Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, June 28, 2014

ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ” ለአንድነታችን በጽናት እንቆማለን” የሚሉ መፈክሮችን በማሰማት የረመዳንን ጾም ጀመሩ

ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ” ለአንድነታችን በጽናት እንቆማለን” የሚሉ መፈክሮችን በማሰማት የረመዳንን ጾም ጀመሩ

ሰኔ ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የሰላማዊ ተቃውሞ ታሪክ ውስጥ ረጅም ጊዜ በማስቆጠር ክብረወሰን የሰበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ፣  በረመዳን ጾም መግቢያም ” በአንድነታችን እንጸናለን” በሚል መፈክር ተካሂዷል።
እንደወትሮው ሁሉ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በአንዋር መስጊድ በተካሄደው  የጸሎት ስነስርአት፣ ሙስሊሙ “በአንድነታችን እንጸናለን” የሚሉ በወረቀት ላይ የተጻፉ መፈክሮችን ከፍ አድርጎ በማሳየትና እጅ ለእጅ በመያያዝ መልእከቱን አስተላልፏል። ዝግጅቱ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተጠናቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት የፍርድ ሂደት እንደቀጠለ ሲሆን ፣ ኢትዮጵያውያኑ ” የሃይማኖት ነጻነታችን ይከበር” የሚል ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ እጅግ አሰቃቂ እንግልትና በቃላት ሊገለጹ የማይችሉ ግፎች በወንዶችና በሴት እሰረኞች ላይ መፈጸማቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች በማህበራዊ ድረገጾች እየተለቀቁ ነው።
የኮሚቴ አባላቱ የሚያሳዩት ጽናት በርካታ ሙስሊሞች በጽናት እንዲቆሙ እንዳደረጋቸው ታዛቢዎች ይናገራሉ። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች መሪዎቻቸውን ለማየትና ለማበረታታት የፍርድ ቤት ቀጠሮች በሚኖሩበት ጊዜ እየተገኙ ድጋፋቸውን ይገልጻሉ።
በሙስሊሙ ትግል መፍትሄ ያጣ የሚመስለው መንግስት፣ ሙስሊሙ መሪዎቹ ሲታሰሩበት ትግሉን ያቆማል ብሎ መሪዎቹን ቢያስርም፣ ተቃውሞው ግን ሊቆም አልቻለም። ታዛቢዎች እንደሚሉት መንግስት መሪዎቹን ከእስር ካልፈታ፣ በሙስሊሙ ህዝብ ላይ ለፈጸመው በደል ይቅርታ ካልጠየቀና  ጥያቄዎቻቸውን  በአስቸኳይ ካልመለሰ፣ ተቃውሞው መቀጠሉ አይቀሬ ነው።

ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣበት የሃረር ውሃ ፕሮጀክት መክኖ መቅረቱን መረጃዎች ጠቆሙ

ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣበት የሃረር ውሃ ፕሮጀክት መክኖ መቅረቱን መረጃዎች ጠቆሙ

ሰኔ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-
ከክልሉ ውሃ ልማት ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የሃረር ከተማን የውሃ ችግር ለመቅረፍ በሚል በተለያዩ ወቅቶች ከ747 ሚሊዮን 175 ሺ ብር በላይ ወጪ ቢደረግም አብዛኛው ፕሮጀክቶች በመክሰማቸው የከተማው ህዝብ ለአሳሳቢ የውሃ ችግር ተዳርጓል።
የከተማውን የውሃ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ከፍተኛ ግምት የተጣለበት የሃሰሊሶ መስመር መጠናቀቁን ተከትሎ ለምረቃ የተዘጋጀው መጽሄት  ” ውሃ በፈረቃ ድሮ ቀረ!” በሚል ርእስ ሃምሌ 2004 ዓም ባሰፈረው ጽሁፍ ” በሀረር ከተማ የመጠት ውሃና ሳንቴሽን ፕሮጀክት ግንባታው በመጠናቁ ከድሬዳዋ አስተዳደር የሃሰሊሶ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ የድሬዳዋ ፖሊስ አካዳሚ፣ የገነት መናፈሻ አካባቢ፣ የጀሎ በሊናና ሀርላ ገጠር ቀበሌዎች ተጠቃሚ ሲሆኑ ከመስራቅ ሃረርጌ አስተዳደር ደግሞ የደንገጎ፣ የአዴሌ፣ የሃረማያና አወዳይ የወሌንቦ ገጠር ቀበሌ፣ እንዲሁም የሃረማያ ዩኒቨርስቲ እና የሃረር ከተማ ነዋሪዎች ባለድርሻ ተጠቃሚ በመሆናቸው ከሁለት አስር አመታት በላይ የዘለቀው የነዋሪዎቹ መሰረታዊ ችግር የነበረው የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ተቀርፎላቸው የ24 ሰአት ተጠቃሚ ሆነዋል” ሲል ይገልጻል።
መጽሄቱ በመቀጠልም ” በክልላችን የተጀመሩትን የልማት ግንባታዎች ከማፋጠኑም በላኢ በከተማችን የተሻለ የማህበራዊ አገልግሎት እና የተረጋጋ የፖለቲካ ሂደት እንዲኖር ትልቁን ድርሻ ይይዛል። ከዚህ በሁዋላ የሃረር ከተማ የውሃ አቅርቦት ጉዳይ ለጸረ-ሰላም ሃይሎች የፖለቲካ መቀስቀሻ አጀንዳ መሆኑም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያከትማል።” ሲል ያትታል።
ይሁን እንጅ ከሁለት አመት በሁዋላ ይህ ብዙ የተባለለት ፕሮጀክት አደጋ ውስጥ በመውደቁ ሃረር በውሃ ችግር አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች።
ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበት የሃሰሊሶ መስመር ሙሉ በሙሉ ሲቋረጥ በሃረር ኤረር ሸለቆ የተቆፈሩት 7 ጥልቅ ጉድጓዶች ደግሞ በሃረሪ ክልል እና በኦሮምያ ምስራቅ ሃረርጌ ዞን በባሌ ወረዳ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እና ውዝግብ ምክንያት በኦሮምያ ክልላዊ መንግስት ውሳኔ እስከሚሰጥበት በሚል ስራው ተቋርጧል፡
የሶስትዮሽ የጋራ ሀብት የሆነው እና 3 ክልሎችን ማለትም ሃረሪ፣ ኦሮምያንና ድሬዳዋን አቆራርጦ የሚሄደው ከ1998 እስከ 2004 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው የሀሰሊሶ ውሃ ከ747 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የወጣበት ሲሆን ፣ 350 ሺ የሚደርስ ህዝብ ለ30 ዓመታት ያለምንም እንከን እንደሚያጠጣ ተስፋ ተጥሎበት ነበር። ይሁን እንጅ ” ውሃ በፈረቃ ድሮ ቀረ፣ ውሃ በቦቴ ቀረ” ተብሎ የተጻፈበት የብእር ቀልም ሳይደርቅ ፣ ፕሮጀክቱ 2ኛ አመት የምረቃ በአሉን ሊያከብር ሁለት ወራት ሲቀረው የውሃ መስመሩ ተቋርጧል።
ክስተቱ በክልሉ ባለስልጣናት እና ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በሙስና ምክንያት እንደቆመ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ይገልጻሉ።
የተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 340/95 ” ለሃረር ከተማ የንጹህ ውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ከአፍሪካ ልማት ፈንድ ብድር ለማግኘት የተፈረመ የብድር ስምምነት” በሚል ያወጣው አዋጅ ከ2005 ዓም ጀምሮ በ40 አመታት የሚከፈል 215 ሚሊዮን ብር መንግስት ከአፍሪካ ልማት ባንክ ገንዘብ መበደሩን ያመለክታል። እንዲሁም ለአቅም ግንባታ በሚል 12ሚሊዮን ተጨማሪ እርዳታ ተሰጥቶበታል።
በፕሮጀክቱ ከተሳተፉት መካከል ሲዮም የተባለው የፈረንሳይ ኩባንያ አጠቃላይ ሂደቱን በመምራቱ 18 ሚሊዮን ብር፣ የቻይና ኮንስትራክሽን እና ኦቨርሲስ ኩባንያ የሲቪል ግንባታዎች ለመስራት 49 ሚሊዮን ብር፣ የህንዱ ቴክኖፋብ ለኤሌክትሮ መካኒካልና ለፓምፕ እና ለመሳሰሉት 100 ሚሊዮን ብር፣ እንዲሁም የኔዘርላንዱ ቬቲንስ ኢቪዴስ ኢንተርናሽናል በውሃው ያለውን ከፍተኛ የካልስየም ባይ ካርቦኔት ስራ ለመስራት 37 ሚሊዮን ብሮች ተከፍሎአቸዋል።
ፕሮጀክቱ እንደተጠናቀቀ ሃረሪ ክልል ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በአዲሱ የውሃ መስመር በአመት ለኤሌክትሪክ ፍጆታ እና ለጥገና የማወጣው ወጪ 13 ሚሊዮን ብር ነው በሚል ምክንያት ቀድሞ ከነበረው ታሪክ ላይ  100 ፐርሰንት በመጨመር ነዋሪዎች ከታህሳስ 1 /2005 ዓም ጀምሮ በአዲሱ ታሪክ መሰረት እንዲከፍሉ አድርጓል።
የሃሮማያ ሃይቅ ሙሉ በሙሉ በደለል ተሞልቶ የከብት ግጦሽ መሬት ቢሆንም ከሃይቁ በስተምስራቅ ዳር ኢፋቴባ በሚባለው ቀበሌ ለመጠባበቂያነት የተቆፈሩት 7 ጉድጓዶች በአሁኑ ወቅት ለነዋሪው ባለውለታ እየሆኑ ነው።
ዳገታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች 20 ሊትር ውሃ በ10 ብር እየገዙ ሲሆን ፣ በክልሉ ያሉት ሁለቱ የውሃ ቦቴዎች በደርሶመልስ ጉዞ 40 ኪሜ ያክል ስለሚጓዙ የነዋሪውን ፍላጎት ማርካት ቀርቶ ማቃመስ አልቻሉም።
የሃረሪ ክልል እና የኦሮምያ ክልል ምስራቅ ሀረርጌ ዞን በባቢሌ ወረዳ ስር የሚገኘው ኤረር ሸለቆ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ በተገመተው ወጪ 7 ከፍተኛ ጥልቅ ጉድጓዶች በቅርቡ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ወጥቶበት በተገዛ የውሃ መቆፈሪያ ማሽን ቢቆፈርም፣ የባብሌ ወረዳ መስተዳደር ባነሳው ” የእንካፈል” ጥያቄ በተፈጠረ ውዝግብ የኦሮምያ ክልል ምላሽ እስከሚሰጥ በሚል ስራው እንዲቆም ተደርጓል።
የሃሰሊሶ ውሃ የተቆፈረው በሀረሪ ክልል ተበዳሪነትና ወጪ እድራጊነት ሲሆን የድሬዳዋ መስተዳደርና የኦሮምያ ምስራቅ ሃረርጌ ዞን መስተዳደር ” ውሃ ካላካፈላችሁን አናስቆፍርም” በማለታቸው ውሃ እንዲካፈሉ ተደርጓል።
በሃረር የውሃ እና የዘይት አቅርቦት ችግር መከሰቱን በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል።

