድርጅት የለም፡፡ የትራንስፖርት ሰጪ ነገሮች የሉም፡፡ ጋሪዎች ናቸው የሚንቀሳቀሱት፡፡ ጋሪዎች ደግሞ ያው የዕለት ፍጆታቸውን፣ ለፈረሶቻቸው የሚሆን ምግብ ማግኘት ስላለባቸው፣ ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው ማለፍ በማይችሉባቸው አስፋልት መንገዶች ሁሉ እየተጓጓዙ ነው ያሉት” ይላሉ፡፡

ማንነታቸው እንዳይነገር የሚሹ ሌላኛው የጎንደር ነዋሪም ተመሳሳይ የትራንስፖርት ችግር በከተማይቱ አስተውለዋል፡፡ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ከትላንት ጀምሮ ከአገልግሎት መታቀባቸውን ይገልጻሉ። የዛሬው የስራ ማቆም አድማ በጎንደር ከተማ በሞላ መተግበሩን ሶስተኛው የከተማይቱ ነዋሪ ያስረዳሉ፡፡

ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች የስራ ማቆሙን አድማ ማን እንደጠራው በግልጽ እንደማይታወቅ ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ህብረተሰቡ እርስ በእርስ በመነጋገር መረጃውን እንደተቀባበለ ይስማማሉ፡፡ የስራ ማቆም አድማው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመቃወም የተጠራ ነው በሚል በማህበራዊ ድረ-ገጾች የተሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም ሲሉ የመጀመሪያው ነዋሪ ያስተባብላሉ፡፡ ከአድማው በስተጀርባ ያሉ ጥያቄዎችንም ያብራራሉ፡፡


በጎንደር ዛሬ አድማ ቢኖርም ከተማይቱ ምንም ችግር አለመፈጠሩን ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡ የመከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልል ፖሊስ አባላት በከተማይቱ በብዛት እንደሚታዩም ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ የከተማይቱ አስተዳደር ሰራተኞች ከትላንት ጀምሮ ስራ ባቋረጡ የንግድ ተቋማት እና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ላይ በቀይ ቀለም የኤክስ ምልክት ሲያደርጉ እንደተመለከቱም እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በመንግስት መስሪያ ቤቶችም ስራ ያልገቡ ሰራተኞችን ስም እየዞሩ የሚመዘገቡ ሰዎች ነበሩ ባይ ናቸው፡፡ ከአድማው ጋር በተያያዘ ትላንት እና ዛሬ ወጣቶች እንደታሰሩም ገልጸዋል፡፡ የጎንደር ነዋሪዎች የስራ ማቆም አድማው ነገም እንደሚቀጥል መስማታቸውን ይናገራሉ፡፡

በአድማው የመጀመሪያ ቀን ተሳትፋ የነበረችው የአማራ ክልል መቀመጫ ባህር ዳር ከትላንት ምማሻውን ጀምሮ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴዋ መመለሷን የከተማይቱ ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ቢሆን ግን በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ አቅራቢያ በርካታ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ተዘግተው እንደሚስተዋሉ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ጠቁሟል፡፡ ስማቸው እንዳይገለጽ የሚፈልጉ አንድ የከተማይቱ ስለ ባህር ዳር የትላንት እና ዛሬ ውሎ አብራርተዋል፡፡

የጎንደር የስራ ማቆም አድማን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ወደ ከተማይቱ የከንቲባ ጽህፈት ቤት ብንደውልም የሚመለከታቸው አካላት ቀኑን ሙሉ ስብሰባ ላይ መሆናቸው ተገልጾልናል፡፡ የአማራ ክልል የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁንንም በተመሳሳይ ምክንያት ልናገኛቸው አልቻልንም፡፡

ዝርዝር ዘገባውን የድምጽ ማዕቀፉን ተጭነው ያድምጡ፡፡


ተስፋለም ወልደየስ ሂሩት መለሰ

ቢቢሲ አማርኛ የሚከተለውን ዘግቧል

ብዙ ሁነቶችን ባስተናገደው ባለፈው ሳምንት ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞችና የመብት አቀንቃኞች በምህርትና በይቅርታ ተፈተዋል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው እንዲሁም ከፓርቲያቸው አመራር ኃላፊነት የመልቀቅ ጥያቄ ባቀረቡ ማግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ለብዙዎች አነጋጋሪ ሆኗል።

ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ በኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ ድንጋጌ በመንግሥታዊው ቴሌቪዥን በይፋ ከተገለፀበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ ስሜቶች እየተስተናገዱ ሲሆን፤ በአንዳንድ የአማራ ክልል ከተሞች በአፀፋው የሥራ ማቆም አድማ አድርገዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በታወጀ 72 ሰዓታት ጊዜ ውስጥ በጎንደር ከተማ የስራ ማቆም አድማ የተነሳ ሰሆን የንግድ ቤቶች ተዘግተዋል እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንደተቋረጠ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልፀዋል። የጎንደር ከተማ ፀጥ ረጭ እንዳለችም ጨምረው ተናግረዋል።

በተቃራኒው የተለያዩ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ክፍት እንደነበሩና አገልግሎትም ሲሰጡ እንደነበር ተነግሯል።

የኢፌዲሪ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት በፌስቡክ ገፁ ላይ እንዳሰፈረው ትናንት ምሽት የከተማው ከንቲባ አቶ ተቀባ ተባባል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በከተማው ውስጥ የስራ ማቆም አድማ በተለይም የንግድ ቤቶችን መዘጋትና ትራንስፖርት ማቆም እንዳለ አምነው ነገር ግን “ህገወጥ ስለሆነ ህዝቡ ሊቃወመው ይገባል” ብለዋል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው የጎንደር ነዋሪዎችም ግልፅ በሆነ ሁኔታ ማን አድማውን እንደጠራው አልታወቀም ብለዋል። የከተማው ከንቲባ በበኩላቸው “ባለቤቱ ያልታወቀ አድማ” ብለውታል።

“ህዝቡ በሰለጠነና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄዎቹን አሁንም በማቅረብ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተቀራርቦ መስራት አለበት” ቢሉም ከንቲባው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሀገሪቱ ላይ የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ ካልተነሳ በአድማው እንደሚቀጥሉ እየገለፁ ነው ።

ትናንት አመሻሹ ላይ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ከእስር የመፈታታቸውንም ዜና ተከትሎ በጎንደር ከተማ ደስታቸውን ለመግለፅ ብዙዎች እንደወጡ ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በባህርዳር ከተማም ትናንት ጥዋት አካባቢ ላይ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የስራ ማቆም አድማ እንደነበርና የንግድ ቤቶችም መዘጋታቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል እንዲሁም በደብረ-ታቦር ከተማ መጠነኛ የሚባል የሥራ ማቆም አድማ እንደነበር መረዳት ተችሏል።

ሁለተኛ ቀኑን በያዘው በዚሁ የስራ ማቆም አድማ በጎንደር እንደቀጠለ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልፀዋል። የንግድ ቤቶች እንደተዘጉ ሲሆን የትራንስፖርት አገልግሎትም ዛሬም እንደሌለ እየተናገሩ ነው። ትናንት ክፍት የነበሩ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በዛሬው ዕለት አንዳንዶቹም ዝግ እንደሆኑ ነዋሪዎቹ ጨምረው ገልፀዋል።


*ስለ ሶርያ እንማልዳለን***መ/ር ታሪኩ አበራ



**ስለ ሶርያ እንማልዳለን***

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እባክህን ለሙስሊሙም ለክርስቲያኑም የምሕረት እጅህን ዘርጋላቸው።

የነበርህ ፣ያለህና የምትኖር የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሆይ በሰላም ውለን እንድናድር፣ በሰላምም ወጥተን እንድንገባ ስለ ረዳኽን ክብርና ምሥጋና ለታላቅ ስምህ ይሁን።


ቅዱስ አባት ሆይ ምንም እንኳ የእኛም ሀገር በችግርና በመከራ ውስጥ ብትሆንም ከእኛ በባሰ ሁኔታ በሶርያ ምድር ላይ የአዳም ዘር እንደ ቅጠል እየረገፈ ደማቸውም ከምድር አፈር ጋር እየተቀላቀለ ነውና ጌታ ሆይ ቀኝህን ዘርጋላቸው።እረፍትና ሰላምንም አንተ አብዛላቸው።በሶርያ ምድር ላይ የሰው ደም ጠምቶት ከጥልቁ የወጣው የአጋንንት ሠራዊት ሁሉ በመለኮታዊ እሳት ተቃጥሎ ወደ ሲዖል ይወርወር።

