Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, August 25, 2018

አርቲስት፣ አክቲቪስትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነን የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት በተመለከተ!

አርቲስት፣ አክቲቪስትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነን የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት በተመለከተ!
Image may contain: 1 person
.
እጅግ በጣም ተወዳጁ የአገር ባለውለታ ታማኝ በየነ
ወደ እናት አገሩ ወደ ኢትዮጵያ ከረጅም ዓመት ቆይታ በኋላ ነሐሴ 26 ቀን 2010 ዓ.ም ይገባል ። ታማኝ በየነ "አንድ ሕዝብ ፣አንድ ኢትዮጵያ " በማለት ባለፉቱ 28 ዓመታት ብሔር ፣ ሐይማኖት ፣ቋንቋ እና ቦታ ሣይገድበው ስለ-ኢትዮጵያዊያን እና ስለ-ሚወዳት እናት ሃገሩ ኢትዮጵያ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል 
ሙሉ ጊዜውን የሰጠ ምርጥ የኢትዮጵያ ልጅ ነው። ስለ-ታማኝ ይህ ከላይ የተገለጸው መልካም ተግባር ከውቅያኖስ በማንኪያ እንደመጨለፍ የሚቆጠር እንጂ የእርሱን በጎ ተግባር ሙሉ በሙሉ የሚገልጽ አይደለም ። ይህ ሀቅ እንዳለ ሆኖ የአርቲስት፣ አክቲቪስትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነ ወደ እናት ሃገሩ ሲገባ የሚደረገለት አቀባበል በመልካም ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል
ለረጅም ዓመታት አንድነትን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን እና መተሳሰብን ሲሰብክ የኖረ፣ አንድ ህዝብ አንዲት ኢትዮጵያ የሚል አቋም ያለዉ እና ብሔር ሃይማኖት ሳይለይ ለኢትዮጵያ ህዝብ የታገለ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ለመቀበል ፤ 1ኛ. ረ/ፕ ነብዩ ባዬ፣ 2ኛ. ሀብታሙብ አዱኛ ፣3ኛ. አርቲስት ዳዊት ይፍሩ ፣ 4ኛ. አቶ ይልማ ይፍሩ ፣ 5ኛ. አርቲስትና ጋዜጠኛ ሠይፉ ፋንታሁን ፣ 6ኛ. አቶ የሺዋስ አስፋ ፣ 7ኛ. ኮሜዲያን ደረጃ ሀይሌ ፣ 8ኛ. ድምፃዊ አረጋኸኝ ወራሽ ፣ 9ኛ. አቶ ይድነቃቸው ከበደ ፣ 10ኛ. አቶ ፋአድ ሰማን ፣ 11ኛ. አርቲስት አብርሃም ወልዴ ፣ 12ኛ. ድምፃዊ ታደለ ሮባ፤ የአቀባበሉ ዐብይ የኮሚቴ አባላት መካከል ሲሆኑ፤ ሌሎችም ንዑስ ኮሚቴ አባላት በታላቁ ሰው የአቀባበል ሥነ-ስርዓት ስራዎችን የሚያከናውኑ የኮሚቴ አባላት ተዋቅረው ስራዎችን እያከናወኑ ይገኛሉ። የአርቲስት ፣ የአክቲቪስ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የታማኝ በየነን አቀባበል ለማስተባበር በዋነኛነት ይህ ከላይ የተገለጸው ኮሚቴ ነሐሴ 26 እና 27 በሚከናወነው መርሐ ግብር ላይ በዋነኛነት ስራውን ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ነው።
.
(ይድነቃቸው ከበደ)

Image may contain: one or more people, people on stage and people standing


የአግ7 አርበኛ ታጋዩች ትጥቃቸውን አይፈቱም፤ ከነሙሉ ትጥቃቸው ይገባሉ።

ስለ አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ፅኑወች አርበኛ ታጋዩች የመጀመሪያ ዙር ወደ ሀገር ቤት አገባብ እና አቀባበል ሁኔታ በቅንጭቡ ፦
፩ኛ. ከኤርትራ የተለያዩ ካምፕች ከ300 በላይ ታጋይ አርበኞች ከነሙሉ ትጥቃቸው ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ።
፪ኛ. በአማራ ክልል በ3 የማሰልጠኛ ጣቢያወች የሰለጠኑ ፣ እንዲሁም ንቅናቄው በጎበዝ አለቆች አደራጂቶ አስፈላጊውን የትጥቅ፣ የስንቅ አቅርቦት እያሟላ በተለያዩ አካባቢወች የህወሓትን ቡድን መፈናፈኛ አሳጥተው የነበሩ ከ5ሺ በላይ አርበኛ ታጋዩች ከነሙሉ ትጥቃቸው ይቀላቀላሉ።
፫ኛ. ሁለት ከተሞች ጎንደር እና ባህርዳር የአቀባበል መረሀ ግብሮች ተዘጋጂተዋል በጊዜያዊነት ከክልሉ የለውጥ ሃይል ጋር በመወያየት በተዘጋጀ ስፍራ ይሰፍራሉ። ዘላቂው ካምፕ ሙሉ በሙሉ እስኪዘጋጂ ድረስ።
፬ኛ. ሲገቡ በፀረ ለውጥ ሀይሉ የደህንነት ስጋት እንዳይፈጠር ከሀገር መከላከያ እና ከፀጥታ ሃይሉ ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
፭ኛ. የአግ7 አርበኛ ታጋዩች ትጥቃቸውን አይፈቱም፤ ከነሙሉ ትጥቃቸው ይገባሉ። ከገቡም በኃላ የእራሳቸው ህጋዊ ሰርተፍኬት ይሰጣቸዋል።ከካምፕ ውጭ ወደ ቤተሰብ ቢያቀኑ እንኳ ትጥቃቸውን ይዘው መሄድ ይችላሉ።
፮ኛ. በነፃነት ትግሉ በእስር ፣ በአካል መጉደል ፣ በቤተሰብ መበተን ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ለተጋለጡ አርበኛ ታጋዩች የንቅናቄው አባላት ለአመታት የሚቆይ በሚፈልጉት የሙያ መስክ ብቁ የሚያደርግ እና የሚያቋቁም ትልቅ ፕሮጀክት ተቀርፆ ወደ ስራ ተግብቷል።
፯ኛ. በመላ ሀገሪቱ ለአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ አባሎቹ ወደ ካምፕ የሚገቡ ከ6 በላይ ካምፕች ቦታ መረጣና ወታደራዊ ጥናት እየተካሄደባቸው ይገኛል።4ቱ ወይም 5ቱ በአማራ ክልል ይሆናሉ።
በፅኑ ኢትዮጵያዊነት ከህብረ ብሄራዊው የአርበኞች ግንቦት 7 ሃይል ጋር ወደ ፊት !!
ኢትዮጵያን እና ህዝቧን እግዚአብሔር ይባርክ ይቀድስም!!

