Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, January 28, 2020

የታገቱት ተማሪዎች፡ የቤተሰብ ሰቀቀን፤ የማሕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጩኸት፤ የመንግሥት ዝምታ


የተጋች ቤተሰብ
ከሚማሩበት የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለደህንነታቸው በመስጋት ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ሳለ ማንነታቸው ባልታወቀ ወጣቶች የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ አሁንም ምላሽ አላገኘም።
ተማሪዎቹ ከታገቱ 50 ቀናት አልፏቸዋል። ወላጆች ልጆቻቸው መታገታቸውን ከሰሙ አንስቶ ለሚመለከታቸው አካላት ልጆቻቸውን እንዲመለሱላቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ መንግሥት በጉዳዩ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ አልሰጠም።
የተማሪዎችን መታገት ተከትሎ ከቀናት በፊት ወደ አዲስ ዘመን ያቀናው የቢቢሲ ዘጋቢ ከተማዋ ሃዘን እንዳጠላባት ይናገራል።
የታጋች ቤተሰቦች ፊታቸው ጠቁሮ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆነው ነው ያገኘኋቸው የሚለው ዘጋቢያችን ቤተሰቦችን ማነጋገር እጅግ አሳዛኝ እንደነበር ያስረዳል።
መሪጌታ የኔነህ አዱኛ
አጭር የምስል መግለጫመሪጌታ የኔነህ አዱኛ
መሪጌታ የኔነህ አዱኛ የተማሪ ግርማሽ የኔነህ አባት ናቸው።
መሪጌታ የኔነህ ''በጥር 2 ተለቀዋል ስንባል ደስ ብሎን ነበር፤ ነገር ግን እስካሁን ከልጆቻችን ጋር አልተገናኘንም። መንግሥትም ያለን ነገር የለም። ገድለውብን ይሆናል ብለን እየፈራን ነው። በዚያ ላይ ልጆቹ አይተውት የማያውቁትን ነገር ሲያዩ ይደነግጣሉ ብለን እናስባለን። ሞተውም ከሆነ እውነቱን ነግረውን ቤተሰብ ጋር ተሰባስበን አልቅሰን እርማችንን ብናወጣ ይሻለናል፤ እንዲህ በየቀኑ ምን ሆነው ይሆን እያልን በሰቆቃ ከምንኖር" ይላሉ።
መሪጌታ እንደሚሉት የልጃቻቸው መታገት በቤተሰባቸው ላይ ከፍተኛ ጭንቀት ማሳደሩን ይናገራሉ። "ባለቤቴ ጨንቅላቷ ተጨንቆ ጸበል ወስጄ ነው ያከረምኳት" በማለት ይናገራሉ።
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
አጭር የምስል መግለጫወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ
ወ/ሮ ማሬ አበበ የተማሪ በላይነሽ መኮንን ወላጅ ናቸው።
ወ/ሮ ማሬ የእጅ ስልክ ስለሌላቸው በላይነሽን በስልክ ካገኙ ሰነባባተዋል። "ስልክ ስለሌለኝ የሆነው ሁሉ የምሰማው ከሰው ነው" ይላሉ።
''እህል አልበላ። ሌተ ተቀነ አይ ጉድ እያልኩ ነው። እግዜር ቢሰማን፤ መንግሥትም ቢራራልን፣ ልጆቻችን ቢሰዱልን እያልን ነው . . . አሳድጌ አሳድጌ ልጅ የለኝም ማለት ነው?" ሲሉም መልሰው ይጠይቃሉ።
ተማሪዎቹን መንግሥት እንዳስለቀቃቸው ሲሰሙ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቷቸው እንደነበረ የሚያስታውሱት ወ/ሮ ማሬ፤ "ወሬ ሆኖ ቀረ እንጂ" በማለት ተማሪዎቹ ተለቀዋል ቢባልም ከልጃቸው ጋር ሳይገናኙ እንደቀሩ ያስረዳሉ።
አቶ ሃብቴ እማኙ
አጭር የምስል መግለጫአቶ ሃብቴ እማኙ የተማሪ ግርማ ሃብቴ ወላጅ አባት
አቶ ሃብቴ እማኙ የተማሪ ግርማ ሃብቴ ወላጅ አባት ናቸው።
ልጃቸው ግርማ ከታገተ በሶስተኛው ቀን በአጋቾቹ ስልክ ደውሎላቸው እንደነበረ ያስታውሳሉ። "የነበረበትን አልነገረኝም። ብቻ ደህና ነኝ ነው ያለኝ።"
"ተስፋዬ የነበረው እሱ ነው" የሚሉት አቶ ሃብቴ፤ "እናቱ ቤተ-ክርስቲያን እየተንፏቀቀች እኔም የምሰራው ቅጡ ጠፋኝ። ልጄ የሚያውቀው ነገር የለም፤ የቤት ልጅ ነው። እንኳን የሰው አገር የራሱንም አያውቀው። . . . እናቱም የእሱን ሁኔታ አይታ በቤት ውስጥ የሉትን ልጆች ልትመራልኝ አልቻለችም" ይላሉ።
አቶ ሃብቴ "የማደርገው ጠፋኝ፤ ከፍ ብል ሰማይ ዝቅ ብል መሬት ሆኖብኝ፤ የእሱን መከራ ሳላይ ብሞት አይነደኝም ነበር" ይላሉ።
Presentational grey line
የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ላቀ አያሌው ከታገቱ ተማሪዎች ወላጆች መካከል የተወሰኑትን አነጋግሬአለሁ ይላሉ። ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ፤ እንደ አገር ተማሪዎችን ለማስለቀቅ የሚደረገው ጥረት አናሳ በመሆኑ ፈጥኖ መፍትሔ ማግኘት አልቻለም ባይ ናቸው።
«በተለይም አካባቢውን የሚያስተዳድረው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና የፌዴራሉ መንግሥት ትኩረት መስጠትና ተማሪዎችን ማስለቀቅ አለባቸው» በማለት ለክልሉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።