ጌታ ሆይ በፈሰሰው ደምህ፣በአማኑኤል ስምህ እንማጸናለን የንጹሐን ሕጻናትን እልቂት በታላቅ ክንድህ አቁመው፣እሮጠው ያልጠገቡ እግሮች በከባድ መሳሪያ እየተቆረጡ ነው፣ አባ እማ ብለው የሚኮለተፋ አንደበቶች በረጋ ደም እየተቆለፋ ነው፣አንዳችም ነውርና ኃጢአት የሌለባቸው ጨቅላ ህጻናት በግፍ ደማቸው እንደ ጅረት እየፈሰሰ በሞት እየተነጠቁ ነው ፣ወላጆች ልጆቻቸውን በመሪር ሞት እየተነጠቁ የወላድ መኻን ሆነዋል፤ ልጆችም የወላጆቻቸውን አስከሬን እያዩ በምድረ በዳ እንደ ሚቅበዘበዝ ግልገል ሆነዋል። ጌታ ሆይ የሶርያ ምድር አኬልዳማ ሆናለችና በምህረት ዓይንህ ተመልከታቸው የሀገራቸውን እንቆቅልሽ በመለኮታዊ ጥበብህ አንተው ፍታላቸው።

መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ ሆይ ምንም እንኳ ዛሬ ላይ ኢጥሙቃን ቢበዙባትም ሶርያ የታላቁ አባት የቅዱስ ኤፍሬም ሀገር ናት።የአንተ አዳኝነት የእናትህ ክብርና ምሥጋና የተነገረባት የክርስቲያኖች ምድርናት ዛሬም ስለ ስምህና ስለ ክርስትናቸው ዋጋ የሚከፍሉ አማኞች ያሉባት ምድርናትና እባክህ ጌታ ሆይ በእነርሱ ላይ የተነሳውን የጦርነት እሳት በቅዱስ መንፈስህ አብርድላቸው።
እምባቸውንም አብስላቸው።ዳግም እግዚአብሔር ታላቅ ነው ብለው ስለ አዳኝነትህ የሚዘምሩበትን የንስሐ እድሜ ስጣቸው።

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሆይ በፊትህ ዝቅ ብለን እንማፀንሃለን በሶርያም በኢትዮጵያም ላይ አንተ ከፍ ብለህ ታይ ፍጥረት ሁሉ እግዚአብሔር ረዳን ብሎ አንተን ያክብር ።ጦርነቱን በሰላም ቀይረህ ወጀብ ማእበሉን በታላቅ ክንድህ ገስፀህ ለሕዝብህ እረፍትና መረጋጋትን አምጣ።የሆነው ችግርና መከራ ሁሉ አንተን መፍራትና አንተን ማምለክን አስተምሮን ይለፍ እንጂ ከአንተ የሚለየን እልኽኞችና ከሀዲዎች አያድርገን።ጌታ ሆይ በኢትዮጵያም በሶርያም ምድር እኛ የማናውቀው አንተ የምታውቀው በድብቅ የተሰራ ኃጢአትና ግፍ ይኖራል ነገር ግን ጌታ ሆይ በቃ በለን በቀራንዮ ስለ ፈሰሰው ደም ብለህ ይቅርበለን ።በዝሙት፣በግብረ ሰዶም፣ጽንስ በማስወረድ፣በጣዖት አምልኮ፣በጥንቆላ፣በዘረኝነትና በአድመኝነት አንተን የበደልንበትን ያለፈውን ዘመን ይቅርበለን።

በእግዚአብሔር ፊት የጽድቅን ታጋድሎ በድል አጠናቃችሁ የጽድቅን አክሊል ያገኛችሁ ቅዱሳን ሁላችሁ የሶርያ ምድር እንድትፈወሰ ኢትዮጵያም እንድትባረክ ምልጃችሁ ይርዳን።

ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ሆይ የባለሟልሽ የቅዱስ ኤፍሬም ሀገር ሰላምና ምሕረት ከልጅች እንደ ሰማይ ጠል እንዲወርድላት ምልጃሽ አይለያት።አሜን።

እባካችሁ ሁላችን በጸሎት እናግዛቸው ዘንድ ይህንን ጸሎት ለሰው ሁሉ ሼር አድርጉት::

መ/ር ታሪኩ አበራ

እባካችሁ ኮሜንት መስጫ ላይ የአሻንጉሊት ምስል አትለጣጥፋ አንዲት የጸሎት ቃል ብቻ ከልባችሁ ወደ እግዚአብሔር ጸልዩላቸው።
Image may contain: 2 people, people standing, beard and outdoorImage may contain: 2 people, people sitting

