Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, February 8, 2018

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና አቶ አንዷለም አራጌን ጨምሮ ከ700 በላይ እስረኞች እንዲፈቱ ተወሰነ።

ላለፉት 7 አመታት ያህል በወህኒ የቆዩት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አቶ አንዱአለም አራጌን ጨምሮ ከ700 የሚበልጡ እስረኞች እንዲፈቱ መወሰኑን የመንግስትና የፓርቲ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ።
ጠቅላይ አቃቢ ህግን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃኑ እንደዘገቡት በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ እንዲፈቱ የተወሰነላቸው እስረኞች ቁጥር በአጠቃላይ 746 ናቸው።
ከመስከረም 3/2004 ጀምሮ በወህኒ ቤት የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አንዱአለም አራጌ ከተፈቺዎቹ ውስጥ በስም ተጠቅሰዋል።
ነገር ግን ስለሌሎቹ ተፈቺዎች የተገለጸ ነገር የለም።
ተፈርዶባቸው በወህኒ ቤት ከሚገኙ እስረኞች ውስጥ 417ቱ በይቅርታ እንዲፈቱ የይቅርታ ቦርድ መወሰኑ ተገልጿል።
ለፊርማ ወደ ፕሬዝዳንቱ መሄዱም ተመልክቷል።
ክሳቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ 329 እስረኞች ደግሞ ክሳቸው እንዲቋረጥና ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል።
የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በወሰነው መሰረት እየተካሄደ ነው በተባለው እስረኞችን የመልቀቅ ተግባር በይቅርታ ከሚለቀቁት 417 እስረኞች 298ቱ ከፌደራል ወህኒ ቤት መሆናቸው ታውቋል።
119ኙ ደግሞ በአማራ ክልል የታሰሩ መሆናቸው ይፋ ሆኗል።
ክሳቸው እንዲቋረጥ የተወሰነላቸው ደግሞ 278ቱ ከፌደራል ወህኒ ቤት ሲሆን 18 ከአማራ ክልል እንዲሁም ከትግራይ ክልል ደግሞ 33 እንደሆኑም ተመልክቷል።
እስክንድር ነጋና አንዱአለም አራጌን ጨምሮ 417ቱ እስረኞች ከፕሬዝዳንቱ ፊርማ በኋላ የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ይፈታሉ ብለዋል መገናኛ ብዙሃኑ በዘገባቸው።
እስረኞቹ በትትክል መቼ ይፈታሉ ለሚለው ግን ቀን አልተቆረጠለትም።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ውስጥ ቀደምት ከነበሩት ጋዜጠኞች አንዱ ሲሆን ሃሳቡን በአደባባይ በመግለጹ ለ8 ጊዜያት ያህል በተደጋጋሚ የታሰረ ሲሆን ከ7 ከሚበልጡ አለምአቀፍ ተቋማት የፕሬስ ነጻነት ሽልማትን ተቀዳጅቷል።
እስክንድር ነጋ የተፈረደበት የ18 አመታት እስራት ነበር።

No comments:

Post a Comment

wanted officials