Friday, August 24, 2018

Ethiopian lady looted and deposited billions in a bank in Germany





በከፍተኛ የሙስና ወንጀል የሚታሙት ፤ የመብራት ሀይል ሹመታቸውን ተከትሎ ቢሊዮኖችን በጀርመን ባንኮች ያከማቹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ ከሀላፊነታቸው ተነሱ።

የፋይላችን መረጃ የአሜሪካ ባለስልጣን የነበሩትን ያማማቶን ዋቢ አድርጎ እንደሚጠቁመው ከደሃው የኢትዮጲያ ህዝብ ላይ የተዘረፈው ብር በአንደኛ ደረጃ የሚገኘው በጀርመን ሀገር እንደሆነ ....... ከሚታወቁት ቱባ-ቱባ የህወሓት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት በላይ ኤልክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ዋና ሃላፊ የሆነችዋ ሴትዮ $180,000,000 ዶላር በውጪ ሀገር ባንክ ማስቀመጧ ሁሉም አስገርሟል፡፡ ይህቺ ጀማሪ ባለስልጣን 180 ሚሊዮን ዶላር ከዘረፈች ነባሮቹ ምን ያህል እንደሚዘርፉ መገመት ይቻላል፡፡


ሡዳን ጌታቸው አሰፋን አሳልፋ ላለመስጠት እያንገራገረች ነው



ሡዳን ጌታቸው አሰፋን አሳልፋ ላለመስጠት እያንገራገረች መሆኑን እጅግ የታመነ የሊክድ ኒውስ ምንጮቻችን አሳውቀውናል፡፡




ጌታቸው አሰፋ አገር እየቆረሰ ጉርብትና ባፈራው ወዳጅነት ሱዳኖች አሳልፎ ላለመስጠት እያንገራገሩ ነው። ለኢትዮጲያ መንግስት ተላልፎ እንዲሰጥ መንግስት በከፍተኛ ንግግር ላይ ነው፡፡
የሱዳን መንግስትና ወያኔ በአንድ በኩል የኢትዮያ መንግስት በሌላ ሆነው ስጥ፣ አልስጥም የጦፈ ክርክር ላይ ናቸው። አሁን ላይ ሱዳኖች አሳልፈው እንደሚሰጡ ቃል እየገቡ ነው።

አፈትላኪ ዜናዎች ጌታቸው አሰፋን መፈርጠጡን በግምባር ቀደምትነት ያረጋገጠች ሲሆን አንዳንድ ተልካሻዎች ጌታቸው አሰፋ አዲስ አበባ ነው ብለው የሚያወሩት ፍፁም ሀሰት መሆኑን ልናረጋግጥና
እንኳን አዲሳባ ሊመጣ ከስልጣኑ እንደተነሳ ኦፊሱን ቆልፎ ነው ተደብቆ ወደ መቀሌ የሸሸው።

ከወራት ቆይታ በኋላ በቅርቡ ወደ ሱዳን መሸሹን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በቅርቡም ሴክሬታሪው እቃ ይዛ ወደ መቀሌ ልታመልጥ ስትል ተይዛለች በነገራችን ላይ ብዙ ጉድ አለ እንዲወጣ የሀገሬ ህዝብ እንዲያውቀው እየታገልኩ ነው፡፡ ጌታቸው እንደውቅያኖስ የሰፋ ግፍ አገራችን ላይ ሲፈጽም የነበረ ነው ጠብቁ እንዳንድ ነገሮች ይኖራሉ..!!አባኮስትር በላይ

ፍትህ የጌታቸው አሰፋ ሰለባ ለሆነችው አገራችን!
Image may contain: 1 person, text

ሰበር ዜና : አቶ በረከት ስምዖን እና ታደሰ ጥንቅሹ ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሜቴ ታገዱ::

ሰበር ዜና :
አቶ በረከት ስምዖን እና ታደሰ ጥንቅሹ ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሜቴ ታገዱ::
Image may contain: 2 people, people sitting

ሶማሊ ላንድ ሲያመልጡ የነበሩ ሁለት የኢትዮጵያ ባልስልጣናትን ይዛ አሰረች።


ሶማሊ ላንድ ሲያመልጡ የነበሩ ሁለት የ ኢትዮጵያ ባልስልጣናትን ይዛ አሰረች።
 ሀልቤግ የተሰኘው የሀገሪቱ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው፣ የሶማሊላንድ የደህንነት ባለስልጣናት ሀርጌሳ ውሰጥ ነው ሁለት የአብዲ ኢሌይ የካቢኔ አባላትን ይዘው ያሰሩት።
የታሰሩት ባለስልጣናት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ የነበሩት ኢብራሂም አድም ማሃድ እና የፍትህ ቢሮ ሃላፊው አብዲልማጅድ አህመድ ጃማ ናቸው።
ባለስልጣናቱ የተያዙት፤የክልሉ ርእስ መስተዳድር አቶ አብዲ ኢሌይ ከስልጣን መነሳታቸውን ተከትሎ ከጅጅጋ ሲያመልጡ ነው። ሹመኞቹ ከጅግጅጋ ውድ ሶማሊ ላንድ መዲና ወደ ሀርጌሳ በማቅናት ላለፈው ሳምንት እዚያው መቆየታቸው ታወቆአል።
የሶማሊላንድ የኢሚግሬሽንና የደህንነት ዲፓርትመንት ሀላፊ ታይፕ ኦስማን ለሀልቤግ የዜና አገልግሎት ሲናገሩ ባለስልጣናቱ በኢልጋ አውሮፕላን ማረፊያ በህገ ወጥ መንገድ በመግባታቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል ብለዋል።
የባለስልጣናቱ አላማ ወደ ሞቃዲሾ ለመሄድ እንደነበር የጠቀሱት ሚሰተር ኦስማን፤ ሆኖም ሁለቱም ምንም አይነት ህጋዊ የጉዞ ሰነድ እንደሌላቸው አመልክተዋል።No automatic alt text available.

ጀርመን ውስጥ 1.6 ሚሊዮን ክፍት የስራ ቦታዎች አሉ

አዲሱ የጀርመን የፍልሰት ጉዳይ ረቂቅ ህግ 

በአዲሱ ህግ  ጀርመን ውስጥ በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ የውጭ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ገብተው መሥራት የሚያስችሏቸው መስፈርቶች ተቀምጠዋል። የትምህርት ደረጃ፣ እድሜ፣ የቋንቋ ችሎታ፣ የተጨበጠ የሥራ እድል እና ኑሮን በራስ የመምራት አቅም ጀርመን ለሥራ የሚመጡ የውጭ ዜጎች የሚመረጡባቸው መስፈርቶች ናቸው።
    