የዋልድባ መነኮሳት ክስ አሁንም እንደቀጠለ ነው

ጠበቃ አማሃ መኮንን የሕግ መርህ ተጥሷል እያሉ ነው ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬው እለት የካቲት 19 ቀን 2010 ዓ.ም በዋለው ችሎት፤ በእነ ተሻገር ወ/ሚካኤል ላቀው የክስ መዝገብ ስር የተከሰሱት የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባ ገ/እየሱስ ኪ/ማርያም ካሴ እና አባ ገ/ስላሴ ወ/ሀይማኖት። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረውን የሽብርተኝነት ክስ አሁንም እንደቀጠለ ነው ። መነኮሳቱ የሃይማኖት ልብሳቸውን እንዲያወልቁ መገደዳቸውና መደብደባቸውን አስመልክቶ ለሚደርስባቸው ኢሰብዓዊ ድርጊት ቀደም ብሎ ለችሎቱ በጽሁፍ ያቀረቡትን አቤቱታ አስመልክቶ ፣ ፍርድ ቤቱ በጽሁፍ ለቀረበለት አቤቱታ የሚመለከተው የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ምላሽ እንዲሰጥ ለየካቲት 30/ 2010 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን፤ በመነኮሳቱ ላይ ለቀረበው ክስ የዐቃቤ ሕግ ሦስት የሰው ምስክሮች ለመስማት ለመጋቢት 18 ቀን 2010 ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በእነ ተሻገር ወ/ሚካኤል ላቀው የክስ መዝገብ 38 ተከሳሾች የተከሰሱ ሲሆን የ35ቱ ክሱ ሲቋረጥ፤ መነኮሳቱን ጨምሮ የአንድ ሰው ክስ እንደቀጠለ ነው። ይህን በተመለከተ የዋልድባ መነኮሳት ጠበቃ የሆኑት አማሃ መኮንን በደንቦኞቼ ላይ የህገ መንግስቱ ዋንኛ መርህ የሆነው ” ሰዎች ሁሉ በሕግ ፊት እኩል ናቸው” የሚለውን በይፋ በሚጣረስ መልኩ ፤ የዋልድባ መነኮሳት ላይ የሕግ አድሏዊነት እየተፈጸመባቸው ነው። ያሉ ሲሆን፣ አያይዘውም ” በተመሳሳይ መዝገብ፣ በተመሳሳይ ክስ የሚገኙትን እየለዩ አንዱን መፍታት ሌላውን ማሰር የትኛውም አይነት የሕግ ድጋፍ የለውም ” ብለዋል ።

የዋልድባ መነኮሳት ለባለፈው አንድ አመት ከአንድ ወር በእስር ላይ ይገኛሉ። መነኮሳቱ “መንግሥት” የዋልድባ ገዳም ይዞታ በሆነው አካባቢ የስኳር ፋብሪካ ለማቋቋም ማቀዱ እና ዕቅዱ በገዳሙ መነኮሳት ተቃውሞ የገጠመው ሲሆን ከ 2004 ዓ.ም ጀምሮ መነኮሳቱ ለእስር እስከተዳረጉበት ድረስ አቤቱታቸውን ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በተደጋጋሚ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።

(ይድነቃቸው ከበደ )