የማሕበራዊ ሚድያ ጩኸት

የተማሪዎች መታገት ከተሰማ ወዲህ ጀምሮ በማሕበራዊ ሚድያዎች በተለይም በፌስቡክና ትዊተር አለፍ ገደም ያሉ ዘመቻዎች መካሄድ ጀምረው ነበር። ከጥቂት ቀናት በፊት ጀምሮ ግን የማሕበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ጩኸታቸውን በሰፊው ማሰማት ጀምረዋል።
ታዋቂ ኢትዮጵያዊያን የማሕበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችም ዘመቻውን ተቀላቅለዋል። በተለይ ትዊተር በተሰኘው ማሕበራዊ መድረክ ላይ #Bringourgirlsback #Bringourstudentsback #WhereAreTheStudents? #ተማሪዎችየትገቡ? የተሰኙ ዘመቻዎች በመካሄድ ላይ ናቸው።

ስለታገቱት ተማሪዎች የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች በአማራ ክልል፡ ተካሄዱ


በባህር ዳር
አጭር የምስል መግለጫባህር ዳር
ሁለት ወር ለሚጠጋ ጊዜ የደረሱበት ያልታወቀ የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደህንነት ያሳሰባቸው በተለያዩ የአማራ ክልል ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች ድርጊቱን የሚቃወሙ ሰልፎች አካሄዱ።
በዩኒቨርስቲው ያጋጠመን አለመረጋጋት ሸሽተው ወደ መጡበት ሲመለሱ ባልታወቁ ወገኖች ተይዘው ደብዛቸው የጠፋው ተማሪዎች ጉዳይ ከመገናኛ ብዙሃን ርዕስነት አልፎ ለሰልፎቹ መካሄድ ምክንያት ሆኗል።
በዛሬው ዕለት በአማራ ክልል ርዕሰ ከተማ በተካሄደው የተማሪዎቹን መታገት በሚያወግዘው ሰልፍ ላይ በርካታ ቁጥር ያለው የከተማው ነዋሪ ተሳታፊ ሆኗል። በዚህም ምክንያት የተለያዩ የመንግሥትትና የግል ተቋማት ተዘግተው እንደነበር ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የሰላምና የህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ በክልሉ የተካሄዱት ሰልፎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን አስታውቋል።
ቢሮው ይህን ይበል እንጂ በባህር ዳር በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የክልሉ ባለስልጣናት በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለተገኘው ህዝብ መልዕክት ለማስተላለፍ ሲሞክሩ የተቃውሞ ድምጽ ተሰምቶ ዝግጅቱም መቋረጡን ሪፖርተራችን ከስፍራው ዘግቧል።
ከክቡር ትሪቡን አቅጣጫ ደንጋይ የተወረወረ ሲሆን ከስታዲየም ውጪም የተኩስ ድምጽ ሲሰማ ነበር።
በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር ከተማ በርካታ ጸጥታ አስከባሪዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ እና ከተማዋም ወደ የተረጋጋ እንቅስቃሴ መመለሷን ሪፖርተራችን ታዝቧል።
ከባህር ዳር ከተማ ውጪ ደብረማርቆስ፣ ወልዲያ፣ ቆቦ፣ዋድላ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ዱር ቤቴ፣ ዳንግላ፣ ደብረ ብርሃን፣ ፍኖተ ሰላም፣ እና በሬ የተቃውሞ ሰልፎቹ የተካሄዱባቸው ከተሞች ናቸው።
በተቃውሞ ሰልፎቹ የተሳተፉ ሰዎች መንግሥት የታገቱትን ተማሪዎች ጉዳይ ችላ ማለቱንና ተገቢውን መረጃ ባለመስጠቱ ወቀሳ ከማቅረባቸው በተጨማሪ፤ ታጋቾቹ ተለቀዋል ተብሎ የተሰጠው መግለጫን "ሐሰተኛ" በማለት ምላሽ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል።
ድርጊቱን ለማውገዝ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉት ሰዎች መንግሥት ስለታገቱት ተማሪዎች ተገቢውን መረጃ እንዲሰጥ፣ ተማሪዎቹ እንዲለቀቁ፣ መንግሥት በአጋቾች ላይ እርምጃ እንዲወሰድና በጉዳዩ ውስጥ እጃቸው አለበት የሚባሉ አካላትም በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።
ሰልፈኞች በባህር ዳርImage copyrightAMMA
በሁሉም ቦታዎች በተካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች ላይ በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ የነበሩና ለወራት የደረሱበት ያልታወቁት ተማሪዎች ያሉበት ሁኔታ እንዲገለጽ እንዲሁም በቶሎ ተለቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ በአጽንኦት ተጠይቋል።
ታግተዋል የተባሉት ተማሪዎች ቁጥር 17 እንደሆነ የተነገረ ሲሆን ከመካከላቸው 13ቱ ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል። በዚህም መሰረት ባለፉት ሳምንታት በማሕበራዊ የመገናኛ መድረኮች ላይ "እህቶቻችንን መልሱ" በሚል ርዕስ ዘመቻዎች ሲካሄዱ ቆይተዋል።
ቢቢሲ እስካሁን ባገኘው መረጃ ሰላማዊ ሰልፎቹ በባሕር ዳር፣ በወልዲያ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በደብረ ብርሃን፣ በዱርቤቴ፣ ፍኖተሰላም፣ በራያ ቆቦ፣ በሸዋ ሮቢት፣ በዳንግላና በሌሎች ቦታዎች ተካሂደዋል።
ሰልፈኞቹ፤ "የታገቱት ተማሪዎች የት አሉ?"፣ "ደብተርና ስክርቢቶ የያዙ ተማሪዎችን ማገት ጀግንነት አይደለም"፣ "ለታገቱ ተማሪዎች መጮህ ፖለቲካ ሳይሆን ሰብዓዊነት ነው"፣ "መንግሥት ተለቀቁ ያላቸው ተማሪዎች የት አሉ?" የሚሉ ጥያቄዎችና መልዕክቶችን ማስተጋባታቸውን የቢቢሲ ዘጋቢ ከስፍራው ገልጿል።
በባህር ዳር በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ 6 የታጋች ተማሪ ወላጆች ተሳታፉ መሆናቸውን ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አንዱ አቶ መታገስ ገ/ሚካኤል ለቢቢሲ ተናግረዋል።