አውዲዮውን ያዳምጡ።11:14

አዲሱ የጀርመን የፍልሰት ጉዳይ ረቂቅ ህግ

የሰለጠነ የሰው ኃይል ከውጭ ወደ ጀርመን በቀላሉ እንዲገባ ያስችላል የተባለው አዲሱ የጀርመን የፈላስያን ጉዳይ ህግ ዕውን ሊሆን የተቃረበ ይመስላል። ጀርመን ውስጥ በአንዳንድ የሞያ መስኮች በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት አለ። በተለይ የመሀንዲሶች፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሙያተኞች እና የጤና ባለሞያዎች እጥረት ከፍተኛ ነው።  የኤኮኖሚ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት  እንዳስቀመጠው 1.6 ሚሊዮን ክፍት የስራ ቦታዎች አሉ። በተለያዩ የሙያ መስኮች የሚታየውን ጉድለት ለመሙላት በመፍትሄነት ከሚቀርቡት ውስጥ ከውጭ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማስገባት አንዱ ነው። ይህም ከ20 ዓመታት በላይ ሲያነጋግር ሲያከራክር እና ሲያወዛግብ የቆየ ጉዳይ ነው። ከአከራካሪዎቹ ጉዳዮች ውስጥ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል ከውጭ ይግባ ፣የለም ጀርመን ያሉ ስራ አጦችን ችግሩ ባየለባቸው ዘርፎች በማሰልጠን ለመተካት ጥረት ይደረግ የሚሉ እና የመሳሰሉት ይገኙበታል። ከዚሁ ጋርም የሀገሪቱ የፍልሰት ጉዳይ ህግ የውጭ ዜጎችን በተለይም በልዩ ክህሎታቸው የሚፈለጉትን ባለሞያዎች የሚማርክ አለመሆኑ ችግሩ እንዳይፈታ እንቅፋት ሆኖ መዝለቁ ነው የሚነገረው። የጀርመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በሙያቸው የሚፈለጉ የውጭ ዜጎች በቀላሉ ጀርመን ገብተው እንዲሰሩ ያስችላል የተባለ  አዲስ ህግ በቅርቡ አርቅቋል። የጀርመን ሥራ ሚኒስቴር እና የኤኮኖሚ ሚኒስቴር የተስማሙበት ይህ
Deutschland ausländische Experten (picture-alliance/dpa)
ረቂቅ ከአንድ ሳምንት በኋላ ለጀርመን ካቢኔ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ረቂቅ ህግ እንደሚጠቁመው የችግሩ መንስኤ በሀገሪቱ ሥራ አጥነት መቀነሱ እና ከወጣቱ ይልቅ በእድሜ የገፋው ህዝብ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ነው። በዚህ የተነሳም የጀርመን ኩባንያዎች የሰው ኃይል እጥረት ባለባቸው የስራ መስኮች ሙያተኞችን ለማግኘት ለሌሎች የአውሮጳ ህብረት አባል ሀገራት ዜጎች የበለጠውን እድል ሲሰጡ ቢቆዩም የሚፈልጉትን ሙያተኛ ማግኘት አለመቻላቸው በረቂቁ ተገልጿል። እናም ጀርመን ከአውሮጳ ህብረት ውጭ ከሦስተኛው ዓለም ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠኑ ሙያተኞችን ማስገባት የግድ ይላታል በረቂቁ እንደሰፈረው። ሀገሪቱ የዛሬ 3 ዓመት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን  ስትቀበል  የሞያተኞች እጥረት በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ይቀንሳል የሚል ግምት ነበር። ሆኖም በጀርመኑ የኤኮኖሚ ትብብር እና የልማት ድርጅት የፍልሰት ጉዳዮች ተመራማሪ ቶማስ ሊቢሽ እንደሚሉት ይህ ተስፋ እንደተደረገው መፍትሄ ሊሆን አልቻለም። ሊቢሽ ለዶቼቬለ በሰጡት አስተያየት ስደተኞች በብዛት መግባታቸው ጥቅም ነበረው። ግን ያኔ ወደ ጀርመን የገባው ስደተኛ ግን እዚህ ያለውን የሥራ ገበያ የሚመጥን አልነበረም።
« ስደተኞች መግባታቸው በተወሰነ ደረጃ ረድቷል። ሆኖም አብዛኛዎቹ ክህሎታቸው ዝቅተኛ ነው። ለምሳሌ በኢንዱስትሪው እና በጤና ዘርፍ ሙያተኞች የሆኑ ሰዎች ይመጣሉ። ሆኖም
Deutschland ausländische Experten (picture-alliance/dpa)
ለሥራው የሚፈልገው አቅም የሌላቸው  ወይም የሥራ ገበያው የማይፈልጋቸው ናቸው። ከ2 ከ3 ዓመት በፉት የገቡት ስደተኞች ተስፋ እእንዳደረግነው ሆነው አላገኘናቸውም።»
በአዲሱ ህግ  ጀርመን ውስጥ በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ የውጭ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ገብተው መሥራት የሚያስችሏቸው መስፈርቶች ተቀምጠዋል። የትምህርት ደረጃ፣ እድሜ፣ የቋንቋ ችሎታ፣ የተጨበጠ የሥራ እድል እና ኑሮን በራስ የመምራት አቅም ጀርመን ለሥራ የሚመጡ የውጭ ዜጎች የሚመረጡባቸው መስፈርቶች ናቸው። የውጭ ዜጎች ለነዚህ መስፈርቶች የተቀመጠውን ነጥብ ካሟሉ ጀርመን መግባት ይፈቀድላቸዋል። የፖለቲካ ሳይንስ እና የህግ ምሁሩ ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ  ከከዚህ ቀደሞቹ መመዘኛዎች ተፈላጊ ሙያተኞችን የሚስቡ አልነበሩም ይላሉ። በዚህ የተነሳም ችግሩን መፍታት አለመቻሉን ያስረዳሉ። ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ጋር እያነጻጸሩ ስለ አዲሱ ረቂቅ ህግ በሰጡት አስተያየት  በውስጡ የተቀመጡት መስፈርቶች የውጭ ዜጎችን መማረክ መቻላቸው ያጠራጥራል ይላሉ ዶክተር ለማ ።
ጀርመን የውጭ ዜጎችን ለሥራ እየመለመለች ወደ ሀገርዋ ማስገባት የጀመረችው ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ነው። ያኔ የሀገሪቱ ኩባንያዎች ሠራተኞች በእጅጉ ያስፈልጓቸው ነበር። በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር በ1950 ዎቹ እና 60ዎቹ በጦርነቱ የወደመውን መልሶ ለመገንባት የሚያስፈልግ የሰው ኃይል በርካሽ ጉልበት ጀርመን ገባ።  በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች ከኢጣልያ፣ ከግሪክ እና ከቱርክ  «እንግዳ ሠራተኞች» እየተባሉ መጥተው በሀገሪቱ የኤኮኖሚ ተዐምር ማምጣት ተቻለ። ከዚያን ወዲህ የውጭ ዜጎችን የሚመለከተው የጀርመን ህግ እንዳወዛገበ
Symbolbild Flüchtlinge als Fachkräfte (picture-alliance/dpa/S. Hoppe)
ነው። ለሥራ የመጡ የውጭ ዜጎች ሥራቸው ሲያበቃ ወደ ሀገራቸው ከመመለስ ይልቅ በተለያዩ ምክንያቶች ጀርመን መቅረታቸው ከሚያወዛግቡት ጉዳዮች  አንዱ ሆኖ ዘልቋል። በነዚህ ውዝግቦች መንስኤ የፌደራል መንግሥቱ በጎርጎሮሳዊው 1973 የውጭ ዜጎችን ለሥራ መመልመልን አስቁሞ ነበር። በ2000 ዓም መንግሥትን ይመራ የነበረው የሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ይህን እገዳ አንስቶ በተለይ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በምህጻሩ የአይ.ቲ ባለሞያዎች በአሜሪካኑ ግሪን ካርድ አምሳያ ጀርመን እንዲገቡ ተደረጓል። ከዚያን ጊዜ አንስቶም የፖለቲካው ትኩረት በሥራ ወደ ጀርመን የሚገቡ ስደተኞች እና አጠቃላዪ የፍልሰት ጉዳይ ሆነ። ጀርመንን አሁን የሚመራው የእህትማማቾቹ የክርስቲያን ዴሞክራት ህብረት እና የክርስቲያን ሶሻል ህብረት ፓርቲዎች እንዲሁም የሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ተጣማሪ መንግሥት በዚህ ዓመት በየካቲት ወር ሲመሰረት አንድ የፍልሰት ጉዳይ  ህግ ለማውጣት ተስማምቶ ነበር ። በዚሁ መሠረት የተዘጋጀው አዲሱ ሰነድ በጀርመን ምጣኔ ሀብት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል ችግር በአግባቡ እና በግልጽ አሰራር መፍትሄ ሊፈለግለት እንደሚገባ ተጠቅሷል። ከዚህ ቀደም የተቀመጡ አንዳንድ ገደቦችን ማንሳት አስፈላጊ እንደሆነ ይገልጻል። ለዓመታት ለዘለቀው ችግር መፍትሄ ያስገኛሉ የተባሉ ሌሎች ህጎችም ወጥተው ነበር። አሁን ሌላ አዲስ ህግ ያስፈለገው የፍልሰት ጉዳዮች ተመራማሪው ሊቢሽ እንደሚያስረዱት የቀደሙት መሻሻል ስላለባቸው ነው።
«ከህዝብ ቁጥር ጋር በተያያዘ ምክንያት ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል። በሚቀጥለው ዓመት ብዙ ሰዎች በጡረታ ይሰናበታሉ። እነርሱን የሚተካ በቂ ወጣት የለም። ስለዚህ ከቀድሞው የበለጠ የሠራተኛ ኃይል ያስፈልገናል። እነዚህ ማሻሻያዎች ስለሚያስፈልጉን ጥሩ እና የፍልሰተኞች ጉዳይ ህግ ያስፈልገናል።»
Symbolbild Industriearbeiter (picture-alliance/PhotoAlto)
በእስከዛሬው ህግ በማንኛውም ሥራ ቅድሚያ የሚሰጠው ለሀገር ውስጥ አመላካቾች ነበር። ሠራተኞችም ከውጭ የሚገባ የሰው ኃይል ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ በሆነባቸው ሥራዎች ብቻ ነበር የሚፈለጉት ። የሚገቡትም ሥራ ካገኙ በኋላ ነበር ይሁን እና  የሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ SPD አሁን ይህን የሚቀይር ሃሳብ ይዞ ነው የቀረበው። ወደፊት የውጭ ዜጎች ሥራ ሳያገኙም ለሥራ ፍለጋ ጀርመን መምጣት ይችላሉ። ሥራ መፈለጊያ የ6 ወራት ጊዜ ይሰጣቸዋል ተብሏል። በዶክተር ለማ እምነት ይህም የውጭ ዜጋ ሞያተኞች ጀርመን ለሥራ ፍለጋ እንዲመጡ የሚያበረታታ አይመስላቸውም። በአሁኑ ጊዜ ጀርመን በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠኑ ባለሞያዎች እጥረት ብቻ አይደለም ያለባት። መካከለኛ በሚባል ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል ችግርም ሰንጎ ይዟታል። የነርሶች፣ የበሽተኛ ተንከባካቢዎች፣ የመዋዕለ ህጻናት ረዳቶች ከእጅ ሞያ ዘርፍ ደግሞ ፣የኤሌክትሪክ ባለሞያዎች እና የአናጢዎች አጥረት አለ ። በእነዚህና በመሳሰሉት ዘርፎች ሙያተኞችን ከሦስተኛው ዓለምም ጭምር ለማስገባት የሚደረገው ሙከራ የሁሉንም ፖለቲከኞች ይሁንታ አላገኘም። ቀኝ ጽንፈኛው አማራጭ ለጀርመን የተባለው ፓርቲ  ረቂቁ  ለፍልሰት የተከፈተ የጓሮ በር ነው ሲል ይቃወማል። ከሁሉ በተለየ የግራዎቹ ፓርቲ ይህን መሰሉ አሠራር በሌሎች ሀገራት የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ይፈጥራል ሲል ስጋቱን ይገልጻል። አሠሪዎች ግን የሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት እድገት እንዳይደናቀፍ ችግሩን መፍታት ጊዜ ሊሰጠው የሚገባ አይደለም ሲሉ አጥብቀው ይከራከራሉ። 
ኂሩት መለሰ 
ነጋሽ መሐመድ