የደሞዝ ጭማሪ እንደሚኖር መነገሩን ተከትሎ የእቃዎች ዋጋ ወደ ላይ እየወጣ ነው

የደሞዝ ጭማሪ እንደሚኖር መነገሩን ተከትሎ የእቃዎች ዋጋ ወደ ላይ እየወጣ ነው

ሰኔ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :
-አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ በሃምሌ ወር መጨረሻ የደሞዝ ጭማሪ ይኖራል በማለት ከተናገሩ በሁዋላ ደሞዙ ሳይለቀቅ፣ የቤት ኪራይ እንዲሁም የምግብ እና የአላቂ እቃዎች ዋጋ ጭማሬ እያሳየ ነው።
ጭማሪው በመላ አገሪቱ የሚታይ ሲሆን በአንዳንድ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የሚባል ጭማሪ እየታየ ነው።
መንግስት ስለጭማሪው ተጨማሪ ማብራሪያ ባይሰጥም፣ ነጋዴውና ቤት አከራዮች ጭማሪ በማድረጋቸው የደሞዙን ጭማሪ ለማየት በሚጓጓው ሰራተኛ ላይ ፍርሃት እንዲነግስ አድርጓል።

ሰርካለም ፋሲል በቴዎድሮስ ባህሩ ላይ የመሰረተቻቸው ክሶች

ሰርካለም ፋሲል በቴዎድሮስ ባህሩ ላይ የመሰረተቻቸው ክሶች

የህወሐት ገዥ አካል እርሷን እና ባለቤቷን እስክንድር ነጋን ወደ እስር ቤት እስከወረወረበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ እና አሳታሚ ሆና ስትሰራ በቆየችው ሰርካለም ፋሲል በቴዎድሮስ ባህሩ ላይ በጣም ጠንካራና ማስረጃ የሞላው ክስ አቅረባለች፡፡ ሁለቱም ሰርካለም እና እስክንድር (በአሁኑ ጊዜ በሀሰት የሸፍጥ ክስ ተመስርቶበት የ18 ዓመታት እስራት ተበይኖበት ከመሀል ከተማ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ በሚገኘው በታዋቂው የ “መለስ ዜናዊ የቃሊ እስር ቤት”በመማቀቅ ላይ ያለው) በዘመናዊ የአፍሪካ የነጻ ጋዜጠኞች ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በገዥው አካል ጥቃት የተፈጸመባቸው እና ከፍተኛ የሆነ ዓለም አቀፋዊ አድናቆትን ያገኙ ሰላማዊ ጋዜጠኞች እስክንድርና ሰርካለም ናቸው፡፡ ባለፉት ሶስት ዓመታት ውሰጥ እስክንድር እያንዳንዱን ታዋቂ እና ታላላቅ ዓለም አቀፋዊ የፕሬስ ሽልማቶች አሸናፊ ነበር :: ከሁለት ሳምንታት በፊት በተወካዩ አማካይነት የተቀበለውን የ2014 ወርቃማ የብዕር የነጻነት ሽልማት ጨምሮ በዓለም ታዋቂና ተወዳጅ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ሰርካለምም እንደዚሁ “ዓለም አቀፍ የሴቶች ሜዲያ ፋውንዴሽን” ከተባለው ዓለም አቀፍ የፕሬስ ድርጅት አደጋ ተደቅኖ ባለበት ሁኔታ የተለዬ ጀግንነትን ለሚያሳዩ ጋዜጠኞች ”ለደፋር ጋዜጠኝነት ሽልማት“ የሚለውን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ሽልማቶችን አግኝታለች፡፡ በተቀዳ የድምጽ/ኦዲዮ ቃለ መጠይቅ ሰርካለም ቴዎድሮስ ባህሩ በቀላሉ “ትዕዛዝን ብቻ በመቀበል” የሰራ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከፍርድ ቤቶች ውጭ ወደ እስር ቤት እንዲገባ እና እንዲወጣ ትዕዛዝ ከሚሰጡት ሰዎች አንዱ ነበር ብላለች፡፡ ሰርካለም በተጨባጭ እንዳስቀመጠችው ባህሩ ባለቤቷን የገዥውን አካል ትዕዛዝ ተቀብሎ ከመተግበርም ባሻገር “ሆን ብሎ እና ስሜታዊነት በተሞላበት ሁኔታ” ሲያሰቃየው እንደደነበረ ገልጻለች፡፡ እንደ ሰርካለም አባባል ከሆነ ባህሩ ቁጡ፣ ጨካኝ፣ ችግር ፈጣሪ፣ ምህረት የለሽ እና ሩህሩህነት የማይሰማው አረመኔ አቃቤ ህግ ነበር ብላለች፡፡ እንደ ባለሙያ ዓቃቤ ህግ የሚገባውን ህጋዊ ስርዓት ተከትሎ የሚሰራ ሳይሆን እንደ ፖለቲካ አቃቤ ህግ ተከላካዮችን ያድን ነበር፡፡ ባህሩ ተከላካዮችን አሳንሶ ለማሳየት በፍርድ ቤቱ ችሎት ፊት ሁሉንም አጋጣሚዎች ሁሉ ያደርግ ነበር፡፡ ተከላካዮች ምንም ዓይነት ወንጀል ያልሰሩ ነጻ መሆናቸውን ሊያስረዱ የሚችሉ ሰነዶችን እና ምስክሮችን በሚያቀርቡበት ጊዜ ሁሉ እነዚህን በሚያስተባብል መልኩ ተቃውሞዎችን እያቀረበ ይከላከል ነበር፡፡ ተከላካዮች ፍትሀዊ ብይን እንዳያገኙ እና ማለቂያ በሌለው ረዥም ቀጠሮ እየተመላለሱ እንዲጉላሉ በማሰብ እንዲሁም የፍርድ ሂደቱን ስርዓት በማጣመም ከፍትህ አካላት የአሰራር መርህ ውጭ በሆነ መልኩ ፍትህን ሲያዛበ ነበር፡፡ የጥፋተኝነት ውሳኔ ለማሰጠት በማሰብ የተፈበረኩ እና የሀሰት ማስረጃዎችን ያቀርብ ነበር ብላለች፡፡ ሰርካለም በተለየ መልኩ ቴዎድሮስ ባህሩ በእራሱ አቅም እና እንደ መንግስት ዓቃቤ ህግ እያወቀ ሆን ብሎ እና የያዘውን ስልጣን ለእኩይ ተግባር በማዋል በእርሷና በባሌቤቷ የክስ ሂደት ላይ የህግ የበላይነትን ሲያጣምም ቆይቷል በማለት ውንጀላ አቅርባበታለች፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 ባህሩ በባለቤቷ ላይ መሰረተ ቢስ ክስ በመመስረት፣ የሀሰት ማስረጃ እና የሀሰት ምስክር በማቅረብ እውነታውን እያወቀ ሆን ብሎ ሲያጣምም ነበር በማለት ወንጅላዋለች፡፡ ሰርካለም ውንጀላዋን በመቀጠል ባህሩ እስክንድርን የግንቦት ሰባት ድርጅት አመራራ በመሆን ወጣቶችን እየመለመለ ለሽብር ጥቃት ሲዳርግ ነበር ብላለች፡፡ ባህሩ ይህንን ውንጀላ ለማስተባበል የሚያስችል ምንም ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አልቻለም፡፡ ሆኖም ግን የሸፍጥ ስራውን ለማከናወን ከዳኞች ጋር የሸፍጥ ዱለታ በማካሄድ ጥፋተኛ እንዲባል አስደርጓል፡፡ ሰርካለም ባህሩ እና ብርሀኑ ወንድምአገኝ የተባሉ ሁለት ዓቃብያነ ህጎች በግል የቤተሰቦቿን ንብረቶች፣ ቤቶቻቸውን፣ መኪኖቻቸውን እና ሌሎችን የግል መጠቀሚያ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ከህግ አግባብ ውጭ እንዲነጠቁ በማድረጉ ሂደት ላይ ተባባሪ ነበሩ በማለት ውንጀላ አቅርባባቸዋለች፡፡ ባህሩ እያወቀ ስልጣኑን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም ሆን ብሎ እና ሌሎችን የኢትዮጵያን የነጻውን ፕሬስ ጋዜጠኞች ለማጥቃት እንደ ሰርካለም አባባል ዓለም አቀፍ የፕሬስ አሸናፊ ተሸላሚ የሆኑትን እነ ርዕዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታዬ እና ሌሎችም ፍትሀዊ ዳኝነት እንዳያገኙ በማድረግ ደባ ፈጽሟል ብላለች፡፡ ሰርካለም በቴዎድሮስ ባህሩ ላይ ያቀረበችው ውንጀላ በተለይም የህግ የበላይነትን ከማስጠበቅ አኳያ እና የመንግስት ዓቃብያነ ህጎች ንጹሀን ዜጎች የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ሰለባ እንዳይሆኑ በመከላከል ሂደት ላይ የሚጫወቱትን ቁልፍ ሚና በሚመለከት በርካታ የህግ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርገዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህግ ዓቃብያነ ህጎች የሰብአዊ መብት ጥበቃ ንቁ ተከላካይ መሆን እንዳለባቸው እና የአገር እና ዓለም አቀፍ ህጎች ታማኝነት እና የሰብአዊ መብት መርሆዎች በከፍተኛ ደረጃ መጠበቅ እንዳለባቸው ይጠይቃል፡፡ ዓቃብያነ ህጎች ለፍትሀዊ ዳኝነት ሂደት እና ለፖለቲካ ዓላማ ሲባል ኃላፊነቶቻቸውን በአግባቡ ሳይወጡ የሚቀሩ ቢሆን የህግ የበላይነት መርሆዎችን ብቻ አይደለም እየጣሱ ያሉት፣ ሆኖም ግን ቆመንለታል የሚሉትን የፍትህን ጠቅላላ መጨንገፍ የሚያመላክት ስለሆነ የእነርሱ መኖር በእጅጉ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሁለቱም ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌ እና ዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ስምምነቶች/ሲፖመስ (ዩናይትድ ስቴትስ ሲፖመስን በኢትዮጵያ ህገመንግስት አንቀጽ 13(1)) ላይ የተቀመጠውን “እያንዳንዱ ሰው በነጻ እና ገለልተኛ በሆነ የፍትህ አካል ችሎት ፍትህን የማግኘት እና የመደመጥ መብት እንዳለው እና ማንኛውም በግለሰቦች ላይ የሚመሰረትን የወንጀል ክስ ለመከላክል መብት እንዳለው የሚደነግገውን እና እ.