Sunday, January 26, 2020

በባግዳድ የአሜሪካ ኤምባሲ የሮኬት ጥቃት ደረሰበት


በኢራቅ ጸረ አሜሪካ ተቃውሞዎች ሲደረጉ ነበር
Image copyrightREUTERS
አጭር የምስል መግለጫበኢራቅ ጸረ አሜሪካ ተቃውሞዎች ሲደረጉ ነበር
በትንሹ ሦስት ሮኬቶች ተወንጭፈው ባግዳድ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲን ትናንት እሑድ እንደመቱ ተገለጸ።
የመጀመርያው ሮኬት የኤምባሲው ካፍቴሪያ ላይ ሲወድቅ የተቀሩት ሁለቱ ደግሞ በቅርብ ርቀት ወድቀዋል ይላል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በዘገባው።
ሮይተርስ በበኩሉ በጥቃቱ በትንሹ ሦስት ሰዎች የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል ሲል ዘግቧል። አሜሪካ ኤምባሲዋ ላይ ጥቃት ሲደርስ ይህ በረዥም ዓመታት ውስጥ የመጀመርያው ነው ተብሏል።
እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ባይኖርም አሜሪካ ግን ኢራን የምትደግፈው የኢራቅ ወታደራዊ ክንፍ ነው ድርጊቱን የፈጸመው ብላለች።
የኢራቁ ጠቅላይ ሚኒስትር አዲል አብዱል መሐዲ ጥቃቱን ያወገዙ ሲሆን እንዲህ አይነት ጥቃቶች ኢራቅን ዳግም ወደ ወታደራዊ አውድማነት ይቀይራታል ብለዋል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ "የኢራቅ መንግሥት የአሜሪካ ጥቅሞችን በማስጠበቅ ግዴታውን ሊወጣ የግድ ይለዋል" ብሏል።
በቅርብ ጊዜ የአሜሪካ ወታደራዊ ማዕከል ጥቃት ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል።
ይህም የሆነውን አሜሪካ ቁጥር አንድ ኢራናዊውን ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን በሰው አልባ አውሮፕላን ተኩሳ ከገደለችው በኋላ ነው።
በዚያ ጥቃት ከሱለይማኒ ጋር የነበረው ኢራቃዊው የካታቢ ሂዝቦላህ ክንፍ መሪ አብዱ መሐዲ አልሙሐንዲስም ተገድሏል።
እጅግ ተጽእኖ ፈጣሪ የሚባሉት የሺዓው ሼክ ሙቅታድ አልሳድር አሜሪካ አካባቢው ለቃ እንድትወጣ ሰፊ የተቃውሞ ሰልፎች እንዲደረጉ ጥሪ አቅርበው ነበር።
የሳድር ደጋፊዎች ጸረ አሜሪካ ተቃውሞ ማድረግ ከመጀመራቸው በፊት የኢራቅ አስተዳደር ፈርሶ በአዲስ እንዲዋቀር በጎዳና ላይ ነውጥ ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።

Friday, January 24, 2020

ሩዋንዳ የወባ ትንኞችን ለመግደል 'ድሮኖችን' አሰማራች


ሩዋንዳ
Image copyrightGETTY IMAGES
የሩዋንዳ መንግሥት የወባ ትንኞች በመራቢያ አከባቢያቸው ለመግደል ድሮኖችን በመጠቀም ጸረ-ወባ ኬሚካል ርጭት ማካሄድ ጀመረ።
የሩዋንዳ ባዮሜዲካል ማዕከል ኃላፊ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ድሮኖች 10 ሊተር ጸረ-ተባይ ኬሚካሎችን ይዘው በመነሳት የወባ ትንኞች ያስወግዳሉ።
ቤት ለቤት የኬሚካል ርጭትን እንዲሁም አጎበርን በመጠቀም የወባ ትንኞችን የመከላከል ጥረትን ድሮኖቹ እንደሚያግዙ ኃላፊው አኢምብሌ አምቢቱዩሙሬመይ ተናግረዋል።
"አሁን ፍላጎታችን የወባ ትንኞቹን ከምንጫቸው ማስወገድ ነው። ድሮኖቹ በመጀመሪያ የእድገት ደረጃ ላይ ያሉ የወባ ትንኞችን የሚገድል ኬሚካል ነው የሚረጩት" ብለዋል።
ሰው አልባ በራሪዎቹ የሚረጩት ኬሚካል በሰው እና በአከባቢ ላይ የሚያስከትሉት ጉዳት እንደማይኖር ተነግሯል።
የሩዋንዳ ባዮሜዲካል ማዕከል አሃዝ እንደሚጠቁመው በፈረንጆቹ 2018 እና 2019 መካከል 3.9 ሚሊዮን ሩዋንዳውያን በወባ በሽታ ተይዘዋል።
ይህ አሃዝ ግን 2017 ከነበረው በወባ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ጋር ሲነጻጸር፤ ዝቅተኛ ነው።
እአአ 2017 ላይ 4.8 ሚሊዮን ሩዋንዳውያን በወባ በሽታ ተይዘው ነበር።
ሩዋንዳ ከዚህ ቀደም ድሮኖችን በመጠቀም በገጠራማ አከባቢዎች ለሚገኙ ክሊኒኮች ደም እና መድሃኒቶችን ያቀርባሉ።