Tuesday, August 21, 2018

ኢሳት-የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ በመግባት በሰላማዊ መንገድ ትግሉ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ደረሱ


 የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገለጸ።
በፕሬዝዳንቱ የሚመራው የልኡካን ቡድን ወደ አማራ ክልል እንደሚመጣ የአማራ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ናቸው።
በአስመራ ቆይታ ያደረገው የአማራ ክልል የልኡካን ቡድን ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ አመራሮች ጋር መወያቱ ታውቋል።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል የሚያደርጉት ጉብኝት መቼና በምን ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር እንደሚሆን ግን በዝርዝር አልተገለጸም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ41 አመት በኋላ ወደ ሞቃዲሾ በረራ ሊጀምር ነው ተብሏል።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንደገለጹት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ አማራ ክልል በመምጣት ጉብኝት እንዲያደርጉ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የሕዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲና ፍትህ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ልዩ አማካሪ ከሆኑት ከአቶ የማነ ገብረአብ ጋር ውይይት መደረጉን የጠቀሱት አቶ ንጉሱ ጥላሁን በአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራ የልዑካን ቡድን ወደ አማራ ክልል እንዲመጣ መስማማታቸውን ገልጸዋል።
ጉብኝቱ መቼና በምን ጉዳይ ላይ እንደሚያተኩር ግን ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
አቶ ኢሳያስ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ለ20 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በአዲስ መልክ ከተጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ የአማራ ክልሉ ለሁለተኛ ጊዜ ሆኖ ይመዘገባል።
የአማራ ክልል ልዩ የልዑካን ቡድንም ወደ ኤርትራ በቅርቡ እንደሚያመራ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገልጸዋል።
አቶ ንጉሱ ሰሞኑን የክልላቸውን መንግስት ወክለው አንድ የልዑካን ቡድን በመምራት አስመራ ቆይታ ማድረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል።
በዚህን ወቅት በኤርትራ ብረት አንስቶ እየታገለ ከሚገኘው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ጋር መወያያቱ ተገልጿል።
ንቅናቄው ወደ ሀገር ቤት በመግባት በሰላማዊ መንገድ ትግሉ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ መደረሱንም አቶ ንጉሱ ጥላሁን አስታውቀዋል።
በኤርትራ ቆይታ ወቅት ከሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ምክክር መደረጉን የጠቀሱት አቶ ንጉሱ ጥላሁን በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት መደረጉም ተመልክቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ በረራ ሊጀመር መሆኑ ተገልጿል።
ወደ ሞቃዲሾ የሚደረገው በረራ ከ41 ዓመታት በኋላ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በሳምንት ሶስት ጊዜ እንደሚደረግም ለማወቅ ተችሏል።
ከሶማሊያ ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት በጅቡቲና በናይሮቢ ሲደረግ የነበረውን በረራ የሚያስቀረው የሞቃዲሾው አዲሱ መስመር መቼ እንደሚጀመር ግን የተገለጸ ነገር የለም።

በኢትዮጵያ እና ኤርትራ እርቅ ዙሪያ የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች ሚና ጉልህ ድርሻ እንደነበረው የንቅናቄው ዋና ጸሀፊ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ገለጹ።


በኢትዮጵያ እና ኤርትራ እርቅ ዙሪያ የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች ሚና ጉልህ ድርሻ እንደነበረው የንቅናቄው ዋና ጸሀፊ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ገለጹ።
( ኢሳት ዜና ነሐሴ 14 ቀን 2010 ዓ/ም ) አቶ አንዳርጋቸው ይህን የገለሱት በዋሽንግተን ዲሲ በተደረገ ታላቅ ስብሰባ ላይ የኤርትራ መንግስት የነጻነት ትግሉን በማገዝ በኩል ላደረገው ድጋፍና ውለታ ምስጋና ባቀረቡበት ጊዜ ነው።
አንዳንድ ወገኖች ኤርትራና ኢትዮጵያ ከ20 ዓመታት በኋላ ወደ እርቅ የመጡት በውጭ ኃይሎች ተጽዕኖ እንደሆነ መላምት ሢሰነዝሩ ቢደመጡም፤ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ግን ሀገራቱ ወደ እርቅና ፍቅር የመጡት ያለ አንድም የውጭ ኃይላት ሸምጋይ እንደሆነ አስረግጠው ተናግረዋል።
ይልቁንም የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ በዚህ ረገድ ገንቢ ሚና መጫዎቱን የጠቀሱት አቶ አንዳርጋቸው፣”ንቅናቄያችን በወቅቱ የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በኤርትራ መንግስት አመኔታን ያተረፈ ነው” ብለዋል።
በርካታ የንቅናቄው ደጋፊዎች በታደሙበት በዲሲው ስብሰባ ታጋይ አንዳርጋቸው የተለያዩ ሽልማቶች የተበረከቱላቸው ሲሆን፣ ዝግጅቱ ላይ ለጨረታ የቀረበውን የገዛኸኝ ነብሮብን ምስል የባልቲሞር ወጣቶች አሸንፈዋል።
አቶ አንዳርጋቸው ቀደም ሲል በሌላ ከተማ በተሰናዳ ተመሣሳይ መድረክ በእስር ቤት ሳሉ የተወሰዱባቸውን የመጽሀፍ ረቂቅ ሶፍት ኮፒ ዶክተር አብይ አሕመድ እንደላኩላቸው፣ በየመን ሰንዓ ሲታገቱ የተወሰደውንም 4 ሺህ ዶላር እንደመለሱላቸው በማውሳት፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተለዬ ክብርና አድናቆት እንዳላቸው መግለጻቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ቅናቄ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ኢየሩሳሌም ሆቴል የተሳካስብሰባ አድርጓል።
የፋኖ፣ የቄሮ እና የዘርማ ተወካዮችን ጨምሮ ከየክፍለ ከተማው የተውጣጡ በርካታ ወጣቶች በተገኙበት በዚህ ስብሰባ ላይ በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡትን የንቅናቄውን አመራሮች በልዩ ድምቀት መቀበል በሚቻልበት ሁኔታ እና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ሰፊ ውይይት መካሄዱ ታውቋል።