ኤ.አ በ1992 ያጸደቀችውን፣(ሰፖመስ በአንቀጽ 14፡ የአፍሪካ ቻርተር ሰዎች እና በህዝቦች መብቶች (አቻሰህመ) ከአንቀጽ 6-8 የተዘረዘሩትን መመልከት ይቻላል)፡፡ የሮማ ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (አይሲሲ) የወንጀለኞች ፍትህ የማግኘት መብት መርሆዎችን በግልጽ ያስቀምጣል (ከአንቀጽ 22-33) እና የፍትሀዊ ዳኝነት (ከአንቀጽ 62 – 67) በግልጽ ተመልክቷል፡፡ ለሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ሰላባዎች ካሳ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ህግ እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ህግ መጣስን አስመልክቶ (በተባበሩት መንግስታት የጠቅላላው ጉባኤ የዴሴምበር 16/2005 ጉባኤ ውሳኔ ቁጥር 60/147) እንደሚገልጸው መንግስታት በሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል የተጠረጠሩትን እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶችን ጥሰዋል የሚባሉትን መብት ደፍጣጮች የመዳኘት ኃላፊነት እንዳለባቸው በግልጽ ተደንግጓል፡፡“በሰው ልጆች ላይ ወንጀልን ፈጽመው በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ተደብቀው በሚገኙ የኢትዮጵያ ወንጀለኞች ላይ ጥቆማ እንዲደረግ የቀረበ ጥሪ፣ እ.ኤ.አ ጃንዋሪ 2012 “የአፍሪካ አምባገነኖች፡ የትም ሮጠው ሊያመልጡ አይችሉም፣ የትም ተደብቀው ሊያመልጡ አይችሉም!“ በሚል ያቀረብኩት ፅሁፍ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶችን ደፍጥጠው ወደ ውጭ በመኮብለል በአሁኑ ጊዜ በአሜሪካ እየኖሩ የሚገኙትን መብት ደፍጣጮች አሳድዶ በማደን ስማቸውን እና ያሉበትን ልዩ ቦታ ለአሜሪካ ባለስልጣኖች ጥቆማ በመስጠት የዜግነት ግዴታዎቻችሁን እንድትወጡ እና የወገኖቻችሁ ደም ደመከልብ ሆኖ እንዳይቀር የሚል ጥሪ አስተላልፌ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ እየተጠናከሩ በመጡት ምርመራዎች እና የሰብአዊ መብቶችን በመደፍጠጥ ወደ አሜሪካ በማታለል እና በህገወጥ መልክ የገቡትን ወንጀለኞች አሳድዶ በመያዝ በተለይም ለአሜሪካ ባለስልጣኖች ለህግ ማቅረብ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህን የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ለዜግነት እና ለጉምሩክ አስፋጻሚ ፣ ለአገር ውስጥ ደህንነት ጉዳይ ፣ ለሰብአዊ መብት ደፍጣጮች እና ለጦር ወንጀለኞች ቡድኖች እና ለብሄራዊ ደህንነት የምርመራ ክፍል መ/ቤቶች መጠቆም ትችላላችሁ፡፡ ያሜሪካ መንግስት የጦር ወንጀለኞች፣ የዘር ማጥፋት ወንጀለኞች፣ የአሰቃዮች እና ሌሎች በዓለም ላይ ግጭትን ሊያመጡ የሚችሉ የሰብአዊ መብቶች ደፍጣጮች ኮሚሽን መደበቂያ ገነት እንዳትሆን ለመከላከል ጠንካራ ምርመራዎችን ያደርጋል፡፡ የውጭ ተጠርጣሪ የጦር ወንጀለኞች፣ አሰቃዮች እና የሰብአዊ መብት ድፍጣጮች ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የግዛት ክልል ውስጥ መኖራቸው በሚታወቅበት ጊዜ የምርመራ ቡድን ሙሉ የህግ ኃይሉን እና ስልጣኑን በመጠቀም ለማጣራት፣ ለመዳኘት እና በሚቻልት ሁኔታ ሁሉ እንደዚህ ያሉ ሰብአዊ መብት ደፍጣጮችን ከአሜሪካ ለማስወገድ ጥረት ያደርጋል፡፡ ባለፉት አስርት ዓመታት ያሜሪካ መንግስት በመቶዎች በሚቆጠሩ ከሰብአዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ መልኩ በወንጀለኛ እና/ወይም ስደተኞች ምርመራ ላይ ስኬታማ ሆኗል፡፡ የዚህ ቡድን የዳታ መሰረት በርካታ የታወቁ ተጠርጣሪ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮችን ስም ዝርዝር አካትቶ ይዟል፡፡ የዳታ ቋቱ የታወቁ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለማድረግ ጠቃሚ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ዜጉአ ወደ100 አካባቢ ከሚሆኑ ከተለያዩ አገሮች የመጡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ላይ ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመቶዎች የሚቆጠሩ ከሰብአዊ መብት ድፍጣጮች እና ከተለያዩ የወንጀለኛ እና/ወይም ከስደተኝነት ጋር በተያያዘ መልኩ በቁጥጥር ስር አውሎ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩትን ታዋቂ ወይም ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ደግሞ ከዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በማስወጣት ወደ አገራቸው እንዲጋዙ አድርጓል፡፡ በሰው ልጆች ላይ ወንጀልን የፈጸሙ እና በአሜሪካ እየኖሩ ያሉ የኢትዮጵያወንጀለኞች ለምርመራ ለዜጉአ ሰመደጦወቡ ጥቆማ መቅረብ ይኖርባቸዋል፣ በኢትዮጵያ በሰው ልጆች ላይ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣዎች እና የጦር ወንጀሎች መረጃዎች በተሟላ ሁኔታ ተተንትነው እና ተጠቃለው ተዘጋጅተው ተይዘዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2007 በኢትዮጵያ ያለው የህወሐት ገዥ አካል አጣሪ ኮሚሽን ባቀረበው ዘገባ መሰረት የ2005 ድህረ ምርጫ ውዝግብን ተከትሎ በአገሪቱ ውስጥ ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ 193 ሰላማዊ ዜጎች የተገደሉ፣ ሌሎች 763 ሰዎች ቁስለኛ እና ሌሎች ወደ 30 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ከህግ አግባብ ውጭ ለዘፈቀደ እስራት የተዳረጉ መሆናቸውን በተጨባጭ መረጃ አስደግፎ አቅርቧል፡፡ በዚህ የወንጀል ድርጊት ውስጥ ተዋንያን የነበሩ 237 ግለሰቦች ታውቀዋል፣ እንዲሁም ከዚሁ ጋር ንክኪ ያላቸው ተጠርጣሪዎች ተለይተዋል፡፡ እ.