Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, August 14, 2018

ከደብረ ብርሃን 12 ኪ.ሜ ርቀት በምትገኘው ጫጫ ከተማ አቅራቢያ በተከሰተ የመኪና አደጋ 16 ሰዎች ሞቱ


ከደብረ ብርሃን 12 ኪ.ሜ ርቀት በምትገኘው ጫጫ ከተማ አቅራቢያ በተከሰተ የመኪና አደጋ 16 ሰዎች ሞቱ፡፡
በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሰዎች ጭኖ ሲሄድ የነበረ ቅጥቅጥ መኪና፣ ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ ከሚመጣ ሚትስቡሽ ሲኖ ትራክ መኪና ጋር ተጋጭቶ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
የደብረ ብርሃን ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ዋና ሳጅን ላቀው ዘነበ ለኢቢሲ እንዳሉት አደጋው ከባድ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር ከ16 ሊጨምር ይችላል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ተሳፋሪዎች ለህክምና መላካቸውንም አመልክተዋል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ዋና ሳጅን ላቀው ተናግረዋል፡፡
Ebc

No comments:

Post a Comment

wanted officials