Wednesday, January 22, 2020

የአሲድ ጥቃት የደረሰባት ኢትዮጵያዊት በትራምፕ የድጋፍ ደብዳቤ ወደ አሜሪካ አቀናች


አፀደ ንጉስ ከአሲድ ጥቃቱ በፊትና በኋላ
Image copyrightMENBERE AKLILU FB
በአዲግራት ከተማ ተወልዳ ያደገችው አጸደ ንጉሥ 2ኛ ደረጃ ትምርቷን በያለም ብርሃን፤ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአግአዚ ትምህርት ቤት ተከታትላለች።
አልገፋችበትም እንጂ ለከፍተኛ ትምህርት የሚያበቃትን ነጥብ አምጥታ ሐዋሳ ዩኒቨርስቲም የዲግሪ ትምህርቷን መከታተል ጀምራ ነበር።
ይሁን እንጅ ከሁለት ዓመት በፊት በገዛ ባለቤቷ የተፈጸመባት አሰቃቂ ጥቃት የሕይወቷን አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ለውጦታል።
"እናቴ ብቻዋን ነው ያሳደገችኝ፤ አባቴ ታጋይ ነበር፤ ወደ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ የወሰደኝ ኑሮን ለማሸነፍ በሚል ነበር። በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በሚሠራ አንድ ሕንጻ ውስጥ ሥራ አገኘሁ።" ትላለች።
አጸደ በዚያ ጊዜ ነበር ሕይወቷን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያመራ ያደረገውን ባለቤቷን የተዋወቀችው።
"እሱ የፌዴራል ፖሊስ ባልደረባ ነበር። በዚያ ወቅት ደግሞ በጅግጅጋ ፖሊስ የፈለገውን ነበር የሚያደርገው፤ ስለዚህ በጣም እፈራው ነበር" ትላለች ጊዜውን ስታስታውስ።
የትዳር ጥያቄውን የተቀበለችው ወዳና ፈቅዳ ሳይሆን በፍርሃት እንደነበረ ታስረዳለች።
የተወሰነ ጊዜ ጅግጅጋ ከቆዩ በኋላ ወደ ጋምቤላ እንደሚሄዱ ነገራት።
በጋምቤላ ከተማ እሱ ባጃጅ እየሠራ እሷ ደሞ ጅግጅጋ ትሠራ እንደነበረው ዓይነት ተመሳሳይ የኮንስትራክሽን ሥራ ውስጥ እየሠራች መኖር ጀመሩ።
በዚያው ዓመት፤ በ2004 ዓ.ም መሆኑ ነው፤ ወንድ ልጅ ተገላገለች።
አጸደ እየቆየች ስትሄድ ግን "ትዳር ማለት የሕይወትን ሸክም ተካፍሎ ማቅለል ነው" የሚለው ትርጉም እውነት ሆኖ አላገኘችውም።
"ባለቤቴ ሞገደኛ ነው፤ በሚረባውም በማይረባውም፤ በትንሹም በትልቁም ይመታኛል፤ ያከራዩኝ ሰዎች ሁኔታችንን ሲያዩ እግዚኦ ይላሉ።" ትላለች የነበረችበትን ሕይወት ወደ ኋላ መለስ ብላ ስታስታውስ።
ምንም እንኳን ድብደባው ቢበረታባትም፤ አጸደ እሷ ያደገችበትን ሁኔታ ስለምታውቅ ልጇን ያለ አባት ልታስቀረው አልፈቀደችም።
"ልጅ ከወለድኩ በኋላ እኛ አባታችን ስላልነበረ፤ እናታችን እንዴት ተቸግራ እንዳሳደገችን ስለማውቅ ሁሉን ችዬ እኖር ነበር። እንደዚያ ሲደበድበኝ አንድ ቀን እንኳን ለእናቴም ሆነ ለእህቴ ነግሬያቸው አላውቅም፤ አንድም ቀን" ስትል እምባ እየተናነቃት ለቢቢሲ ተናግራለች።
ከልጇ ጋር ሁሉን ችላ መኖሯ ግን የኋላ ኋላ መዘዝ ይዞባት መጣ። "የነበርኩበትን ሁኔታ የሚያውቁ ዘመድ አዝማዶች እናነጋግረው ሲሉኝ 'ተው እንጂ! ምንም ቢሆን እኮ የልጄ አባት ነው' እያልኩ ኑሮዬን ቀጠልኩ" ትላለች።
ነገሮች በዚህ ሁኔታ ቀጠሉ። በ2007 ዓ.ም ልጇን አዲግራት የምትኖረው እናቷ ጋር እንድትወስደው እሷ ደግሞ ከነበረችበት ሥራ ወጥታ በራሷ ሥራ እንድትጀምር ሐሳብ አቀረበላት። የሰጣት ገንዘብ ግን አልነበረም።
ልጇን ትታ መኖሩ እንዳሰበችው ቀላል አልነበረም። ስለ ልጇ ትብሰለሰል ያዘች። ቀኑ ነግቶ አልመሽ አላት።
አንድ ቀን "ወይ ከሥራዬ ወይ ከልጄ አልሆንኩ ምን ተሻለ?" ብላ ትጠይቀዋለች። እርሱ ግን ሀሳቧን እና ጭንቀቷን ከመጤፍ ሳይቆጥር ገንዘብ የሚባል የለኝም፤ የማውቀው ነገር የለም ሲል እንደመለሰላት ትናገራለች።
በዚህ አንድ ሁለት ሲባባሉ በተነሳ ግጭት በቡጢ ስለመታት ፊቷ አብጦ ነበር
ጋምቤላ ያሉ ዘመዶች እሷና ባሏ ተስማምተው መኖር እንደማይችሉ በመረዳታቸው ተለያይተው እንዲሞክሩት በማሰብ እሷ ወደ አገሯ ሄዳ ሥራ እንደትሰራ ይመክራሉ።
በዚህም ተስማምተው 10 ሺህ ብር ሰጥተው አለያዩኝ ትላለች።
ወደ አዲግራት እንደተመለሰች አረብ አገር የምትኖር እህቷና እናቷ አግዘዋት ትንሽዬ የውበት መጠበቂያ ምርቶች [ኮስሞቲክስ] መሸጫ ሱቅ ከፈተች። ጥሩ መንቀሳቀስ ጀምራም ነበር።
ባለቤቷ ግን ድንገት ወደ አዲግራት ጠቅልሎ በመምጣት በቤተሰብ ግፊት በድጋሚ አብረው መኖር ጀመሩ።
ይሁንና አሁንም ሊስማሙ አልቻሉም። ይባስ ብሎ ሱቋ ውስጥ "ማን ገባ? ማን ወጣ?" እያለ መጨቃጨቅ ጀመረ።
ከዕለታት አንድ ቀን ባለቤቷ ብድግ ብሎ ወደ አረብ አገር ሄደ፤ ሳይነግራት። ከጂቡቲ ድንበር ደውሎ 8 ሺህ ብር ለደላላዎች ላኪልኝ አላት። በሁኔታው የተደናገጠችው አጸደ ከዚያም ከዚህም ብላ ላከችለት።
ከየመን ወደ ሳዑዲ ከተሻገረ በኋላ ደግሞ አረብ አገር ከምትኖረው እህቷ የሒሳብ ደብተር 15 ሺህ ብር እንድታስልክ አደረገ። ሳዑዲ ከገባና ሥራ ከጀመረ በኋላ ግን ጭራሽ መደወል ትቶ እንደተራራቁ ትናገራለች።
ሄድኩ ሳይል እንደወጣው፤ ከእለታት አንድ ቀን ደግሞ መጣሁ ሳይላት መጣ- አዲግራት።