የስዊድኑ የልብስ አምራች H&M አዲስ ቅሌት በሀዋሳ H& M Scandal in Ethiopia

“ሶስት ሺህ ብር እንድሚከፈለን በደላሎቻቸው አማካኝነት ሲነግሩን አሰተማሪዎች ሳይቀሩ ሰራቸውን ጥለው በፋብሪካ ውስጥ ተቀጥረው ነበር፣ ነገር ግን የእውነተኛ ክፍያው በወር አንድ ሺህ 50 ብር ብቻ ነው።” ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ባንግላዴሽ በነበረው ፋበሪካው ውስጥ በደረሰ የመደርመስ አደጋ አንድ ሺህ 1 መቶ ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የሰራ ላይ የደህንነት ማረጋገጫዎችን ሰለማይተገብር ወቀሳ ደርሶበት ነበር። በተመሳሳይ በኢትዮጲያ ባለው ፋበሪካው መሰረታዊ የደህንነት ማረጋገጫዎችን አላሟላም በሏል የሲውዲኑ ባንክ።
ዋዜማ ራዲዮ– የሲውዲንን መንግስትን ከፊል የእርዳታ ገንዘብ ተቀብሎ ኢትዮጲያ ውስጥ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ከፍቶ ስራ የጀመረው ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ኢትዮጲያ ለሚገኙ ሰራተኞቹ የክፍያ መሰፈርትን ሳያሟላ፣ አጀግ በጣም ዝቅተኛ ከሚባለው በታች እየከፈለ፣ አለማቀፍ የሆነውን የሰራተኞች ዝቅተኛ ክፍያ ባላሟሟላቱ ድርጅቱ ላይ ገንዘብ ያፈሰሰው የሲውዲኑ ኖርዲያ ባንክ ለኤች ኤንድ ኤም (H&M) የሰጠውን ገንዘብ አገተበት።
በሐዋሳ ኢንዱሰትሪ ፓርክ ከከትሙ በርካታ አለም አቀፍ ዝና ያላቸው የንግድ ተቋም መካከል የሆነው ኤች ኤንድ ኤም (H&M) በሐዋሳ ሰራ ከጀመረ ከሁለት አመታት በላይ አሰቆጥሯል፡፡ እንደ ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ከሆነ አራት ሺህ ሰራተኞችን ቀጥሮ በአሁኑ ሰዓት እያሰራ ይገኛል፡፡
የሲውዲን የህዝብ ቴሌቨዥን ድርጅት ኤስ ቪ ቲ (SVT) ኤች ኤንድ ኤም (H&M) በኢትዮጲያ ውስጥ በሚገኛው የሐዋሳ ፋብሪካው ለሰራተኞች ዝቅተኛ ከሚባለው የዓለም አቀፍ ደረጃ ወርዶ በጣም ዝቅ ያለ ክፍያ እየከፈለ ይገኛል በሎ መዘገቡን ተከትሎ የሲውዲኑ ኖርዲያ ባንክ ለኤች ኤንድ ኤም (H&M)ክፍያውን አግዶበታል፡፡
በሰዓት ሲሰላ አራት ብር ከአርባ ሳንቲም በሐዋሳ በሚገኘው ፋብሪካው ለኢትዮጲያውያኑ ሰራተኞቹ የሚከፍለው የኽው ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ድርጅት አገሪቷ ለሰራተኞቿ ከምትከፍለው ያነሰ ክፍያ አልከፈልኩም ብሎ ተከራክሯል፡፡
“እየተጠቀሙብኝ ነው። ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሰው ሃገር እንደሚሰሩ አይነት ሰዎች እንደሆንኩ ይስማኛል፡፡ ግን ይህ ሃገሬ ነው።” ስትል ለኤስ ቪ ቲ (SVT) ቴሌቭዥን ጣቢያ አሰተያየቷን ሰጥታለች አሁን በሐዋሳ ኢንዱሰትሪ ፋብሪካ ተቀጥራ በመሰራት ላይ ያለችው የባህርሰው ጥበቡ።