ኤ.አ ዴሴምበር 2003 በኢትዮጵያ በጋምቤላ 424 ንጹሀን ዜጎች ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ ለህወሐት ታማኝ በሆኑ የደህንነት ኃይሎች ተገድለዋል፡፡ በኦጋዴን ላይ በሚደረገው ጭቆና እ.ኤ.አ በ2008 ሂዩማን ራይትስ ዎች ባወጣው ዘገባ መሰረት “150 የተገደሉ ግለሰቦች“ እና ሌሎች 37 ተጨማሪ ሰላማዊ ዜጎች በጦር ወንጀለኝነት ተጠያቂ በሚሆኑ በኢትዮጵያ ወታደሮች ትዕዛዝ እና ተሳታፊነት በተደረገ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝር ተመዝግቦ ተይዟል፡፡ ይህንን የጦር ወንጀል የሚያወቁት ወይም ደግሞ እንደዚህ ያለ ወንጀል እንደሚፈጸም ማወቅ ያለባቸው ሆኖም ግን ምንም ዓይነት እርምጃ ያልወሰዱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች እና የሲቪል ባለስልጣኖች እንደ ትዕዛዝ ሰጭነታቸው በወንጀሉ ተጠያቂዎች ናቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የተስፋፋው እና ስልታዊ በሆነ መልክ በሶማሊ ክልል በእያንዳንዱ መንደር ላይ እየተካሄደ ያለው ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ የሚደረገው ግድያ፣ ማሰቃየት፣ አስገድዶ መድፈር፣ እና አፍኖ መሰወር በስልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ ገዥ አካል የመጨረሻውን ተጠያቂነት ሊወስድ የሚችልባቸው እና ሊጠየቅባቸው የሚችሉ በሰው ልጆች ላይ እየፈጸማቸው ያሉ ወንጀሎች ጠንካራ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ከብዙው በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ተደብቀው በሚገኙ የኢትዮጵያ ወንጀለኞች ላይጥቆማ ለማድረግ ለምን ተነሳሽነት ማሳየት እንዳለብን፣ ምናልባትም ባለፉት በርካታ ዓመታት በኢትዮጵያውያን/ት ዘንድ በተደጋጋሚነት ሲቀርቡልኝ ከነበሩት ጥያቄዎች ውስጥ “እኔ እንደ ግለሰብ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብት ለማሻሻል ምን ማድረግ እችላለሁ?“ የሚሉ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያውያን/ት የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ለአሜሪካ የዜጎች እና ጉምሩክ አስፈጻሚ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች እና የጦር ወንጀለኞች ቡድን ለምን መጠቆም እንዳለባቸው በማስረጃ እና በመረጃ የተደገፉ በርካታ ምክንቶች አሉ፡፡
1ኛ) በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ወንጀል ሰርተው በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ሄደው ተደብቀው የሚኖሩትን መጠቆም በምንም ዓይነት ሊታለፍ የማይችል በቀጥታ የጥቃቱ ሰለባ የሆነው የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ/ት ወይም ደግሞ በሌሎች ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመ ለመሆኑ እውቀቱ ያለው የሞራል ሰብዕና ተግባር በመሆኑ ነው፡፡ በሰው ልጆች ላይ እንደዚህ ያለ ወንጅልን የሚፈጽሙ ወንጀለኞች መጋለጥ እና ከአሜሪካ ህብረተሰብ መካከል መወገድ ይኖርባቸዋል፡፡
2ኛ) በእነዚህ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ላይ ጥቆማ ማካሄድ በኢትዮጵያ በስልጣን ወንበር ላይ ተጣብቀው ላሉት ባለስልጣኖች አሜሪካ የሰብአዊ መብትን እየደፈጠጡ ለሚመጡ ወሮበላ ወንጀለኞች የሀሰት እና የተጭበረበረ የጥገኝነት ቪዛ እያመጡ በሰላም ለመኖር አሜሪካ በተጨባጭ መደበቂያ ገነት የማትሆን መሆኗን የሚገልጽ ጠንካራ መልዕክት ያስተላልፋል፡፡ እነዚህ ወንጀለኞች አሜሪካ ቢገቡ እንኳ ወደ እስር ቤት እንደሚጋዙ ዝግጅት ማድረግ አለባቸው ምክንያቱም ለፖሊስ ጥቆማ በማቅረብ ለፍትህ ይቀርባሉ፡፡
3ኛ) በዚህ ጥቆማ ላይ የሚደረግ ሰፊ የሆነ ተሳትፎ ኢትዮዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት የገዥው አካል አባላት አስቀያሚ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈጽመው ወደ ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በመሄድ አሜሪካንን የሚረግጡ ከሆነ በአሜሪካ ባንኮች የደለበውን የባንክ ሂሳቦቻቸውን ብቻ አይደለም የሚያጡት፣ ሆኖም ግን የእራሳቸውን ነጻነትም እንደሚያጡ ጠንካራ የሆነ መልዕክት ያስተላልፋል፡፡ የመጨረሻዎቹን ቀናት በአሜሪካ እስር ቤቶች ሊያሳልፉ እንደሚችሉ ዝግጅት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
4ኛ) የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች አሜሪካ የእነርሱ መደበቂያ ገነት ዋሻ እንደማትሆን እሰካመኑ ድረስ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሰብአዊ መብቶችን ጥሰት ከመፈጸም እኩይ ተግባራት ይታቀባሉ፡፡ ሁሉም የገዥው አካል አመራር አባላት በሚባል መልኩ እና የእነርሱ ታማኝ ሎሌዎች በአሁኑ ጊዜ ነገሮች በዚህ ሁኔታ የሚቀጥሉ ከሆነ እና በኢትዮጵያ ለውጥ ከመጣ ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን የፍርጠጣ ጉዞ በመሰረዝ ወደ ሌላ አዲስ ቦታ ጉዞ እንደሚያርጉ ይታመናል፡፡ እንደገና ቢያስቡ የተሻለ ይሆናል!
በኢትዮጵያ ወንጀል ፈጽመው ወደ አሜሪካ በመሄድ ተደብቀው የሚኖሩወንጀለኞች እንዳሉ እያወቁ አለመጠቆም እና ለፍትህ እንዲቀርቡ አለማድረግእና እንዲኖሩም መፍቀድ በእራሱ ወንጀል ነው፡፡ ወንጀል ከተሰራ በኋላለወንጀለኞች ተባባሪ መሆን ወንጀል ከመስራት ጋር እኩል ነው፡፡ እነዚህ በሰው ልጆች ላይ ወንጀልን ፈጽመው በአሜሪካን አገር ተደብቀው የሚገኙ ወንጀለኞች ፍትህ እንደዘገዬ ባቡር መሆኑን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ የጥቃት ሰለባዎች ለጥቂት ጊዜ መታገስ ይኖርባቸዋል፣ ሆኖም ግን በመጨረሻው ሰዓት ፍትህ በሙሉ ኃይሉ ታጅቦ ይመጣል፡፡ እ.ኤ.አ ሜይ 23/2014 ከፈለኝ ዓለሙ ወርቁ የተማረው ይህንን ሀቅ ነው፡፡ ያ በአሜሪካ ግልጽ ተደብቆ እየኖረ ያለው እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ/ት የሰብአዊ መብት ደፍጣጭ በየዕለቱ ሊማርበት የሚገባ አብይ ትምህርት ነው፡፡ ያ ሁኔታ አሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብትን እየደፈጠጡ ያሉ እና አሜሪካ ሄዶ ከመደበቅ ይልቅ ወደ ሌላ አዲስ ቦታ ለመሸሽ ዕቅድ የሚያወጡት ወንጀለኞች ሊማሩበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡
Ewnetu Taye