"አሲድ አይቼ አላውቅም"
ቅዳሜ ሐምሌ 8 ቀን 2009 ዓ.ም።
አጸደ እዚያች ኮስሞቲክስ መሸጫ ሱቋ ውስጥ ምሽት ላይ ከጓደኛዋ ጋር እራት በልተው ይጫወቱ ነበር።
በጨዋታቸው መካከልም አንድ አፍታ ባለቤቷ ውልብ ሲል አየችው። በዚያ አካባቢ እሱን ማየቷ ደስ ስላላት ጓደኛዋን ትታ ወደ ቤቷ ጉዞ መጀመሯን ታስታውሳለች።
ጉዞዋ ቤታቸው በር እስክትደርስ ሰላማዊ ነበር።
"ቤታችን ግቢው በር አካባቢ ዝግባና ጥድ አለ። እዚያ ተደብቆ ቆይቶ ድንገት ደፋብኝ። ይሄ ቢጫው ሐያት የሚባለው የዘይት መያዣ ጄሪካን አለ አይደል? በሱ አሲድ ይዞ ነበር፤ ከዚያም ደፋብኝ" ትላለች።
በወቅቱ በመላ አካሏ ምን እንደፈሰሰባት የምታውቀው ነገር አልነበረም።
"የተደፋብኝ ነገር ጋዝ ነበር የመሰለኝ፤ በእሳት ሊያቃጥለኝ ፈልጎ መስሎኝ ነበር" ትላለች።
"ትንሽ ቆይቶ ግን ሰውነቴ መንደድ ጀመረ። ኡኡ እያልኩ ድረሱልኝ ስል ጮህኩ፤ እሱ ግን ባጃጅ አዘጋጅቶ ስለነበር አመለጠ። እናቴም እህቴም ባጃጁን ቢከተሉትም ሊደርሱበት አልቻሉም።"
አሁን ከራስ ቅሏ መላ አካላቷ የፈሰሰው አሲድ መላ አካላቷን ቀይሮታል። የዐይን ብርሃኗን አሳጥቷታል።
በጠዋት በሙሉ አካሏ ትታው የወጣችበት ቤት ማታ ተመርታ ገባች።
አጸደ በሕይወቷ አሲድ አይታ አታውቅም።
"ቃሉንም የማስታውሰው ኬሚስትሪ ስንማር ነው። በጭራሽ አይቼ አላውቅም። ሐኪሙም ግራ ገብቶት ነበር፤ ስለዚህ እርዳታ በቶሎ ማግኘት አልቻልኩም" ትላለች።
በመጀመሪያ አካባቢ ዐይኗ አካባቢ በተደረገላት ሕክምና የተወሰነ ማየት ጀምራ ነበር። ነገር ግን ዕይታዋ ከአንድ ሳምንት አላለፈም።
በዚህ የአሲድ ጥቃት ከዕይታዋ በተጨማሪ አንድ እግሯ፣ ሁለቱም እጆቿ፣ ሙሉ የፊት ገጽታዋ እስከ ደረቷ ድረስ፤ ጸጉሯ፣ የራስ ቅሏ እንዲሁም ጆሮዎቿ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ለአርባ ቀናት የተመላለሰችበት የአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ብዙም እንዳልረዳት ትናገራለች።
ለተሻለ ሕክምና ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ከተላከች በኋላም 40 ቀን የቆየ የአሲድ ጥቃት እንዴት አድርገን እንቀበል ብለው እምብዛምም ሊረዷት እንደማይችሉ እንደነገሯት ታስታውሳለች።
ሆኖም በመጨረሻ እኔ ኃላፊቱነት እወስዳለሁ ያለች አንዲት ሐኪም በማግኘቷ እርዳታ ማግኘት እንደቻለች እምባ እየተናነቃት ትናገራለች።
"ዐይንሽ መውጣት አለበት"
አጸደ በ2010 ዓ/ም መጀመሪያ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ታይላንድ ሄዳ ነበር። ለሁለት ወራት በዘለቀው ሕክምና ከ3 መቶ ሺህ በላይ ብር አስፈልጓት ነበር።
ይህንን ወጪ ለመሸፈን አቅሙ ስላልነበራት በተለያዩ አገራት በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና የሌሎች አገር ዜጎች ጭምር ድጋፍ አድርገውላት ሕክምናውን መከታተል ጀመረች።
ሆኖም ሕክምናው እንዳሰበችው አልሆነላትም። ከሁሉም በላይ ይመልሱልኛል ብላ ተስፋ ያደረገችበት እና በጉጉት ትጠብቀው የነበረው የዐይን ብርሃኗ መርዶ ይዞ መጣ።
አብራት የነበረችው ታላቅ እህቷ አንድ እሁድ ጠዋት በግሏ ይዛው ቆይታ የነበረውን ትልቅ ምሥጢር ነገረቻት።
"ኢንፌክሽን እየፈጠረብሽ ስለሆነ መውጣት አለበት ተብሏል አለችኝ" ስትል ዕለቱን በጠለቀ ሐዘን ታስታውሳለች።
እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን እሄድ ነበር፤ "ዐይኔን በሰንበት እንዲያወጡት አልፈልግም፤ አገሬ ውሰጅኝ አልኳት" ለእህቴ ትላለች።
ሕክምናዋን አቋርጣ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰቸው አጸደ፤ በሴቶች ማኅበር አዲስ አበባ በተቋቋመ ጾታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ማገገሚያ ማዕከል ለስምንት ወር እንድትቆይ ተደረገች።
"አንድ ሰው በረዳህ ቁጥር ያንተ ቁስል እየሻረ ይሄዳል" ወ/ሮ መንበረ አክሊሉ
በዚህ ማገገሚያ ማዕከል ሳለች በአርቲስት አዜብ ወርቁ በኩል አንዲት እገዛ ልታደርግላት የምትችል ሴት አገኘች፤ ይቺ በጎ አድራጊ ሴት ወ/ሮ መንበረ አክሊሉ ናት።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የምትኖረው መንበረ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችን በማገዝ ስሟ የሚጠራ በጎ አድራጊ ናት።
በወንዶች የሚፈጸም ጥቃትን ጊዜ ሳትሰጥ የምታግዝበት ምክንያት እርሷም ኢትዮጵያ ሳለች ያለ ፈቃዷ በልጅነቷ ያገባቸው ሰው ያደረሰባት ግፍና መከራን በማስታወስ እንደሆነ ትገልጻለች።
"ሲጋራውን ካጨሰ በኋላ፤ ፊቴ ላይ ይተረኩሰው ነበር፤ አፍንጫዬን እስከመስበር የደረሰ ጥቃት ያደርስብኝ ነበር፤ ሦስት አራት ጊዜ ሊገድለኝ በመሞከሩ በመጨረሻ ቤቴን ለቅቄ እንድጠፋ ሆንኩ። በዚህ ምክንያት ጎዳና ለማደር ሁሉ በቅቼ ነበር በአንድ ወቅት" ትላለች ወ/ሮ መንበረ።