Monday, August 20, 2018

ኢሳት ዜና : ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከስልጣን ከተነሱ አሜሪካ የኢኮኖሚ አደጋ ያጋጥማታል አሉ


ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከስልጣን ከተነሱ አሜሪካ የኢኮኖሚ አደጋ ያጋጥማታል አሉ
 ፕሬዚዳንቱ ከፎክስ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እርሳቸውን ከስልጣን ለማንሳት ሙከራ የሚደረግ ከሆነ የአገሪቱ ኢኮኖሚ አደጋ ውስጥ ሊወድቅ ይችላል። ፕሬዚዳንቱ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ለሁለት ሴቶች ገንዘብ መክፈላቸውንም የቀድሞው ጠበቃቸውና ጉዳይ አስፈጻሚያቸው ሚካኤል ኮኸን ካጋለጡ በሁዋላ ነው። ፕሬዚዳንቱ በጠበቃቸው አማካኝነት የከፈሉት ገንዘብ ከሁለቱ ሴቶች ጋር ከፈጸሙት ወሲብ ጋር የሚገናኝ ሲሆን፣ ይህ ይፋ እንዳይሆንባቸውም የአፍ ማዘጊያ ገንዘብ እንዲከፈል ማዘዛቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል።
ከፍተኛ የህግ ፈተና የገጠማቸው ፕሬዚዳንቱ ፣ ከስልጣን እንዲወርዱ ግፊት እየመጣባቸው ሲሆን፣ እርሳቸው ግን ከስልጣን የሚወርዱ ከሆነ በአገሪቱ ላይ ከፍተና የኢኮኖሚ ቀውስ እንዲመከሰት በማስጠንቀቅ ስልጣናቸውን ለማቆየት እየታገሉ ነው።
ዋነኛ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው የሆኑት የዲሞክራቲክ ፓርቲክ ፓርቲ ፖለቲከኞች ከመጪው ህዳር ወር አጋማሽ ምርጫ ወዲህ ፣ ፕሬዚዳንቱን የመክሰስ ፍላጎት እንደሌላቸው እየተዘገበ ነው። ፕሬዚዳንት ትራምም ብቸኛ ተስፋቸው የፓርልማና የህግ መወሰኛ ምክር ቤቶችን ተቆጣጥረው የያዙት የረብሊካኖች ሲሆኑ፣ እነዚህን ሁለት የስልጣን ቦታዎች በዲሞክራቶች ላለመነጠቅ ከፍተኛ ቀስቀሳ እያደረጉ ነው።
ከምርጫው ማግስት ዲሞክራቶች በሁለቱም የምክር ቤት ወንበሮች አብላጫ ድምጽ የሚያገኙ ከሆነ፣ ትራምፕን ከስልጣን ለማንሳት ከፍተኛ እድል ይኖራል። ከፍተኛ የሪፐብሊካን ድጋፍ ያላቸው ፕሬዚዳንቱን ከስልጣን ማውረድ ቀላል እንደማይሆን ብዙዎች ይስማማሉ።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በምርጫው ወቅት ከሩስያ ጋር በማበር ተፎካካሪያቸው ሄላሪ ክሊንተን እንዲሸነፉ አድርገዋል በሚል የተጀመረው ምርመራ እስካሁን አልተጠናቀቀም። በዚህ የምርመራ ውጤት ፕሬዚዳንቱ ጥፋተኛ ከሆኑ፣ የራሳቸው ፓርቲ አባላት ሳይቀሩ ድጋፋቸውን ሊነሱዋቸው የሚችሉበት አጋጣሚ ከፍተኛ ይሆናል ተብሎ ይገመታል።

የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ አዛዥ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው


የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ አዛዥ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው
 ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓም በመስቀል አደባባይ ላይ በደረሰው ፍንዳታ በመምራትና በማስተባበር እጃቸው አለበት የተባሉት የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ አዛዥ ጌታቸው ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የምርምራ ጊዜ በተጠየቀባቸው መሰረት ፍርድ ቤት የ2 ሳምንታት የቀጠሮ ጊዜ ሰጥቷል።
የተጠርጣሪው ጠበቆች ግለሰቡ ከተያዘ 43 ቀናት ያለፈው በመሆኑ የዋስ መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ ተከራክረዋል። ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጉዳዩ ከግድያ እና ሽብር ተግባር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ተጨማሪ የምርምራ ጊዜ እንደሚያስፈልግ ወስኗል።
በሰኔው የቦንብ ጥቃት እጃቸው አለበት በሚል ተይዘው በእስር ላይ የነበሩት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አባል ኮማንደር ገብረ ኪዳን አሰግዶም፣ ኮማንደር ገብረ ሥላሴ ተፈራ፣ ኮማንደር ግርማይ በርሄ፣ ኮማንደር አንተነህ ዘነበ፣ ምክትል ኮማንደር አባቡ ዳምጤ፣ ምክትል ኮማንደር አብዲሳ ጋዲሳና ምክትል ኮማንደር ጫኔ ጠቋሬ ፣ ምክትል ኢንስፔክተር ሀገሬ ቀኔሳ፣ ዋና ሳጅን ድራር ታረቀኝና ዋና ሳጅን ከድር ዓሊ ከ15 እስከ 6 ሺ ብር በሚደርስ ዋስ መለቀቃቸው ይታወቃል

ስደተኞችን የሚረዳ የኢትዮጵያውያን ማህበር በኑርንበርግ


ወደ ሥራው ከመግባታቸው በፊት በጀርመን ህግ መሠረት አስፈላጊ የሆነውን ሥልጠና መውሰዳቸውን የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አህመድ ሲራጅ ይናገራሉ። አቶ አህመድ እንዳሉት ይህን ስልጠና መውሰዳቸው በአካባቢያቸው በሚገኝ ትልቁ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ በኤድስ ላይ ያተኮረ የምክር አገልግሎት መስጠት አስችሏቸዋል። 
    
አውዲዮውን ያዳምጡ።11:57

ስደተኞችን የሚረዳ የኢትዮጵያውያን ማህበር

መጠሪያው «የህብረት ክንድ በኤድስ ላይ» ይባላል። በደቡባዊ ጀርመንዋ ከተማ በኑርንበርግ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዛሬ 15 ዓመት ያቋቋሙት ማህበር ነው። 15 ሆነው ነበር የመሰረቱት። በኢትዮጵያ በኤድስ ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናትን የመርዳት ዓላማ ይዞ ነበር የተመሰረተው። ለማህበሩ ምሥረታ መነሻ  የሆናቸውም ከሀገር ቤት ይቀርብላቸው የነበሩ የእርዳታ ጥሪዎች እና የማህበሩ መስራቾች ኢትዮጵያ ሄደው ያዩት የችግሩ ስፋት እንደነበረ ያነጋገርኳቸው የማህበሩ መሥራቾች እና እስካሁንም ሥራውን በማከናወን ላይ የሚገኙት 3 የማህበሩ አመራሮች ተናግረዋል። ወደ ሥራው ከመግባታቸው በፊትም በጀርመን ህግ መሠረት አስፈላጊ የሆነውን ሥልጠና መውሰዳቸውን የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አህመድ ሲራጅ ይናገራሉ። አቶ አህመድ እንዳሉት ይህን ስልጠና መውሰዳቸው በአካባቢያቸው በሚገኝ ትልቁ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ስለ ኤድስ የምክር አገልግሎት መስጠት አስችሏቸዋል።
Gemeinsamer Arm Gegen Aids e.V. Preisverleihung (Gemeinsamer Arm Gegen Aids e.V.)
አቶ አህመድ ትልቁ የስደተኞች ካምፕ የሚሉት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችም የነበሩበትን በባየርን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር የሚገኘውን የሲሪንዶርፍ የስደተኞች መጠለያ ነው። እነ አቶ አህመድ ከኑርንበርግ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በዚህ መጠለያ ካዩዋቸው ችግሮች በመነሳት ለስደተኞች ተጨማሪ አገልግሎት መስጠት ቀጠሉ ።ወይዘሮ ገነት የማነ የማህበሩ መሥራች እና የገንዘብ ያዥ ናቸው።