ስደተኞችን አስገድዶ በአውሮፕላን የሚጭነው የኖርዌይ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ለፍርድ ሊቀርብ ነው

ስደተኞችን አስገድዶ በአውሮፕላን የሚጭነው የኖርዌይ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ለፍርድ ሊቀርብ ነው።


ባለፈው አመት አስገድዶ ሰዎችን በአውሮፕላን መጫን ጉዳይ፣ አንድን ሰው እንዴት በግዴታ እንዳይወሰድ ማድረግ እንደሚቻልና በመንግስት ስለሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት እዚሁ ፌስ ቡክ ላይ ጽፌ ነበር። ግንቦት 22 ቀን 2014 ይሄው ነገር በተግባር ታየ።
በአለም አቀፍ ህግ አንድ ልኡዋላዊ ሃገር ዜጎች ያልሆኑ ህገ ወጥ ነዋሪዎችን በግዴታ ወደ ሃገራቸው የመላክ መብት አለው። 
ነገር ግን ይህ አስገድዶ የመላክ መብት አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታዎችም አሉት።
1. ከሃገር የማስወጣትና የመጓጓዣው ሂደት ኢ-ሰብዓዊ መሆን የለበትም
2. የአንድ ሃገር ሰዎችን በጅምላ ማባረር ክልክል ነው “collective expulsions is prohibited” – European Court of Human Rights, Article 4 of Protocol No. 4
3. ሃገራቸው ዜጎቼ ናቸው ብሎ ለመቀበል መስማማት አለበት (Return Agreement)
4. ሌላው ዋነኛው ተቀባዩ ሃገራቸው በተመላሾች ላይ ኢ-ሰብዓዊ ብቀላ የማያደርግ መሆን አለበት። (European Court of Human Rights Article 3)
ሰሞኑን የተፈጠረው ነገር አንድ ናስር ካኔ የተባለ የ38 ዓመት የኢራቅ ዜጋን ወደ ሃገሩ ለመሸኘት እጁ በካቴና ታስሮ በሶስት የሲቪል ፖሊስ ታጆብ አውሮፕላኑ በር ላይ ሲደርስ እጁ የታሰረ ሰው በአየር መጓዝ ስለሚከለከል ካተናውን ውስጥ ሳይገቡ ይፈቱለታል። ወንበሩ ላይ ያስቀምጡታል። አውሮፕላኑ ውስጥ ሌሎችም ተሳፋሪዎች ገብተው በየቦታቸው ተቀምጠው ነበር። አስተናጋጆቹ ቀበቷችሁን እሰሩ ብለው ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ፖሊሶቹ ቀበቶውን አስረውለት በየቦታቸው ሲቀመጡ ቀበቶውን ፈትቶ ኡኡኡ በማለት የዋይታ ድረሱልኝ ጩኸቱን ጀመረ ካፕቴን ይርዱኝ Captain Help Me .. Help Me!! በማለት በጠበጠው። ተሳፋሪው ተረበሸ። ፖሊሶቹ ድምጹን ለመቀነስ ተነስተው ተረባረቡበት። በዚህ ወቅት አፉንና አንገቱን በመያዛቸው ካፕቴኑ አራቱንም ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ አዘዘ። በህግ የሰውን አንገት መያዝ የተከለከለ ነው። በህጉ መሰረት ፖሊስ በአውሮፕላን ውስጥ በጉልበት ሰውን የመያዝ ስልጣን የለውም። ይሄን የማድረግ መብት ያላቸው በአውሮፕላኑ ውስጥ በሚሰሩት ብቻ ናቸው። ከአውሮፕላኑ ከወረደ በኋላ ፖሊስን በመክሰሱ ፖሊስ ራሱ በምርመራ ላይ እንደሆነ ዳግብላደት የተባለው ጋዜጣ ዘግቧል። እኔም ናስር ካኔንን ስለነበረው ሁኔታ በዝርዝር እንዲነግረኝ አዋርቼው አንድ ሰው በቆራጥነት ከወሰነ በግዴታ ሰዎችን ማጓጓዝ በጭራሽ እንደማይቻል ነግሮኛል። ናስር ካኔን በዚህ መልኩ ከአውሮፕላን እንዲወርድ የተደረገው ለሶስተኛ ጊዜ ነው። በመሰረቱ በግዴታ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ የሚገደደው ሰው ቀበቶ ለማሰር ፈቃደኛ አለመሆኑ ብቻ ከአውሮፕላኑ እንዲወርድ ያስገድደዋል። በናስር ካኔ ጉዳይ ፖሊስ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ የመኖሪያ ፈቃድ ያገኛል ማለት ነው።
by Girum Zeleke

የኦሮምያ ክልል ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አባረረ

የኦሮምያ ክልል ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አባረረ

ሰኔ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ሲሰሩ የነበሩ 17 ጋዜጠኞች ከስራ መባረራቸው ተገልጾላቸዋል።
ጋዜጠኞች የተባረሩበት ዝርዝር ምክንያት ባይታወቅም፣ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ከተፈጠረው ተቃውሞ እንዲሁም ባህርዳር ላይ ተደርጎ ከነበረው የስፖርት ዝግጅት የቀጥታ ስርጭት ጋር በተያያዘ ሳይሆን አይቀርም።
ቀድም ብሎ ውስጣዊ ግምገማዎች ሲካሄዱ እንደነበር የኢሳት የመረጃ ምንጮች ጠቁመው፣ 6 የሚሆኑ ጋዜጠኞች ቀደም ብለው እንዲታገዱ መደረጉን አስታውሰዋል።
በውስጥ ትርምስ ውስጥ የሚገኘው ኦህዴድ፣ በክልሉ የሚታየውን አለመረጋጋት ለማብረድ ላይ ታች ቢልም እስካሁን አልተሳካለትም።
በሚቀጥሉት ተከታታይ ሳምንታት አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ባለስልጣናት እንደሚባረሩ የኢሳት ምንጮች ጠቁመዋል።

የአማራን ህዝብ በማጥፋት ወያኔና ተቃዋሚው በጋራ እየሰሩ ነው

የአማራን ህዝብ በማጥፋት ወያኔና ተቃዋሚው በጋራ እየሰሩ ነው





አቶ አዲሱ አበበ አርብ ጁን 20 2014 በአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ያስተላለፉትን ቃለ መጠይቅ ቃል በቃል በጽሁፍ ገልብጨ ከአውዲዮው ጋር እንድልክላችሁ ያነሳሳኝ ሆን ተብሎ በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመው ዘር ማጥፋት፣ ድርጊቱን ቀጥታ በሚፈጽሙት አካላት ብቻ ሳይሆን የወያኔ ትግሬዎችን የጎሳ ፖለቲካ እንቃወማለን የሚሉ ሳይቀሩ ሆን ብለው የተሰሳተ መረጃ በመስጠት በአማራው ህዝብ ላይ የክህደት ስራ እየሰሩ ለመሆኑ ለመጠቆም እና አንባቢም ቃለ መጠየቁን በማንበብም ሆነ ቃለ መጠየቁን ከተለያዩ ድህረገጾች በመስማት ያራሱን ፍርድ እንዲሰጥ ነው። በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ በወያኔና የሱ ተናካሽ ውሾች በሆኑ የብሄር ድርጅቶች ብቻ ሳይሆን፤ በኢትዮጵያ ስም የተደራጁ ፓርቲዎች፣ ድርጅቶች፣ ሬዲዮ ጣቢያዎች፣ ድህረገጾች ወዘተ ጭምር በጋራ የሚተባበሩበት ለመሆኑ የሚጠይቅ አይምሮ ያለው ያስተውለው።
ተፈናቃዮች አማራ ናችሁ ተብለን ከወለጋ ተፈናቀልን እያሉ፤ አቶ አዲሱ አበበ አማረኛ ተናጋሪዎች ተፈናቀሉ ይላሉ። በአማረኛ ተናጋሪነት ከሆነ ከወለጋ የተጠየቁ አፈናቃዮችኮ በአማረኛ ነው ከአቶ አዲሱ አበበ ጋር የሚነጋገሩት፤ አቶ አዲሱ አበበ የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ጋዜጠኛ ስለሆኑ፣ እንዲሁም የአሜሪካ መንግስት ከምንም ጊዜ ይበልጥና ከማንም በላይ የወያኔ ትግሬዎችን መንግስት በገንዘብና በሰው ሀይል ስለሚረዳ አቶ አዲስ አበበ ከቀጣሪያቸው አቋም ውጭ ሊሆኑ አይችሉም ብንል፡ ከአማራው ኪስ በሚወጣ መዋጮ የሚንቀሳቀሱ እንደ ኢሳትና ሌሎችም በየሀገሩና በየከተማው የተቋቋሙ ሬዲዮ ጣቢያዎችና ድህረገጾች፣ የአማራው ህዝብ አማራ በመሆናችን ብቻ ተነጥለን፤ ሀብትና ንብረታችን ተዘርፎ፣ ተደብድበን፣ ከፊሎችም ተገለው ከሞት አምልጠን እዚህ ደረሰን ሲሉ፣ ”ከባለቤቱ ይበልጥ ያወቀ ቡዳ ነው” እንደሚባለው፤ አማራ ስለሆኑ አይደለም፤ አማረኛ ተናጋሪ ስለሆኑ ነው ብለው በአማራው ህዝብ ላይ አማራ በመሆኑ ብቻ ወንጀል እንደላልተፈጸመበት አድርገው የተዛባ ማስተባበያ ለህዝብ ጀሮ ያቀርበዋል።  ከዚህ ተጨማሪ ስለዚህ መፈናቀል የዘገቡ ኢትዮጽያዊ የሚባሉ ድህረገጾችና ሬዲዮ ጣቢያዎች ብዙም ባይሆኑ፣ ለይስሙላ የዘገቡም ዘግበውም በነጋታው ከድህረገጻቸው ያነሱ ድህረገጾችንም ታዝቤአለሁ።
ብአዴን ማን ነው ሲሉ አቶ ገብረመድህን አርአያ ሰፋ ያለ መረጃ ሰጠውናል። ብአድኖች ከመጀመሪያው ”አማራ ህዝብ ጠላት አይደለም” ያሉትን የገደሉና ከዚያም በአማራው ህዝብ ላይ በየክፈለሀገሩ እየዞሩ የአማራውን ህዝብ ነጥለው በመሪነት ያስገደሉና ያሰደዱ ለመሆኑ መረጃዎች አሉ። አሁንም ከዚህ ቃለ መጠየቅ እንደምንረዳው የኦሮሞና የአማራው ክልል ባለስልጣኖች ይሄን ያህል አፈናቅሉ፤ ይሄን ያህል ግደሉ፤ ይሄን ያህል ደግሞ ለፖለቲካ መልሱ እየተበሉ በእቅድ የሚፈጽሙት የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል መሆኑን ቃለ መጠይቁ ይጠቁማል።
በአቶ አዲሱ አበበና በሬዲዮ ጣቢያቸው ላይ እንዲያውም ስለመፈናቀሉ በመዘገባቸው ባለውለታ እንጂ ቅሬታ የለኝም። ሌሎች በተቃዋሚነት ተሰልፈናል የሚሉ ግን አሁንም ቢሆን ለይስሙላ የሚጠይቁት ”ወደ ቀያቼው እንዲመለሱ” የሚል ነው። አንድ ሰው አማራ በመሆኑ ብቻ ሀብት ንብረቱ ተዘርፎ፤ አቅመ ደካማ የሆኑ ሚስት ልጆቹ፣ በእድሜ የገፉ እናት አባት ተገለው፤ ቤቱ ተቃጥሎ ”ወደ ቀያቸው ይመሰለሱ” የሚለው ፍርድ በአማራው ህዝብ ላይ ለሚፈጸመው የዘር ማጥፋትና ማጥዳት ወንጀል ተባባሪነት ካልሆነ በቀር ትክክለኛ ፍርድ አለመሆኑን ህሌናችሁ ፍርድ ይስጥ።
አንድ ሰው አማራ በመሆኑ ብቻ ሀብት ንብረቱን ተቀምቶ፣ የተገደለው ተገሎ የሚፈናቀል ከሆነ፤ አንድ ከአማራ ወላጆች የተወለደ ኢትዮጵያዊ መብቱ ተከብሮ ለመኖሩ የጊዜና የቦታ አለመገጣጠም ካልሆነ በቀር ዛሬ ወለጋ በሚኖሩ አማሮች ላይ የደረሰው መገደልና መፈናቀል በሱ ወይም በሷ ላይ እንደማይደርስ ምንም አይነት መተማመኛ የለም። ብሄረተኝነት የግለሰቡን ብሄር አንጂ የግለሰቡን ሰብአዊ ባህሪ አይቶ ይህ ደግ ነው ተወው፣ ያ ክፉ ነው በለው አይልም። ስለዚህ ማንም ከአማራ ወላጆች የተወለደ ሁሉ በወያኔ ትግሬዎችና የነሱም ተናካሽ ውሾች በሆኑ የብሄር ድርጅቶቹ አንዲሁም ከሀገር ውጭ መረጃ በማጣመም፣ በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ወንጀል በማስተባበልና ማእቀብ በማድረግ ከወያኔ ትግሬዎች ጋር በአጋርነት የተሰለፉ ሬዲዮ ጣቢያዎችና ድህረገጾች የአማራን ህዝብ በማጥፋት ወንጀል እየተባበሩ ለመሆኑ ከኔ ጽሁፍ ይልቅ ትንሽ ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ያለው ሰሞኑን በወለጋ በአማራው ህዝብ ላይ በተፈጸመው ግድያና መፈናቀል ድህረገጾችን አይቶ፣ ሬዲዮ ጣቢያዎችን አዳምጦ ይፍረድ።
ከግለሰብ የተወረወረ ትዝብት
ቃለ መጠይቁን ለማዳመጽ ይሄንን ይጫኑ፣ በጽሁፍ ለማንበብ ከታች ያለውን ይመልከቱ