እንደ ኤች ኤንድ ኤም (H&M) እና ዘሃራ የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ስም እና ዝና ያላቸው ፋብሪካዎችን ወደ ሃገርቤት ለመሳብ የኢትዮጲያ መንግስት ርካሽ የሰው ጉልበት ሰለመኖሩ ቀስቅሶ የተለያዩ ኩባንያዎችን የሳበ ሲሆን፣ ጉትጎታው ሲተገበር ግን ኢትዮጲያ ለሰራተኞቿ የሰዓት ቁርጥ ክፍያ ያላመቻቸች ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በዓለም ዝቅተኛ ክፍያ ለህዘቦቿ እንዲከፈል የምትፈቅድ ሆናለች። በዚህም ድርጊታቸው ዓለም አቀፍ ውግዘትን እንዳያሰከትልባቸው ሰጋት የገባቸው በርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ከሃላፊነት ለመሸሽ እንዲያመቻቸው ደርጅታቸውን ከቻይና ባለሐብቶች ጋር በማያያዝ ሰማቸውን ቀይረው በሐዋሳ ከትመዋል።
ሰራተኞች ከወርሃዊ ዝቅተኛ ክፍያ በተጨማሪ ድንገት ህመም ቢያጋጥማቸው አንድ ቀን ለቀሩበት ከወር ደሞዛቸው 20 በመቶ ይቆርጥባቸዋል ሲል ይኸው ኤስ ቪ ቲ (SVT) ቴሌቭዥን ዘግቧል።
ኤች ኤንድ ኤም (H&M) እንዴት አድርጎ ከሲውዲን መንግስት የተቀበለውን ገንዘብ እየተጠቀመበት እንደሆነ ለማጤን እና የሰነ ምግባር መሰረታዊ መሰፈርቶችን ማሟላታቸውን በትኩረት የሚያረጋግጠው ኖርዲያ ባንክ በተለይ ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ኢትዮጲያ ባለው ፋብሪካው ለአካባቢ ተሰማሚነቱን፣ የውሃ አጠቃቀሙን፣የሰራተኞቹን ከፍያ እንዲሁም ደህንንት እና ከሰራ ሁኔታዎች ጋር የተያያዙ ችግሮቹን አስኪፈታ ገንዘቡን አግቶበታል።
ከሰራ ቀጣይነት፣ ቋሚነት ጋር በተያያዘ መሰረታዊ ችግር እንዳለበት የሚነገርለት ይኸው የልብስ ፋብሪካ ኤች ኤንድ ኤም (H&M) በኢትዮጲያ ለሰራተኞቹ የሚከፍልው ክፍያ “ለመኖር የሚያሰችሉ” ከሚባሉ የሰራ ክፍያዎች ውስጥ የማይመደብ ነው።
“ችግሩ መንግስት ምን ያህል ስራ እንደምንፈልግ ያውቃል። ከቀጣሪያችን ጋር በመሆን ምን ያህል ለእኛ መከፈል እንዳለበት ስምምነት አደርጓል” ትላለች የባህርሰው።
“ሶስት ሺህ ብር እንድሚከፈለን በደላሎቻቸው አማካኝነት ሲነግሩን አሰተማሪዎች ሳይቀሩ ሰራቸውን ጥለው በፋብሪካ ውስጥ ተቀጥረው ነበር፣ ነገር ግን የእውነተኛ ክፍያው በወር አንድ ሺህ 50 ብር ብቻ ነው።”
ኤች ኤንድ ኤም (H&M) ባንግላዴሽ በነበረው ፋበሪካው ውስጥ በደረሰ የመደርመስ አደጋ አንድ ሺህ 1 መቶ ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የሰራ ላይ የደህንነት ማረጋገጫዎችን ሰለማይተገብር ወቀሳ ደርሶበት ነበር። በተመሳሳይ በኢትዮጲያ ባለው ፋበሪካው መሰረታዊ የደህንነት ማረጋገጫዎችን አላሟላም በሏል የሲውዲኑ ባንክ።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሐገሮችን የኢንቨስትመንት ምቹነት የሚያጠናው ሲልክ ኢንቨስት የተባለ ድርጀት በኢትዮጲያ በአሁኑ ሰዓት ከህንድ፣ ከሱዳን፣ ከጀርመን፣ ከጣሊያን፣ ከቱርክ፣ ከሳውዲዓረቡያ፣ ከየመን፣ ከእንግሊዝ፣ ከእስራኤል፣ ከካናዳ የመጡ አዳዲስ ፋበሪካዎችን በሃገሪቷ አቋቁመዋል። [ዝርዝር የድምፅ ዘገባ ከታች ተያይዟል]