አሁን ያ ጊዜ አልፎ መልካም ትዳርና ጥሩ ሕይወት እየመራች እንደሆነ ትናገራለች።
በአጸደ የደረሰውን የአሲድ ጥቃት በማህበራዊ ሚዲያ በኩል መስማቷን የምትናገረው መንበረ፤ ከባለቤቷ ጋር በመመካከር እሷን ለመርዳት እንደወሰኑ ለቢቢሲ ገልጻለች።
"እሷ ላይ የደረሰውን ስመለከት እንደ ማንኛውም ዜጋ ሐዘን ተሰማኝ። በተለይ ልጅ እንዳላት ስሰማ አዘንኩ። እኔም እናት ስለሆንኩ ራሴን በእሷ ቦታ አስቀመጥኩት፤ በዚህ ልቤ እጅግ ተነካ፤ ከዚህም በተጨማሪ እኔም ያለፍኩበት መንገድ ስለሆነ እሷን ማገዝ አለብኝ ብዬ ተነሳሁ።"
መንበረ በአሲድ የተጠቃችን ዜጋ ስታግዝ አጸደ የመጀመሪያዋ አይደለችም።
በፈረንጆቹ በ2017 ዓ.ም አንዲት መሠረት የምትባል በፍቅረኛዋ አሲድ የተደፋባት ሴት ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በመውሰድ ሕክምና እንድታገኝ አድርጋለች።
መሠረት አሁን በመልካም ጤንነትና በጥሩ መንፈስ አሜሪካ ራሷን ችላ እየኖረች ትገኛለች።
አጸደን ወደ አሜሪካ ለመውሰድም ለመንበረ መንገዱ አልጋ በአልጋ አልነበረም።
ሦስት ጊዜ ያህልም በአሜሪካ ኤምባሲ ጉዳዩ ተቀባይነት አላገኘም ነበር። በመጨረሻም ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ደብዳቤ ጽፋ፤ በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ነበር የተሳካው ትላለች።
የአጸደ ጉዳይ ልዩ ትኩረት እንደሚሻ የምትናገረው መንበረ "አሁን አጸደ ዐይነ ስውር ናት። ሆኖም በቅርቡ ማየት እንደምትችል እርግጠኛ ነኝ" ስትል ሙሉ ተስፋዋን ትገልጸላች።
"ራሴን ስለምወደው ነው እሷን ለማገዝ የወሰንኩት። ምክንያቱም አንድ ሰው ባገዝክ ቁጥር ያንተ ቁስል እየሻረ ይሄዳል። ምናልባትም እኔ ያደረኩት ነገር አይተው ሌሎች ሰዎችም ሌሎችን ማገዝ ይጀምሩ ይሆናል።" ትላለች መንበረ።
አጸደ አሁን ከመንበረ ጋር እየኖረች ትገኛለች። መንበረ የአጸደን የሕክምና ሁኔታ እና በሕይወቷ ስላሳደረችባት አዎንታዊ ተጽእኖ በማህበራዊ ሚዲያ ጽፋ ነበር።
አጸደ በበኩሏ ስለሷ የምትናገርበት ቃላት እንደሌላት ትናገራለች። ስላደረገችላት ነገር መናገር ስትጀምር ከቃላት ቀድመው እምባዎቿ ዱብ ዱብ ይላሉ።
"ዓለም የሁላችንም ናት"
አጸደ በአሜሪካ ያካሄደችውን ሕክምና እንደወደደችው ትገልጸላች። በተደረገላት የመጀመሪያ ቀዶ ጥገና የዐይን ክዳን እንደተሰራላት ትገልጻለች።
አሁን ዐይኗን መክደንና መግለጥ ትችላለች፤ የአሲድ ጥቃቱ የዐይን ብርሃኗን ብቻም ሳይሆን የዕይን ሽፋኗን ሙሉ በሙሉ አጥፍቶት ነበር።
በቅርቡ ደግሞ እዚያው አሜሪካ ለመኖር የሚያስችላትን ፍቃድ አግኝታለች። ይህ ደግሞ ከእሷ ተለይቶ ኢትዮጵያ የሚገኘው ልጇን ወደ አሜሪካ ለመውሰድ የሚያስችላት ነው።
አጸደ ስለ ሕይወት ያላት ትርጉም የሚደንቅ ነው።
"መልኬን አይቼው አላውቅም። እኔ ከ2 ዓመት በፊት የነበረችው አጸደን እንጂ አሁን ያለችውን አጸደን አይቻት አላውቅም" ትላለች።
የደረሰባት አካላዊ ጥቃት ሕይወቷን እንድትጠላ እንዳላደረጋት ግን አስረግጣ ትናገራለች።
በተቃራኒው እንዲያውም ለሕይወት መልካም አተያይን አዳብራለች።
"ሕይወት የሁላችንም ናት፤ በዚህ ዓለም ብዙ ጨካኝ አለ፤ ብዙ መልካም ሰዎች ደግሞ አሉ። በተለይ አንዳንድ ጊዜ ፈጣሪ እንዲህ ዓይነት ፈተና የሚያመጣብን ዓለም መልካም ሰዎች እንዳሏት እንድናስተውል ይሆን?" ትላለች።
አጸደ ከሕክምናዋ ጎን ለጎን ትምህርት ትማራለች። ማየት የማይችሉ ሰዎች የሚጠቀሙበትን የብሬል ትምህርት ተምራ አጠናቃለች። አሁን ደግሞ ኮምፒውተር እየተማረች ነው።
"ተምሬ ትልቅ ደረጃ እንደምደርስ እርግጠኛ ነኝ። አላማዬም እሱ ነው። ወደ ኋላ ተመልሼ የምጸጸትበት ነገር አይኖርም።"
"እሷ እናቴ አይደለችም የኔ እናት ቆንጆ ናት"
የአጸደ ልጅ ሃኒ ነው ስሙ።
ትናንት የደረሰባትን በደል፤ ደም ግባቷንና ዕይታዋን አስረስቷታል። አሁን ብርሃኗ ልጇ ነው።
ሀኒ ዕድሜው ገና 7 ነው። እኔ በሕይወት የምኖርበት አንዱ ምክንያቴ እሱ ነው ትላለች።
ይህ አደጋ አጸደ ላይ ሲደርስ እሱ ገና 5 ዓመቱ ነበር። በአሲዱ ምክንያት የደረሰባትን የገጽታ ለውጥ ሲመለከት ታዲያ በልጅነት አዕምሮው እናቱን ሊለያት አልቻለም።
"መጀመርያ ላይ በጣም ፈርቶ ነበር። እናትህ አጸደ እኮ እሷ ናት ሲሉት፤ ኖ ኖ እሷ እናቴ አይደለችም፤ የኔ እናት ቆንጆ ናት" እንዳለ ታስታውሳለች።
"አሁን ግን ሁኔታዎችን ስለተረዳ አይዞሽ ይለኛል። እሱ ስላለልኝ ደግሞ እኔ ጠንክሬ በሁለት እግሬ ለመቆም ቻልኩ ትላለች።"
አሁን ልጇ በአባቱ ቂም ቋጥሮ ጥላቻ እንዲያሳድር እንደማትፈልግ ትናገራለች።
"ልጄ ይቅርታ አድራጊ ሰው እንዲሆን ነው የምፈልገው። እኔም ይቅርታ አድራጊ ሰው እንድሆን እንጂ እንዲህ አድርጎኝ የምል ሰው መሆን አልፈልግም።" ትላለች።
"እኔን ሳይሆን የገዛ ልጁን ነው የበደለው" በማለት ልጇ በለጋ እድሜው መሸከም ከሚችለው በላይ ጫና መሸከሙን ትናገራለች።