በምስራቅ እዝ የመከላከያ መኮንኖች መካከል ውስጣዊ ውጥረት ሰፍኗል

በምስራቅ እዝ የመከላከያ መኮንኖች መካከል ውስጣዊ ውጥረት ሰፍኗል።


ምንሊክ ሳልሳዊ

በወያኔ መኮንኖች እና በኢትዮጵያ የመከላከያ ስራዊት መኮንኖች መካከል በፖለቲካ እና በጥቅማ ጥቅም ጉዳዮች ዙሪያ ውስጥ ውስጡን እየተካረረ የመጣው አተካራ ከባድ ውጥረት መፍጠሩን በእዙ የሚገኙ መኮንኖች የተገኘው መረጃ ጠቁሟል። ሕገመንግስታዊ ጥያቀዎችንእና ወታደራዊ ጥቅማ ጥቅሞችን የሚተይቁ መክንኖች ከየክምፑ ተለቅመው ወደ ሰሜን እዝ እና ወደ ሶማሊያ ከሄደው ጦር ጋር እንዲቀላቀሉ ከተደረገ በኋላ ውጥረቱ እየሰፋ መምጣቱ ታውቋል።

ከዚህ ቀደም የተነሱ ሕገመንግስታዊ ጥያቄዎችን የሕወሓት ከፍተኛ መኮንኖች የጥያቄው ባለመብቶችን ወደ ሌላ አከባቢ በመቀየር የቀሩትንም በጥቅም ለመያዝ ቢሞክሩም ያላዋጣቸው ሲሆን ክመሃል ሃገር ሰልጥነው የተመደቡትም ወታደራዊ ደህንነቶች የአንድ ብሄር አባላት ስለሆኑ የመከላከያ ሰራዊቱ የበታች መኮንኖች በጥርጣሬ ስለሚመለከቷቸው የተላኩበትን ግዳጅ በብቃት መፈጸም ባለመቻላቸው ምንም አይነት ውጤት አለማምታታቸው ችግሩ ዳግም እንዲያገርሽ ሆኗል።

በወታደራዊ ደህንነቶች አማካኝነት እንቆጣጠረዋለን ብለው የምስራቅ እዝ ከፍተኛ የሕወሓት መኮንኖች ያሰቡት ጉዳይ ዳግም ውጥረት መፍጠሩ በድንበሩ አከባቢ ስጋት ስለፈጠረ ወደ አከባቢው አዲስ የመከላከያ ሰራዊት አንድ ሻለቃ ጦር እንዲመደብላቸው ጠይቀዋል።

የምስራቅ እዝ ምኮንኖች አብዛኛው ስራቸው የኮንትሮባድ ተግባራትን መፈጸም መዝረፍ እና ሴቶችን መድፈር መሆኑ ይታወቃል። የሕወሓት መኮንኖች ሌላውን አስፈላጊውን ሕግ የሚፈቅደውን ጥቅማ ጥቅም በመከልከል ከፍተኛ በድል እያደረሱ ሲሆን በሶማሊያ ክልል ውስጥ በዘረጉት ከፍተኛ የቢዝነስ ስራ ውስጥ ማንም ሌላ ሰው እንቅስቃሴ ማድረግ የማይችል ሲሆን እነሱ በሚሰሩ ቢዝነስ ውስጥ የሚገባ ንብረቱ እንደሚወረስ ታውቋል፡፤ የሞባይል ቀፎዎችን እና የኢሌክትሮኒስ ዕቃዎችን በሕገወጥ መንገድ ጭነው ካለፍተሻ ወደ መሃል ህገር በማምጣት በይርጋ ሃይሌ ሕንጻ ካሉ ወኪሎቻቸው ጋር በመተባበር በመላው ሃገሪቱ እንደሚያከፋፍሉ ታውቋል።

በአ.አ ዩኒቨርሲቲ 52 ተማሪዎች በ”ዲሲፕሊን” ሰበብ ፖለቲካዊ ክስ ተመሰረተባቸው

በአ.አ ዩኒቨርሲቲ 52 ተማሪዎች በ”ዲሲፕሊን” ሰበብ ፖለቲካዊ ክስ ተመሰረተባቸው (ዝርዝራቸውን ይዘናል)


ዘ-ሐበሻ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመብት ጥያቄ አንስተው በሃገራዊ ጉዳይ ነቃ ያለ ተሳትፎ የሚያደርጉ 52 ተማሪዎች ላይ የዲሲፕሊን ክስ መመስረቱ ተሰማ። የዲሲፕሊን ክስ የተመሰረተባቸውን ተማሪዎች ስም ዝርዝር የያዘውን ወረቀት በማህበራዊድረገጾች ላይ የለቀቁት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ክሱ የተመሰረተባቸው ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ በ2 ሰዓት በተማሪዎች ጽ/ቤት እንዲገኙ ት ዕዛዝ ተሰጥቷል።

ምናልባትም እነዚህ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ትኩረት አድርገው የሚ ንቀሳቀሱት ተማሪዎች ላይ በዲሲፕሊን ሰበብ ፖለቲካዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚችል የቅርብ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ያስታወቁ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ይህን እርምጃ ከወሰደ ሌላ የተማሪዎች አመጽ እንዲነሳ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ታዛቢዎች ይናገራሉ። በዲሲፕሊንክ ክስ ሰበብ የፖለቲካ እርምጃ ሊወሰድባቸው የተዘጋጁት ተማሪዎች ስምዝርዝር የሚከተለው ነው፦


የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበርኞች ግንባር ሰራዊት በወልቃይት ድል መቀዳጀቱን ገለጸ

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበርኞች ግንባር ሰራዊት በወልቃይት ድል መቀዳጀቱን ገለጸ

ሰኔ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰኔ 16፣ 2006 ዓ/ም በወልቃይት አድነጣ በተሰኘ ስፍራ በስርዓቱ የሚሊሻ ታጣቂ ላይ በወሰደው ወታደራዊ እርምጃ 18 ገድሎ ቻለው ሲሳይ  እና  ተጫነንጉሱ የተባሉ 2 ወታደሮችን መማረኩን አስታውቋል።
ሰራዊቱ ለሁለቱም ምርኮኞች ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታና ስለድርጅቱ አላማና ግብ በማስተማር እንደለቀቃቸውም ድርጅቱ ገልጿል።
ሰኔ 18-2006 ዓ/ም ደግሞ   የኢሕአግሰራዊት ከመንግስት የልዩ ሃይል ታጣቂ ጋር በወልቃይት አወርቂ በተባለ ቦታ ከጠዋቱ 1ሰዓትእስከ 5 ሰዓት ለአራት ሰዓት ያህል ባካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ 36 ገድሎ አርባ ስምንት 48 ማቁሰሉንና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ከነመሰል ጥይቶቻቸውና ትጥቃቸው ጋር መማረኩን ገልጿል።
ውጊያው በተካሄደበት አከባቢ የሚገኙ ነዋሪዎችና በ2007 ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው የምርጫ ድራማ ሳቢያ ከፍተኛ እንግልትና ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኙ ወገኖች ግንባሩን እየተቀላቀሉ እንደሚገኙም ግንባሩ ለኢሳት የላከው ዜና ያመለክታል።
አርበኞች ግንባር አገኘሁ ያለውን ድል በተመለከተ መንግስት የሰጠው አስተያየት የለም።

የወያኔን የጥፋት ድግስ እናምክን!

የወያኔን የጥፋት ድግስ እናምክን!