 ጎርጎሮሳዊው 2014 በርካታ ስደተኞች ወደ ጀርመን መግባት የጀመሩበት ወቅት ነበር። እናም አቶ አህመድ እንዳስረዱት ያኔ ፈታኝ ወቅት ነበር ለማህበራቸው እና አባላቱ። ከዚያ በኋላ ለስደተኞች የሚሰጡት አገልግሎት በመጠንም በዓይነትም እየሰፋ ሄደ

አቶ ዮናስ ብዙነህ የማህበሩ ሊቀመንበር ናቸው። ጀርመን ከመጡ 24 ዓመት ሆኗቸዋል። ከዛሬ 15 ዓመት አንስቶ በዚህ ማህበር ውስጥ በንቃት ይሳተፋሉ። ከሁለት ሳምንት በፊት በአውሮጳ
Gemeinsamer Arm Gegen Aids e.V. Preisverleihung (Gemeinsamer Arm Gegen Aids e.V.)
እና ጀርመን ፕሮግራም ችግራቸውን የተናገሩ ደቡብ ጀርመን ጥገኝነት የጠየቁ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ብዙ ዓመት ጀርመን የቆዩ ኢትዮጵያውያን በአካባቢያቸው ቢኖሩም እንደማይረዷቸው ተናግረው ነበር። አቶ ዮናስ ማህበራቸው እና አባላቱ ግን ስደተኞችን ለመርዳት የበኩላቸውን ከማድረግ ወደ ኋላ እንዳላሉ ያስረዳሉ።
 
 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር በ2017 ሲርንዶርፍ ከተባለው የስደተኞች መጠለያ፣ከኑርንበርግ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደ ሚገኘው የሬግንስቡርግ ካምፕ ቢወሰዱም እነ አቶ አህመድ ርቀት ሳይገድባቸው ስደተኞችን መርዳት መቀጠላቸውን ገልጸዋል። «የህብረት ክንድ በኤድስ ላይ»በተባለው ማህበር ሦስቱ መሥራቾች በንቃት ሲሳተፉ ሌሎች አባላት ደግሞ የተለያዩ እገዛዎች ያደርጉላቸዋል። ይሁን እና በዚህን መሰሉ የግብረ ሰናይ ሥራ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት የሌላቸውም ኢትዮጵያውያንም አሉ። ምክንያታቸውን አናውቅም ይላሉ ወይዘሮ ገነት
«የህብረት ክንድ በኤድስ ላይ»የተባለው ኑርንበርግ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ማህበር አቶ ዮናስ እንደሚሉት ወደፊት ለስደተኞች እገዛ የሚያደርጉ ሌሎች አገልግሎቶች ላይ አትኩሮ የመስራት እቅድ አለው።
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

Sunday, August 19, 2018

አወዛጋቢው የስደተኞች ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል በባቫርያ


እቅዱን የተቀበሉት ጥቂት ፌደራል ግዛቶች ናቸው። ምሥራቃዊቷ ግዛት ዛክሰን በስርዋ በሚገኘው በድሬዝደን ከተማ መሰል ማዕከል ልታዘጋጅ ከመሆኑ ሌላ ከምዕራቦቹ ከሄሰን እና ከኖርድራይን ቬስት ፋለን ፌደራዊ ግዛቶች በስተቀር በእቅዱ የተማረኩ የሉም።
    
አውዲዮውን ያዳምጡ።09:48

የስደተኞች ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል

 
 