የዋልድባ መነኮሳት ምስክር ሊሰማባቸው ነው፤ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የፖለቲካ እስረኛ በእስር ቤት ህይወቱ አለፈ

በእነ ተሻገር ወ/ሚካኤል ክስ መዝገብ የ”ሽብር” ክስ የተመሰረተባቸው የዋልድባ መነኮሳት ለመጋቢት 18/2010 ዓም ምስክር ይሰማባቸዋል ተብሏል። ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የፖለቲካ እስረኛ በእስር ቤት ህይወቱ አለፈ።
በእነ ተሻገር ወ/ሚካኤል ክስ መዝገብ ተከሰው ከነበሩት 35 ተከሳሾች መካከል 32ቱ ክሳቸው ተቋርጦ የተፈቱ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ ነጋ ዘላለም መንግስቴ፣ 4ኛ ተከሳሽ አባ ገ/ እየሱስ ኪ/ማርያም እና 5ኛ ተከሳሽ አባ ገ/ስላሴ ወ/ሐይማኖት ብቻ ክሳቸው ቀጥሏል።
የዛሬው የካቲት 19/2010 ዓም ቀጠሮ ተይዞ የነበረው በመዝገቡ ከተጠቆጠሩት ምስክሮች መካከል ጉዳያቸው ይቀጥላል በተባሉት 3ቱ ተከሳሾች ላይ የሚቀርቡትን አቃቤ ህግ ለይቶ እንዲያስመዘግብ እና መነኮሳቱ ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ነበር። በዚህም መሰረት 1ኛ፣ 2ኛ እና 4ኛ ምስክሮች በመነኮሳቱ እና በ2ኛ ተከሳሽ አቶ ነጋ ዘላለም ላይ ይመሰክራሉ ተብሏል። የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማትም ለመጋቢት 18 ቀጠሮ ተይዟል።
በሌላ በኩል የቂሊንጦ እስር ቤት መነኮሳቱ የምንኩስና ልብሳቸውን እንዲያወልቁ እንያገደዳቸው መሆኑን ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን እስር ቤቱ ለካቲት 30 መልስ እንዲሰጥ ታዟል።
4ኛ ተከሳሽ አባ ገ/እየሱስ ኪ/ማርያም እና 5ኛ ተከሳሽ አባ ገ/ስላሴ ወ/ሐይማኖት ልብሳቸውን አናወልቅም በማለታቸው ባለፉት ቀጠሮዎች ያልቀረቡ ሲሆን በአቤቱታቸው ላይ ቅጣት ቤት እንደሚገኙ መግለፃቸው ይታወሳል። የሁለቱም መነኮሳት አካል ላይ ባለፉት ጊዜያት ያልነበረ ጉስቁልና ይስተዋላል።
አሳዛኝ ዜና
ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የፖለቲካ እስረኛ በእስር ቤት ህይወቱ አለፈ
በእነ እስከዳር ይርጋ ክስ መዝገብ በ”በሽብር” ክስ አራት አመት ተፈርዶበት ይፈታል ተብሎ እየተጠበቀ የነበረው 2ኛ ተከሳሽ ገበየሁ ፈንታሁን በእስር ቤት ባጋጠመው የጤና እክል ህይወቱ አልፏል። ተከሳሹ በቂ ሕክምና ባለማግኘቱ ከደከመ በኋላ ወደ ፖሊስ ሆስፒታል ተወስዶ ትናንት የካቲት 18/2010 በፖሊስ ሆስፒታል ህይወቱ አልፏል።
ገበየሁ ፈንታሁን ማዕከላዊ 8 ቁጥር በሚባል ጨለማ ቤት ታስሮ እንደነበርና በቆይታው ድብደባ እንደደረሰበት በወቅቱ አብሮ ታስሮ የነበረው ጓደኛው ገልፆአል። በተለይ በአንድ ወቅት ከደረጃ ገፍትረው እንደጣሉትና በዚህም ምክንያት የራስ ህመም እንደነበረበት ተገልፆአል። አቶ ገበየሁ ፋንታሁን በታመመበት ወቅት በቂ ህክምና እንዳላገኘ ጓደኛው ገልፆአል።
አቶ ገበየሁ ፋንታሁን የአንድ ልጅ አባት እና ባለትደር እንደነበርና ከባህርዳር ተይዞ እስከታሰረበት ጊዜ ድረስ በሾፌርነት ተቀጥሮ ቤተሰቦቹን ያስተደድር እንደነበር ተገልፆአል። በክስ መዝገብ 2ኛ ተከሳሽ የነበረው አቶ ገበየሁ ፋንታሁን አራት አመት ተፈርዶበት የነበር ሲሆን 1ኛ ተከሳሽ እስከዳር ይርጋ ጥር 9/2010 ዓም ተፈትቷል። አቶ ገበየሁ ፋንታሁን ይፈታል ተብሎ እየተጠበቀ እንደነበር ታውቋል።

የአሜሪካ ኤምባሲ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አወጣ።US warn travellers to Ethiopia


የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ተመሳሳይ መግለጫ ማውጣቱ ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ በኢትዮጵያ ለአሜሪካ አምባሳደር ማብራሪያ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው የቅድመ ማስጠንቀቂያ መግለጫ ሰራተኞቹ ከአዲስ አበባ ውጪ በምንም አይነት መንቀሳቀስ አደገኛ ሁኔታን ሊያስከትል ይችላል ብሏል።
እናም በሀገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የሚሰጡትን መረጃ በመከታተል ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋልም ነው ያለው። በኤምባሲው መግለጫ መሰረት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ሰልፎችና ሕዝባዊ አመጾች ድንገት ሊቀሰቀሱ ይችላሉ። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ ቀውስ ሊባባስ እንደሚችል ነው ያስጠነቀቀው።
በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣውን የቅድመ ማስጠንቀቂያ መግለጫ መነሻ በማድረግም የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ተመሳሳይ ማሳሰቢያ መስጠቱ ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአዲስ አበባ ከአሜሪካው አምባሳደር ማይክል ሬይነር ጋር በሀገሪቱ ባለው አሳሳቢ ሁኔታ ላይ መምከራቸው ተነግሯል።
አቶ ደመቀ አምባሳደሩን በጽሕፈት ቤታቸው ለማናገር የተገደዱት አሜሪካ የኢትዮጵያ ጉዳይ በእጅጉ ያሳሰባት በመሆኑ ነው ተብሏል። በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በኩል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለመደንገግ ስብሰባ ላይ መሆኑ ይነገራል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለ3 ወራት ወይም ለ6 ወራት ሊደነገግ እንደሚችል ዘገባዎች አመልክተዋል።