ኢትዮጵያን የሚገዛው ጉጅሌ ሀገራችንን እየወሰደበት ያለው አደገኛ አቅጣጫ አሳሳቢ ከመሆን አልፎ የአደጋውን መራራ ፍሬ ማየት ከጀመርን ሰነበትን። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ወሳኝ ከሆነው የወደፊቱ የጋራ ጥቅማቸውና ህልውናቸው በበለጠ ልዩነታቸውና ያለፈ ታሪካቸው እንደዋናው ነገር እየተቆጠረ ለሚሰበከው ስብከት የኢትዮጵያ ህዝብ አስተዋይ ባይሆን ኖሮ እስካሁን ብዙ ጥፋት በደረሰ ነበር።
ህወሃት በህዝቡ ውስጥ የኖረውን ልዩነት የጠብ፣ የግጭትና የመፈራራት መሰረት በማድረግ በሥልጣን ላይ ለመቆየት ካለው ምኞት የተነሳ በመደዴ ካድሬዎቹ አማካኝነት ለዘመናት አብሮ የኖረውን ህዝብ በማቃቃር እኩይ ተግባር ላይ ተጠምዶ ይገኛል።
ህወሃት ይህን የማጋጨት ስራ በተለይ በስልጣን የመቆየት ፍርሃት ባባነነው ቁጥር የሚጠቀምበት መሳሪያ አድርጎታል። በባህርዳር ላይ የብሄረሰቦች ኳስ ጭዋታ ውድድር ምክንያት አድርጎ፣ መደዴ ካድሬዎቹን አሰማርቶ ስታዲዮም ውስጥ ኦሮሞዎች እንዲሰደቡ ካደረገ በኋላ ነገሩን ከማረጋጋት ይልቅ በኦሮሞኛ የቴሌቪዥንና ሬድዮ፣ ኦሮሞዎች በአማራዎች ተሰደቡ ብሎ ያስነገረው ለምንድን ነው? ከዚያ በኋላ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ቁጣና ጠብ ለመቀስቀስ ብሎም በዚህ ጠብ ውስጥ ገላጋይ በመምሰል የአንዱ ብሄር ጠባቂ መስሎ ለመታየት ጉዳዩን ባልተረዱ የዋሆች ውስጥ ለመግባት ይፈልጋል። በአማራ ተወላጆች አካባቢ እኛ ከሌለን ኦሮሞ ይፈጇቹኋል፤ በኦሮምያም በሶማሊያም እንዲሁ በተዘጋ በር ውስጥ በተቃራኒው ዘረኝነትንና መከፋፈልን በመስበክ ንጹሃኑ ህዝብ ከፍርሃት ተነስቶ ተገዥ ደጋፊዎቹ እንዲሆኑ በማድረግ ላይ መሆኑንም ያልገባቸው የዋሆች ይኖራሉ። ህወሃትንና ባህርዩን በቅጡ ለምናውቀው ወገኖች ግን ይህ ተንኮሉ ትልቅ ሚስጥር አይደለም።
የጉጅሌው ቡድን የራሱን ስልጣንና የዝርፊያ ኢኮኖሚ ኮርቻ ለማደላደል እስከረዳው ወይም የሚረዳው መስሎ እስከታየው ድረስ ደሃ ገበሬዎችን ማፋጀትን፣ ህዝብን እርስበርስ ማናከስን፣ የቂም መርዝ መዝራትን የሚያየው እንደ ፖለቲካ ጥበብ ነው።
ጉጅሌው ብልጠት መስሎት የጎሰኝነትንና የማንነትን ደመነፍስ የሚነካ ፕሮፖጋንዳ በህዝቡ ውስጥ በመንዛት ሊያደርስ የፈለገው ጥፋት በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ ስላልሰራለት የራሱን ሎሌዎችና ተካፋይ መደዴ ካድሬዎችን በማሰማራት የጭካኔ ስራዎችን በማካሄድ ላይ መሆኑን በብዙ መረጃዎች አረገጋግጠናል። በአሁኑ ወቅት በየቦታው የሚካሄደውን የህዝብ ማፈናቀልና ግጭት የሚመራው ራሱ ህወሃት ያሰማራቸው ካድሬዎች እንጂ በራሱ በህዝቡ ተነሳሽነት እንዳልሆነ ሁላችንም ልናውቅ ይገባል። በዚህ ሳይጣናዊ አካሄድ ለምትደርሰው ለያንዳንዷ ጉዳት ሀላፊነት የሚወስደውም ራሱ ህወሃት መሆኑን ግንቦት 7 አጥብቆ ያምናል።
ህወሃት መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ የሚደግስልንን የጥፋት ድግስ ለማምከን የየብሄረሰቡ ልሂቃን ሁሉ አንድ ላይ ሆነን ህዝባችንን እንድንታደግ ግንቦት 7 ለሁሉም የነጻነት ሃይሎች ጥሪውን ያቀርባል።
ግንቦት 7 በዚህ የህወሃት የጨለማ መንገድ ላይ የሚያበራውን የብርሃን ችቦ ይበልጥ በማብራት ላይ ይገኛል። ሁላችንም በምናገኘው የብርሃን ሃይል ጨለማው ላይ እያበራን ከማሳየት አልፈን ወደ መቃብሩ ልንገፋው ይገባል።
ግንቦት 7 በኢትዮጵያ የማንነትና የብሄር ብሄረሰብ ጉዳዮች በሰለጠነ መንገድ እና በመደማመጥ ሁሉንም ተጠቃሚ በሚያደረግ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ያምናል። ይልቁንም የወደፊቱ የህዝባችንና የሀገራችን ጥቅም ይበልጥ የሚከበረው በስብጥርነታችን ላይ በምንገነባው አንድነት መሆኑን ያምናል።
የተከበራችሁ የአገራችን ዜጎች የነጻነታችን ጊዜ ቅርብ ነው። ህወሃት መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ ያዘጋጀልንን የጥፋት ድግስ፣ ሀገራችን የጋራ ጠላት በመጣባት ጊዜ ሁሉ እንደምታደርገው በአንድ ላይ ታግለን የጋራ ታሪክ እንሰራ ዘንድ የዘወትር ጥሪያችን እናቀርባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