የዘገየ ፍትሕ

የአጸደ ጥቃት አድራሽ ዛሬም ድረስ በፍትሕ አደባባይ አልቆመም። በወቅቱ የሚመለከተውን ክፍል ያሳወቀች ቢሆንም ይገኝበታል የሚባልባቸው ቦታዎችን ፈልጎ ለሕግ ለማቅረብ የሚመለከታቸው አካላት ግዴታቸውን እንዳልተወጡ ትናገራለች።
በደል የሚፈጽሙ አካላት በወቅቱ ሊጠየቁና የሚገባቸውን ቅጣት እንዲያገኙ የሚያስችል ሕግ እንደሌለ ጨምራ ታስረዳለች።
መንበረ በበኩሏ ሕብረተሰብን ከማስተማር ጎን ለጎን በአጥፊዎች ላይ ተገቢውን ቅጣት መጣል እንዲህ አይነት ወንጀሎች እንዳይፈጸሙ ያግዛል ትላለች።
ምክንያቱም ትላለች መንበረ፤ ይህ የአሲድ ጥቃት አጸደን ብቻ አይደለም የጎዳት፤ ልጇን፣ እናቷን፣ እህቷን እንዲሁም መላ ቤተሰቧንም ጭምር ነው።
ይህንን በተመለከተ የትግራይ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋን አነጋግረናቸው ነበር።
ይህንን ወንጀል የፈጸመው ሰው ጠፍቶ ከአገር መውጣቱን የገለጹት አቶ አማኑኤል፤ ፖሊስ ከመጀመሪያው ይህንን ጥቃት ስለፈጸመው ሰው የተሟላ መረጃ አለማግኘቱን፤ በኋላም ወደ መሀል አገር ሄዷል በተባለ ጊዜ ደግሞ በአገሪቱ በነበረው ፖለቲካ፤ መሀል አገር ላለው አካል አመልክተው ሊተባበሯቸው እንዳልቻሉ ይገልጻሉ።
በአቃቢ ሕግ በኩል ደግሞ መጀመሪያ ችግሩ የነበረው በሕይወት ትቆያለች ወይ የሚለውን ለመገመት አስቸጋሪ ስለነበረ አቃቢ ሕግ በምን አግባብ ይክሰስ የሚለው አልተወሰነም ነበር ይላሉ።
"በአካል ማጉደል ከስሶ፤ በኋላ ደግሞ አንድ ጊዜ ከተፈረደበት በኋላ መልሶ በሰው መግደል ልታስፈርድበት ስለማይቻል አስቸጋሪ ነበር" ብለዋል ኃላፊው።
በኋላ ግን ሁኔታዎች በሕክምና ከተረጋገጡ በኋላ ግለሰቡ በከባድ የመግደል ሙከራ ተከሷል። አሜሪካ ሆና በ'ስካይፕ' ቃሏን እንድትሰጥ ተደርጎ ምርመራ ተካሄዶ አሁን ተከሶ እድሜ ልክ እንደተወሰነበት አቶ አማኑኤል ይገልጻሉ።
ወንጀለኛው በኢንተርፖል ወይም በሌላ መልኩ ወደ አገሩ ሲገባ ይህ ቅጣት ተፈጻሚ ይሆናል።
"ምን በድዬህ ነው?"
ከዚያች መጥፎ ዕለት ጀምራ አጸደ ባለቤቷን አይታው አታውቅም፤ ስለሱ ሰምታም አታውቅም። በአካል ድጋሚ ብታገኘው ግን አንድ ጥያቄ ልትጠይቀው አንደምትፈልግ ለቢቢሲ ተናግራለች።
"ምንድን ነው የበደልኩህ?" የሚል