በደቡብ ጀርመንዋ በባቫርያ ፌደራዊ ግዛት አወዛጋቢዎቹ፣ የስደተኞች ጊዜያዊ ማቆያ የተባሉ 7ማዕከላት ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሥራ ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኽርስት ዜሆፈር ማዕከላቱ የተገን አሰጣጥ ሂደትን በአንድ ስፍራ ለማከናወን እና ለማፋጠን ይረዳሉ የሚል ተስፋ አላቸው። ተችዎች ግን ይህ ዓይነቱ አሠራር ችግሮችን ያባብሳል እንጂ አያስወግድም ሲሉ ይቃወማሉ። የነዚህ ማዕከላት ዓላማ በአጭሩ የተገን አሰጣጥ ሂደቶችን ማቀላጠፍ እና በአንድ ጣሪያ ስር ማከናወን መሆኑ ተገልጿል። ማዕከላቱ ከቀድሞው በተለየ ስደተኞችን መቀበያ፣ ጉዳያቸውን አይቶ መወሰኛ እና ተቀባይነት ያላገኙትን ማባረሪያ ይሆናሉ ተብሎ ነው የተነገረው። እያንዳንዳቸው እስከ 1500 ስደተኞች እና ፈላስያንን መያዝ በሚችሉት በእነዚህ ማዕከላት ካለፈው ረቡዕ አንስቶ የተገን አሰጣጥ ሂደት የሚመለከተው እያንዳንዱ መስሪያ ቤት እንደሚገኝ የባቫርያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአሂም ሄርማን በቅርቡ አስታውቀዋል። ማዕከሉ ባቫርያን የሚያስተዳድረው የወግ አጥባቂው የጀርመን ሶሻል ክርስቲያን ህብረት ፓርቲ ሊቀ መንበር እና የፌደራል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የኽርስት ዜሆፈር
Bayerisches Transitzentrum - mögliches Ankerzentrum (picture-alliance/dpa/S. Puchner)
 የጀርመን የስደተኞች ጉዳይ መሪ እቅድ ነው። ጉዳዩ መነሳት የጀመረው በመጋቢት ወር የመራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ፓርቲ ክርስቲያን ዴሞክራት ህብረት ሲዲዩ ከ እህት ፓርቲው ከክርስቲያን ሶሻል ህብረት ሲ ኤስ ዩ እና ከሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ጋር ጥምር መንግሥት ለመመስረት ከተስማሙ በኋላ ነው። ከዚህ በኋላ የሀገሪቱ የተገን አሰጣጥ ስርዓት በተለይም በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ተቀባይነት ያላገኙ ስደተኞች ጀርመን መግባት የለባቸውም የሚለው የዜሆፈር አቋም ከሜርክል ጋር አወዛግቧቸው ሥልጣን እለቃለሁ እስከማለት ደርሰው የጥምር መንግሥቱ መፍረስም አስግቶ ነበር። ይሁን እና ከቀናት ድርድር በኋላ መግባባት ላይ ተደርሶ ችግሩ ተወግዷል። ከስደተኞች ማቆያ ማዕከላቱ ጀርባ ያለው ሃሳብ ተገን ጠያቂዎች ጀርመን መቆየት መቻል አለመቻላቸው እስኪወሰን ድረስ በዚያ እንዲቆዩ  እና ጉዳያቸው ተቀባይነት ያላገኘ ስደተኞችን የማባረሩ ሂደት እንዲፋጠን ማድረግ ነው። ይህን አዲስ አሰራር ከ6 ወራት በኋላ የመገምገም እቅድ ተይዟል። ምዘናዎቹ ከተጠናቀቁ በኋላም የጀርመን ፌደራል መንግሥት ሁኔታዎችን የሚያመቻች ህግ ማዘጋጀት ይኖርበታል። ይህን ለማድረግም በ16 ቱ የጀርመን ፌደራል ግዛቶች ተቀባይነት ማግኘት አለበት።ይሁን እና እቅዱን የተቀበሉት ጥቂት ፌደራል ግዛቶች ናቸው። ምሥራቃዊቷ ግዛት ዛክሰን በስርዋ በሚገኘው በድሬዝደን ከተማ መሰል ማዕከል ልታዘጋጅ ከመሆኑ ሌላ ከምዕራቦቹ ከሄሰን እና ከኖርድራይን ቬስት ፋለን ፌደራዊ ግዛቶች በስተቀር በእቅዱ የተማረኩ የሉም። አብዛኛዎቹ ጊዚያዊ የማቆያ ማዕክላት እንዳይገነቡ እና
Bayerisches Transitzentrum - mögliches Ankerzentrum (picture-alliance/dpa/S. Puchner)
የዚህ የፖለቲካ መርህ አካል ላለመሆን ወሰነዋል። ከስደተኞች ማቆያ ማዕከሉ ግቦች አንዱ በተገን ጥያቄ ማመልከቻዎች ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎችን ማፋጠን ነው ቢባልም  ቨርነር ሺፋወር የተባሉት የጀርመን የፍልሰተኞች ጉዳይ ምክር ቤት ቦርድ ሊቀ መንበር ይህ ይሆናል ብለው አያምኑም። በርሳቸው አስተያየት ምንም እንኳን የተገን ጥያቄ ጉዳይ የሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች በሙሉ በነዚህ ማዕከላት ቢገኙም ሁሉም ነገር ይፋጠናል ብለው አያምኑም።
«ጥያቄው ከዚህ ጋር በተያያዘ የተገቡትን ቃሎች ማክበር ይቻላል ወይ ነው? ሊሆን የሚችለው ምንድን ነው? ግልጽ በሆኑ ጉዳዮች በተለየም በቀጥታ ከጦርነት ቀጠና የሚመጡ ሶሪያዎችን በሚመለከት ፣ሂደቱ በርግጠኝነት ይፋጠናል። ያን ያህል ሊለወጡ የማይችሉት ግልጽ ያልሆኑት ጉዳዮች ናቸው። እኔ እንደምለው ሁሉም የአፍጋኒስታን ስደተኞች ፣ለሁለተኛ ጊዜ የመጡ የአፍጋኒስታን ስደተኞች ጉዳዮችም መፋጠናቸው ያጠራጥራል። ከዚያ ይልቅ እንደ ቀድሞው ጊዜ መውሰዳቸው አይቀርም።»
ሺፋወር በዚህ ረገድ ማንሺንግ እና ባምበርግ በተባሉት የባቫርያ ግዛት ከተሞች ያለውን ተሞክሮ በምሳሌነት በማንሳት ሂደቱን ማፋጠን አለመቻሉን አስረድተዋል። በነዚህ  ከተሞች በሚገኙ ሁለት ማዕከላት በእያንዳንዳቸው ከ1ሺህ በላይ ስደተኞች እንዲገቡ ተደርጓል። የሚኖሩትም በተቀራረቡ ስፍራዎች ያለምንም ስራ ነው። ከተቀረው ዓለምም ተገለዋል። ይህን መሰሉ አያያዝ ለስደተኞች መብት በሚከራከሩ ድርጅቶች ይተቻል። የባቫርያ የስደተኞች ጉዳይ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ በማንሺንግ ከተጠለሉት 10 በመቶው ከ18 ወራት በላይ በማዕከሉ እንዲቆዩ መደረጉን አስታውቋል። በቆይታቸውም እንዳይሰሩ መከልከላቸውን፣በእጃቸው ያለ ገንዘብ መወሰዱን እና የጀርመንኛ ቋንቋ እንዳይማሩ መደረጉን በቂ ትምሕርትም እንደማያገኙ ምክር ቤቱ ገልጿል።ዜሆፈር እንዳሉት በአዳዲሶቹ ጊዜያዊ የማቆያ ማዕከላት ስደተኞች ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ እንዲኖሩ አይደረግም። ይህን  የዜሆፈርን  እቅድ የእርዳታ ድርጅቶችን ጨምሮ
Deutschland Asylpolitik Bayerisches Transitzentrum (picture-alliance/dpa/S. Puchner)
የስደተኞች መብት ተሟጋቾች ይቃወማሉ። በሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን በአንድ ቦታ ማቆየት አደገኛ ነው ሲሉ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል። ይህን የሚቃወሙትም ካለፉ ልምዶች በመነሳት መሆኑንንም ይናገራሉ። ብዙዎች አንድ ላይ በሚኖሩበት ስፍራ በጥቃቅን ነገሮች ሳይቀር በቀላሉ በሚነሳ አለመግባባት እና ግጭት ፖሊስ ሊያስጠራ የሚችሉ ችግሮች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ስጋታቸው ይገልጻሉ። አዲሱን አሰራር የሚቃወሙት የስደተኞች እና የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ብቻ አይደሉም። በጀርመን ላዕላይ ምክር ቤት ስደተኞችን ከህብረተሰቡ ጋር የማዋሀድ ክፍልም ጭምር እንጂ። የዚሁ ክፍል ቃል አቀባይ ሬጊና ክራይዲንግ ህግን ተከትለው የሚካሄዱ ተግባራትን እንደሚደግፉ አስታውቀው አዲሱን አሠራር ግን የማይጠቅም ብለውታል።
«የምንቆመው ለህጋዊው ሁኔታ ነው። ሆኖም በመጀመሪያው የፖለቲካ ግመገማችን ብዙ ሰዎችን በአንድ ሰፊ ቦታ ለረዥም ጊዜ ማስቀመጥ ውጤታማ ያልሆነ እና ለውህደትም የማይጠቅም ሆኖ አግኝተነዋል። ይህን ጠቃሚ አድርገን አንቆጥረውም።»
የማዕከላቱ ተቃዋሚዎች እንደሚሉት ዋናው ዓላማቸው ስደተኞች ወደ ጀርመን ዝር እንዳይሉ ማድረግ ነው። የፍልሰት ጉዳዮች ተመራማሪም የሆኑት ሺፋወርም አስተያየት ተመሳሳይ ነው።
«የመሸጋገሪያ ማዕከላቱ ተስፋ ማስቆረጫ መሆናቸው ግልጽ ነው። ለስደተኞቹ  ምልክት መስጫ ነው። እዚህ መምጣታችሁን አንፈልግም የሚል። ይህ ሊሰራ ይችል ይሆናል። ሆኖም ለውህደት ዋጋ እስከማስከፈል ይሄዳል።»
በነዚህ ማዕከላት እንዲኖሩ የሚያስገድዱ ቅድመ ሁኔታዎች የስደተኞቹን ልብ ሊሰብሩ ይችላሉ። ሺፋወር የሚያስጠነቅቁት ሌላ ጉዳይም አለ። በተለይ ማዕከላቱ የሚገኙበት ቦታ የሚያስከትሏቸው መዘዞች። በርሳቸው አስተያየት እነዚህ ማዕከላት በስደተኞቹም ሆነ በአካባቢው ህብረተሰቡ እንደ እስር ቤት ስለሚቆጠሩ የተለያዩ መዘዞችን ሊያስከትሉ ይችላሉ።
«አንድ ከተማ የመሸጋገሪያ ማዕከል ካላት ሸክም ነው የሚሆንባት።የአካባቢውን ማህበራዊ ድባብ ይመርዛል።አሉታዊ ስሜትም ይፈጥራል።»  
Horst Seehofer Innenministerkonferenz in Quedlinburg (picture-alliance/dpa/H. Schmidt)
በአጠቃላይ በሺፋወር እምነት ፖለቲከኞች እነዚህን ማዕከላት በመፍጠር ለመራጩ ህዝብ ፖለቲካዊ ምልክቶችን እየሰጡ ነው። ሆኖም  የተሳሳተ ያሉት ይህ ምልክት እና የፖለቲካ መርህ  ሰዎች ወደ ህገ ወጥ እርምጃ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ ይሆናል።
«ለብዙሀኑ የህብረተሰብ ክፍል ምልክት መተላለፍ አለበት። እኛ አንድ ነገር እያደረግን ነው። ሁሉንም ነገር በቁጥጥር ስር እናደርጋለን የሚል። ይህ ምልክት አሳሳች ነው። ምክንያቱም ስርዓተ አልበኝነትን ያሰፋፋል። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ የሚዘፈቁት ቁጥር ይጨምራል። ከስዊዘርላንድ ያገኘነው ተሞክሮ አለ። እዚያ ከሚገኙ የስደተኞች የመሸጋገሪያ ማዕከላት መጠረዝ የነበረባቸው ጠፍተዋል። ስዊዘርላንድ አለያም ጎረቤት ሀገራት ውስጥ በህገ ወጥ ስደተኝነት ነው ያሉት ። የባየርን የስደተኞች ጉዳይ ምክር ቤት እንዳለው ከባቫሪያዎቹ ከማንሺንግ እና ከባምበርግ ምዕከላት ሊጠረዙ ከነበሩ ስደተኞች 30 በመቶ ያህሉ የመጠረዣ ቀናቸው ሳይደርስ ጠፍተዋል። »
ስደተኞች ከነዚህ ማዕከላት መሸሻቸው የተለያዩ እንደ ሺፋወር ሌሎች ችግሮችንም ሊያስከትል ይችላል።
«በተለይ ወጣት ወንዶች በነዚህ ማዕከላት ከሚታየው ገፊ አቀባበል በመሸሽ  ወደ ከተማ ሊያመልጡ ይችላሉ። ይህ ደግሞ ከፍተኛ ግጭት ሊያስነሳ ይችላል። ያ ማለት በአካባቢያቸውም ሆነ በቀጥታ በከተማው ውጥረት ሊፈጥር ይችላል።»
በሺፋወር አስተያየት ስርዓት ለማስከበር ቃል ተገብቶ ተጨማሪ ትርምስ እየተፈጠረ ነው። እነዚህን የመሳሰሉ ትችቶች የሚሰነዘሩበት የነዚህ የስደተኞች ጊዜያዊ የማቆያ ማዕከላት ሥራ መቀጠል አለመቀጠል ከ6 ወራት በኋላ በሚካሄድ ግመገማ ውጤት የሚወሰን ይሆናል። በመጪው ጥቅምት ምርጫ የሚጠብቃቸው የባየርን አስተዳዳሪዎች ግን በማዕከላቱ ሥራ መጀመር፣ ለመራጮቻቸው የሚፈልጉትን መልዕክት አስተላልፈዋል። ያሰቡት ይሳካላቸው አይሳካላቸው ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል።
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