Chinese investment hotspot and a state of emergency: What’s going on in Ethiopia



Justina Crabtree | @jlacrabtree  CNBC
Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn resigned last week following anti-government protests. A state of emergency has since been imposed on the country.
Ethiopia is one of the world’s fastest-growing economies, having achieved double-digit gross domestic product growth in recent years.
China provides much of Ethiopia’s foreign direct investment, and the east African country is a linchpin of China’s Belt and Road infrastructure scheme.
Security measures are taken as the Oromo people protest against government during the Irreecha holiday in Addis Ababa, Ethiopia, on October 2, 2016.
Ethiopia is one of the world’s fastest growing economies and a hub for Chinese investment, having rejuvenated its fortunes after a turbulent history marred by civil war and famine.
But, the East African nation’s political story is murkier. Given the surprise resignation of its prime minister and the declaration of a state of emergency last week following protests, CNBC takes a closer look at this major frontier market.

Set up for political failure

Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn resigned on February 15 following mass protests. A six-month long state of emergency was imposed by the government the next day, with the intention of quelling civil unrest.
 
The state of emergency prohibits, among other things, the distribution of potentially sensitive material and unauthorized demonstrations or meetings.
Hailemariam remains in office until a new prime minister is appointed.
Ethiopia is, in essence, a one party state led by the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, a coalition comprising of parties representing different regions of the country.
Tension has been bristling between the powerful Tigray People’s Liberation front, which represents just 6 percent of Ethiopians, and its counterparts representing the Amhara and Oromo ethnic groups. Meanwhile, Hailemariam’s party, the Southern Ethiopian People’s Democratic Movement, is the weakest in the coalition.

People protest against the Ethiopian government during Irreecha, the annual Oromo festival which celebrates the end of the rainy season, in Bishoftu on October 1, 2017.
Zacharias Abubuker | AFP | Getty Images
People protest against the Ethiopian government during Irreecha, the annual Oromo festival which celebrates the end of the rainy season, in Bishoftu on October 1, 2017.
Hailemariam, who took power after the death of his predecessor Meles Zenawi in 2012, has failed to unite his party. The former leader headed up a centralized government and wielded prestige from the country’s civil war to ensure loyalty.
Anti-government protests have bubbled up, most recently in 2016 when the country’s last state of emergency was imposed.
“It is unlikely (Hailemariam’s) successor will adopt a more reformist stance,” Emma Gordon, senior East Africa politics analyst at consultancy Verisk Maplecroft, told CNBC via email. “Protests and political uncertainty will therefore continue.”

Sky-rocketing economic growth

The potential for new leadership in Ethiopia is little more than a band aid.
“The factors that have driven the protests — namely the ethnic federal system, the influence of the military and intelligence services, and the interplay between the political elites and the business sector — will remain in place,” Gordon said.
Ethiopia, one of the least developed economies in the world, has achieved double-digit growth in recent years. Should its incoming prime minister placate ethnic tensions along party lines — leading to the lifting of the state of emergency within six months — this could continue.
“Assuming (a) more benign political outcome, we expect economic growth to remain healthy, albeit below the 11 percent annual expansion targeted by the government’s Growth and Transformation Plan,” Jane Morley, regional manager for the Middle East and Africa at the Economist Intelligence Unit, told CNBC via email.

Chinese Premier Li Keqiang (R) and Ethiopia's Prime Minister Hailemariam Desalegn at the Great Hall of the People on May 12, 2017, in Beijing, China.Thomas Peter | Getty Images
Chinese Premier Li Keqiang (R) and Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn at the Great Hall of the People on May 12, 2017, in Beijing, China.
The plan includes investing $20 billion in the power sector, and boosting the number of tourists visiting the country to 2.5 million annually.
Morley placed the expected gross domestic product (GDP) growth figure at 7-7.5 percent annually over the next five years, thanks to “growing consumer markets, greater integration into global and regional value chains and continued infrastructure investment.”

Belt and Road linchpin

Ethiopia is a key partner of China’s Belt and Road Initiative (BRI), a massive infrastructure spending push to resurrect ancient trading routes centred on China. This is partly because of its strategic location neighboring the tiny port state Djibouti, at which China has a naval base. A maritime presence in the region enables access to European markets via the Suez Canal.
Ethiopia is also attractive because of its low cost labor, transport links and a vast consumer market — with its population of over 100 million making it Africa’s second largest.
Although foreign direct investment (FDI) to Ethiopia has been hampered by unrest in recent years, this remains on an upwards trajectory. According to the Economist Intelligence Unit, Ethiopia attracted $4.2 billion in the fiscal year of 2016-17.
Morley said: “This is partly because large amounts of FDI is Chinese, going into industrial parks, and concerns about human rights and repression have proved less of a deterrent than might be the case with some Western states.”

wanted officials