አሜሪካ ነፍሰ ጡር ቪዛ አመልካቾች ለመቆጣጠር አዲስ ሕግ አወጣች



አውሮፕላን በአሜሪካ ሲያርፍImage copyrightGETTY IMAGES
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነፍሰ ጡር ሴቶች ለመውለድ ሲሉ ወደ አሜሪካ እንዳይሄዱ ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ ሕግ አወጣ።
'የወሊድ ቱሪዝም' ተብሎ የሚጠራውን እና አሜሪካ ሄዶ ለመውለድ የሚደረግን ጉብኝት ለመከላካል የወጣው ፖሊሲ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።
ሕጉ ነፍሰ ጡር ሴቶች ለሥራ ወይም ለጉብኝት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቪዛ ሲያመለክቱ፤ ወደ አሜሪካ የሚሄዱበት ዋነኛ ምክንያት ለመውለድ አለመሆኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል ይላል።
በአሜሪካ ሕግ መሠረት በአገሪቷ የሚወለዱ ልጆች በቀጥታ የአሜሪካ ዜግነት ያገኛሉ። ይህ ሕግ ግን በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ሲተች ቆይቷል
የፕሬዚደንት ትራምፕ አስተዳደር አዲሱ የጉዞ ሕግ የአገሪቷን ብሔራዊ ደህንነትና የሕዝብ ጤና ለመጠበቅ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግሯል።
ትራምፕ ወደ አገሪቷ የሚገቡ ስደተኞችን ለመቀነስ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን፤ ቀደም ብሎ "በአሜሪካ ለተወለዱና ለኖሩ የሌላ አገር ዜጎች" ዜግነት እንደሚሰጥ የሚገልፀው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት መሻሻል እንዳለበት ጠይቀዋል።

አዲሱ ሕግ ምን ይላል?

አዲሱ ሕግ 'ቢ' ቪዛ የሚጠይቁ ሁሉንም አመልካቾች ይመለከታል።
የቪዛ ኦፊሰሮች ዋነኛ አላማቸው ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚገቡ ሴቶችን ቪዛ እንዲከለክሉ ይፈቅዳል።
"የወሊድ ቱሪዝም ኢንደስትሪ የዓለም አቀፉን የወንጀል መስፋፋት ጨምሮ ከወንጀል ድርጊቶች ጋር የተያያዘ ነው" ሲልም ሕጉ ያስረዳል።
ከዚህም በተጨማሪ ሕጉ የተሻለ ሕክምና ለማግኘት ሲሉ ወደ አሜሪካ የሚገቡ ሰዎችም ላይ የሚደረገውን ቁጥጥርም ያጠብቃል።
በመሆኑም ቪዛ አመልካቾች የህክምና ወጪያቸውን ለመሸፈን የሚያስችል የገንዘብ ምንጭና አቅም እንዳላቸው፤ እንዲሁም ህክምናውን ከሚሰጣቸው ዶክተር ጋር ቀጠሮ እንዳላቸው ለቪዛ ኦፊሰሩ በማቅረብ ማሳመን ይጠበቅባቸዋል።
የፕሬዚደንቱ ፕረስ ሴክሬታሪ ስቴፋኒ ግሪሻም፤ በመግለጫቸው እንዳሉት "የወሊድ ቱሪዝም ኢንደስትሪው በሆስፒታሎች ወሳኝ ግብዓቶች ላይ ጫና ያሳደረ ሲሆን የወንጀል ድርጊቶችንም አባብሷል ብለዋል።
በመሆኑም ሕጉ ይህንን አገራዊ የሆነ ችግር ለመከላከልና አሜሪካን በዚህ ምክንያት ከሚከሰቱ የብሔራዊ ደህንነት አደጋዎች መጠበቅ እንደሚያስችል ጨምረው ተናግረዋል።

በወሊድ ቱሪዝም ምን ያህል ህፃናት ተወልደዋል?

በየአመቱ ወደ አሜሪካ ከሚያቀኑ ሰዎች ምን ያህል ህፃነት እንደተወለዱ የሚያሳይ የተመዘገበ መረጃ ባይኖርም የተለያዩ አካላት ግን ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።
እንደ የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል መረጃ በአውሮፓዊያኑ 2017 በአሜሪካ ከሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች 10 ሺህ የሚሆኑ ሕፃናት ተወልደዋል። ይህም የቅርብ ጊዜ መረጃ ነው።
ይህ ቁጥር በአውሮፓዊያኑ 2007 ከነበረው 7,800 የህፃናት ቁጥር ጨምሯል።
የስደተኞች ጥናት ማዕከል ደግሞ በ2016 እና 2017 መጀመሪያው አጋማሽ ጊዜያዊ የጉብኝት ቪዛ ካላቸው እናቶች 33 ሺህ ህፃናት መወለዳቸውን ያስረዳል።
አሁን ላይ ነፍሰጡር ሴቶች እስከሚወልዱ ድረስ ለመቆየት ወደ አሜሪካ መግባት እንደሚችሉ የአሜሪካ የጉምሩክና ድንበር ጥበቃ መሥሪያ ቤት አስታውቋል።
ይሁን እንጅ እናቶች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ በመቆየት ለመቅረት ፍላጎት እንዳላቸው ከታመነ ጉዟቸው ሊከለከል ይችላል።

wanted officials