Friday, August 17, 2018

በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ያለው የዘር መድልኦ ይበልጥ እየተባባሰ መምጣቱ ተነገረ፡

Bildergebnis für ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ

በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ያለው የዘር መድልኦ ይበልጥ እየተባባሰ መምጣቱ ተነገረ፡፡
 በቅርቡ የኢሳት ቴሌቪዥን “በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ አመራሮች ዘንድ የሚሰራውን የተጠናከረ የሙስና አሰራር አጋልጠዋል” በማለት የተጠረጠሩ የሌላ ብሄር ተወላጅ የድርጅቱን ሰራተኞች ከኃላፊነት በማውረድ አሰራሩን ሚስጥራዊ ለማድረግ ይበልጥ እየሰራ መሆኑን ውስጥ አዋቂዎች ተናግረዋል፡፡
የኢሳት ቴሌቪዥን ዜና ከተሰማ በኋላ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የሚገኙት የፋብሪካው ከፍተኛ አመራሮች ፤ በተለይ የአማራ ክልል ተወላጅ የሆኑ ሰራተኞችን በማንሳት እና ከአመራሩ ጥቅማ ጥቅም የሚያገኙ “ጥቅም አደር” ሰራተኞችን በመተካት የቆዬ የዝርፊያ ተግባራቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ሁኔታዎችን እያመቻቹ ነው ተብሏል፡፡
የህወሃት መራሹ የቅዱስ ጊዎርጊስ ቢራ ፋብሪካ ስራ አመራር ቡድን ‘ሊቃወሙንና መረጃ በማቀበል የዘረፋ አሰራራችንን ሊያጋልጡ ይችላሉ’ ብለው ያሰቧቸውን በአመራር ላይ የሚገኙትን ታታሪ ሠራተኞችን በማንሳታቸውም- ሰራተኛው ቅሬታ እያሰማ መሆኑን የውስጥ አዋቂዎች በተለይ ለኢሳት ተናግረዋል፡፡
በፕሮሞተር ክፍል በዋና አስተባባሪነት ስራ ላይ ውጤታማ ስራ እንደሚሰሩ በሠራተኛው የሚታወቁ ሶስት የስራ ኃላፊዎችን ከደረጃ ዝቅ ያደረገው የፋብሪካው የህውሃት ቡድን ፤ ሰራተኞችን ከነበሩበት ቦታ በማንሳቱ ሂደት ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የታዘዙት በምስራቅ አፍሪካ የቢጂአይና ካስቴል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል አለነ ናቸው፡፡
ከአሁን በፊት በፋብሪካው ሰራተኞች ላይ የወሰዱት የማሰርና የማንገላታት አሰራርን ለመከተል የወቅቱ ሁኔታው ያልፈቀደላቸው የፋብሪካው አመራሮች፤ በተቀናጀ መልኩ ምርመራና ክትትል በማድረግ ሚስጢር የሚሾልክበትን ቀዳዳ ለመዝጋት እየሰሩ ነው፡፡ ከአመራር ቦታቸው በግፍ እንደተፈናቀሉ የተነገረላቸው ሶስቱ ሠራተኞች- አቶ መቆያ አለምነው፣አቶ ቴዎድሮስ አላምረውና አቶ ፍቅረ ዮሃንስ እንደሆኑ የውስጥ መረጃ ምንጮች ይገልጻሉ፡፡
አቶ ሱራፌል እርምጃዎችን እንዲወስዱ የተሳሳተ መረጃ በመስጠትና ጥቆማ በማቅረብ በሰራተኞች ላይ ማፈናቀል እየተሰራ መሆኑን የሚናገሩት ሰራተኞች፣ በዚህ ስራ ላይ በፊታውራሪነት የሚሳተፉት አቶ ቴዎድሮስ፣አቶ ኢሳያስና አቶ ፍትሃንግሰት የተባሉት ቀደም ብለው በዝሪፊያው ተግባር የተሰማሩ አመራሮች መሆናቸውን ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል፡፡
የፋብሪካው አመራሮች ለመንግስት መክፈል የሚገባውን ገንዘብ ላለመክፈል ያልተገባ ወጭ በማውጣት እንደሚሰሩ የሚናገሩት የፋብሪካው ሰራተኞች ፤በግቢው ውስጥ ተለያዩ አላስፈላጊ ግንባታዎችን በማካሄድና በየሳምንቱ የማፍረስ – መገንባት ስራ በማከናወን የሃገሪቱ መንግስት ተገቢውን ግብር እንዳያገኝ በመስራት ላይ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡
በረጅም ጊዜ የከተሞች ዕቅድ ፋብሪካዎችን ከማዕከላዊ የከተማ ክፍል ማውጣት ቢሆንም የፋብሪካው አመራሮች ግን አሁንም ታላላቅ ግንባታዎች በማካሄድ በሰበብ ከፍተኛ ምዝበራ እያካሄዱ መሆኑን የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ፋብሪካው ከተለያዩ የህወሃት አስመጭዎች መኪኖችን በከፍተኛ ዋጋ በመግዛት የእርስ በርስ የጥቅም ትስስሩን እንዳጠናከረ የሚናገሩት ሰራተኞች ፤ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያላጠናቀቁ መኪኖችንም የአመራሩ ወዳጅ ቤተሰቦች በወደቀ ዋጋ በመግዛት ህጋዊነትን ያልተከተለ የጨረታ ሂደት በማከናወን እርስ በርስ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አሰራር እንደሚከተሉ ተናረዋል፡፡
አብዛኛው የፋብሪካው ሠራተኛ ከእጅ ወደ አፍ በሆነ የኑሮ ሁኔታ ላይ ቢገኙም ፤ ወደ አመራሩ የቀረቡ ሆድ አደር ሰራተኞችና የህወሃት አባላት ብቻ ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት በፋብሪካው ለረጅም ዓመታት የሰሩ ሃቀኛ ሰራተኞች፤ “አጠቃላይ አሰራሩ ልብን የሚቆስል ነው” በማለት ይናገራሉ፡፡
የአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር የዶክተር አብይ አመራሮች፣ በፋብሪካው ውስጥ የሚካሄደውን ገደብ ያጣ ምዝበራ በመከታተል ሁሉም ዜጋ እንደስራው መጠን ማግኘት የሚችልበትን አሰራር እንዲዘረጉ እኚሁ ሰራተኞች በድጋሜ ጠይቀዋል፡፡

wanted officials