የመጨረሻዉ መጀመሪያ

የመጨረሻዉ መጀመሪያ


በቅርቡ በተከታታይ አገር ቤት ዉስጥ ቅርጽና ይዘት እየያዙ የምናያቸዉና ማንም አሌ የማይላቸዉ ግዙፍ እዉነታዎች ሁሉም በአንድነት የሚጠቁሙት አይቀሬዉ የወያኔ መጨረሻ መጀመሩን ነዉ። ከዚህ ቀደም በግልጽ እንዳየነዉ ወያኔ አንድ ቦታ ሲሸነፍ ሌላ ቦታ እያሸነፈ በጉልበትም በተንኮልም የፖለቲካ የበላይነቱን እንደያዘ ከሃያ ሁለት አመት በላይ ቆይቷል። ወያኔ ለአመታት ህዝብን ያታለለባቸዉ የዉሸት ክምሮችና ህዝባዊዉን ትግል ወደ ኋላ ለመጎተት የተጠቀመባቸዉ ስልቶች ዛሬ ሁሉም ሙጥጥ ብለዉ አልቀዉበት ዬኔ ነዉ ብሎ በሚመካበት ትግራይ ዉስጥ ጭምር መግቢያና መዉጪያዉ የጠፋዉ የተከበበ አዉሬ መስሏል። በያዝነዉ የ2006 ዓም ሁለተኛዉ አጋማሽ ወያኔ ጨካኙን የአግአዚ ኃይል እዚህም እዚያም አሰማርቶ ከሚቆጣጠራቸዉ ጥቂት አደባባዮች ዉጭ እንደቀድሞዉ በግልጽ ወጥቶ ወያኔን የሚያሞግስ ወይም የወያኔን የሌለ ገድል የሚናገር ሰዉ የለም። በሌላ በኩል ደግሞ በተለያዩ የትግል ስልቶች ወያኔን የሚታገሉ ኃይሎች አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ኃይላቸዉና ቁርጠኝነታቸዉ እየጨመረ መጥቶ ወያኔ ያንን የተለመደ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃዉን እዲወስድና የራሱን የመጨረሻ እሱ እራሱ ሳይወድ በግዱ እንዲያፋጥነዉ እያደረጉት ነዉ።
የአገራችንን አንድነት ሊያላሉና ኢትዮጵያ የሚለዉን ታሪካዊ ስም ከታሪክ ዉጭ ማድረግ ከሚችሉ አደገኛ የወያኔ ባህሪዮች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ዘረኝነቱና ለአገር አንድነትና ዳር ድንበር መከበር ያለዉ የግድየለሽነት ባህሪይ ነዉ። ዛሬ ወያኔ በአራቱም ማዕዘን በየቀኑ አየጨመረና እያየለ የሚሄደዉን የህዝብ ቁጣ ለማብረድና አፋፍ ላይ ለደረሰዉ ስርዐቱ ተጨማሪ ግዜ ለመግዛት የሚወስዳቸዉ እርምጃዎች ከዚሁ ከዘረኝነት ባህሪይዉ የሚመነጪ እርምጃዎች ናቸዉ። ወያኔ ዕድሜዉ ሊበረክት የሚችለዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነጻነት የሚታገሉ ኃይሎች መግባባት ሲያቅታቸዉ መሆኑን ያዉቃል፤ ስለዚህም በተቻለዉ መጠን ኢትዮጵያዉያንን የሚለያዩና ግጭት ዉስጥ የሚከትቱ አጀንዳዎችን አየፈጠረ ይወረዉርልናል። ከእነዚህ አገር አጥፊ የወያኔ አጀንዳዎች ዉስጥ አንዱ ህዝብን በዘር ከፋፍሎ እርስ በርሱ እንዲጋጭ ማድረግ ነዉ። ለምሳሌ በቅርቡ ደቡብ ኢትዮጵያ ዲላ ከተማ ዉስጥ በንግዱ ህብረተሰብ ላይ የነጋዴዎችን አቅምና ትርፍ ያላገናዘበ ግብር በመጫን በአንድ በኩል ነጋዴዎቹ በዞኑ አስተዳዳሪዎች ላይ እንዲነሱ በማድረግ በሌላ በኩል ደግሞ የዞኑ አስተዳዳሪዎች ነጋዴዎቹን የምትሰሙን ከሆነ ስሙን አለዚያ ክልሉን ለቅቃችሁ ሂዱ የሚል አስነዋሪና የዜግነት መብትን የሚጋፋ መልስ እንዲሰጡ በመገፋፋት በጌዲኦ ብሄረሰብና በዲላና አካባቢዉ በብዛት በንግድ ስራ ላይ በተሰማራዉ የጉራጌ ማህበረሰብ መካከል ግጭት እንዲቀሰቀስ ለማድረግ ሞክሯል። ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥም እንደዚሁ የጋምቤላ ህዝብ ከጋምቤላ ዉጭ ከሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የመጡትን ኢትዮጵያዉያን ክልሉ የእናንተ አይደለምና ለቅቃችሁ ዉጡ ብሎ እንዲያሰገድድ በመገፋፋት በኢትዮጵያዉያን መካከል ቂምና ጥላቻ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፉት አምስት አመታት ወያኔ ጋምቤላ ዉስጥ ገበሬዉን እያፈናቀለ መሬቱን ለዉጭና ለአገር ዉስጥ በተለይ ለትግራይ ባለኃብቶች በርካሽ ዋጋ ማስረከቡ የሚታወስ ነዉ። ይህ ባዕዳንን ጋምቤላ ላይ እያሰፈረ ኑና እረሱ እያለ የሚለምን ነዉረኛ አገዛዝ ነዉ ዛሬ ኢትዮጵያዉያንን ከጋምቤላ ዉጡ እያለ የሚያሰገድደዉ።
ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን ያክል እንደተጠላ ለማወቅ ባለፈዉ ቅዳሜ መድረክ አዋሳ ዉስጥ የጠራዉን የተቃዉሞ ሰልፍ መመልከቱ ይበቃል። የአዋሳና የአካባቢዉ ህዝብ በዚህ መድረክ በጠራዉ የተቃዉሞ ሰልፍ ላይ የተገኘዉ ፌዴራል ፖሊስ፤ የክልሉ ፖሊስና የአገዛዙ ካድሬዎች በእያንዳንዱ ሰላማዊ ሰልፍኛ ላይ ያወርዱት የነበረዉን ዛቻ፤ ማስፌራሪያና ና የስድብ ናዳ ከምንም በለመቁጠር ነዉ። በዕለቱ የአካባቢዉን ሰላምና የሰልፈኛዉን ደህንነት አስጠብቃለሁ ብሎ በአዋሳ አደባባዮች ላይ የተሰማራዉ የወያኔ የፖሊስ ኃይል በህግ የተሰጠዉን ኃላፉነት ትቶ ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎች ሲወስድ ታይቷል።
ወያኔ ብሶቱን አይቼ 17 ዐመት ታገልኩልት የሚለዉና ዛሬም እወክለዋለሁ ብሎ የሚነግረን ክልል ቢኖር የትግራይ ክልል ነዉ። ዛሬ ትግራይ ዉስጥም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የሞቱት ለዚህ አይደለም ብለዉ ብረት አንስተዉ ወያኔን አምርረዉ የሚታገሉ የትግራይ ወጣቶች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነዉ። አስራ ሰባት አመት ሙሉ በወያኔ የማይጨበጥ ተስፋ ተታልሎ በከንቱ ህይወቱን የገበረዉ የትግራይ ወጣት ዛሬ እዉነቱ ገብቶት ወያኔን በትግራይ ህዝብ ስም መነገድህን አቁም እያለዉ ነዉ። በቅርቡ በመቀሌና በአካባቢዋ የታየዉ ከፍተኛ ፀረ ወያኔ እንቅስቃሴ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ወያኔ ለዚህ የሸተተ ስርአቱ ዕድሜ ለመግዛት ቢፍጨረጨርም “ከወደቁ በኋላ መራገጥ ለመላላጥ” ካልሆነ በቀር ካሁን በኋላ ወያኔዎች በስልጣን ላይ መቆየት ቀርቶ የዘረፉትን ኃብት የሚያሸሹበት ግዜም ልንሰጣቸዉ አይገባም።
የወያኔ ጠመንጃና የሚቆጣጠራቸዉ የአፈና ተቋሞች አላናግር ወይም አላስተነፍስ እያሉት እንደ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር ስለተገደደ ነዉ እንጂ አመጸኞቹ የወያኔ መሪዎች ለተቀረዉ የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ታገልንለት ብለዉ በስሙ ለሚነግዱት የትግራይ ህዝብ በፍጹም የማይበጁ ፀረ አገር ኃይሎች መሆናቸዉን የትግራይ ህዝብ ካወቀ ቆይቷል። ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን የትግራይ ህዝብም በቃ በስሜም አትነግዱ ወንድሞቼንና እህቶቼንም አትበድሉ ብሎ ደጋግሞ እየነገራቸዉ ነዉ። ዛሬ ብዙ የትግራይ ወጣቶች እዚያ የዛሬ ሰላሳና ሰላሳ አምስት አመት አባቶቻቸዉ የታገሉበት ጫካ ዉስጥ ገብተዉ እነሱም በተራቸዉ የዛሬዉን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በጠመንጃ ጭምር በመፋለም ላይ ይገኛሉ። ወያኔ የመጨረሻ መደበቂያዬ ይሆነኛል ብሎ ይተማመንበት የነበረዉ የትግራይ ክልል ዛሬ ግልጽ በሆነ መልኩ የወያኔን መጨረሻ ለማየት የሚቸኩሉ ጀግኖች ክልል እየሆነ ነዉ።
የትግራይ ጫካዎችን ጨምሮ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች “ጨርቅ” ብለዉ ያንኳሰሱትን የኢትዮጵያ ባንዲራ በክብር አንግበዉ ከቋጥኝ ቋጥኝ የሚዘልሉት የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ አርበኞች ወገንን የሚያኮሩ ዘረኞቹን የወያኔ መሪዎች ደግሞ ምነዉ ባልጀመርነዉ የሚያሰኙ የአገርና የወገን አለኝታ ሆነዋል። ዛሬ ወያኔ የትግራይን ምድር የእግር መረማመጃ እስኪጠፋ ድረስ በወታደርና በታንክ ያጠረዉ ይህንኑ በትግራይ ወጣቶች የተገነባ ህዝባዊ የነጻነት ኃይል ስለፈራ ነዉ። አምባገነኖቸ በደም የሚቀባበሉት የተፈጥሮ ባህሪያቸዉ ሆኖ ነዉ እንጂ የታንክና የወታደር ጋጋታ ህዝባዊ ኃይልን የሚያቆም ቢሆን ኖሮ እነሱ ዛሬ ሚኒልክ ቤ/መንግስት ዉስጥ ገብተዉ የኢትዮጵያን ህዝብ ሊረግጡ ቀርቶ ከተፈጠሩበት ደደቢት በረሃ ስንዝር ሳይራመዱ የእሳት እራት ሆነዉ ይቀሩ ነበር። ወያኔ ዛሬ በምድርና በአየር የታጠቀዉ መሰሪያና ሰራዊት ደርግ ከታጠቀዉ መሳሪያና ከነበረዉ ወታደራዊ ብቃት ጋር ሲወዳደር እዚህ ግባ የሚባል አልነበረም፤ ሆኖም ለነጻነቱ ቆርጦ የቆመን ህዝብ የሚገታ ምንም አይነት ምድራዊ ኃይል ሰለሌለ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ድጋፍ አግኝቶ ደርግን መደምሰስ ችሏል። የዛሬዉ አምባገነን ወያኔም ዕድል ከደርግ የተለየ አይደለም። ወያኔ ያሰኘዉን ያክል ቢታጠቅ፤ ያሻዉን ያክል የድንበር አካባቢዎችን በታንክና በወታደር ብዛት ቢያጥር . . . . ደፋርና ጭስ መዉጪያ አያጣምና የወያኔ መሸነፍና መደምሰስ ጉዳይ ቀን እስኪያልፍ ያለፋል ካልሆነ በቀር ያለቀለት ጉዳይ ነዉ።
ደርግ ስልጣን በያዘባቸዉ የመጀመሪያዎቹ አምስት አመታት ዉስጥ ወታደራዊ አገዛዝ አንቀበልም ብለዉ ደርግን መግቢያና መዉጪያ ካሳጡት የህብረተሰብ ክፍሎች ዉስጥ ትልቁን ሚና የተጫዉተዉ ወጣቱ ትዉልድ ነበር። ይህ ወጣት ትዉልድ በኢትዮጵያ ህዝብ የዲሞክራሲ ትግል ዉስጥ ምን ግዜም ቢሆን ትዝታዉ የማይደበዝዝ አኩሪ የመስዋዕትነት ትግል ያካሄደና ያለምንም ፍርሃት ዉድ ህይወቱን ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነጻነት መከበር አሳልፎ የሰጠ ጀግና ትዉልድ ነዉ። ዛሬም አዲስ አበባ፤ አዋሳ፤ ባህርዳር፤ ጅማ፤ አምቦ ጊምቢና በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተማዎች የሚኖረዉ ወጣት እኔም አገሬም አብረን ከምንጠፋ እኔ ሞቼ አገሬን አኖራለሁ በሚል ኢትዮጵያዊ እልህ ተነሳስቶ የወያኔን የመጨረሻ እያፋጠነ ነዉ። የወያኔን እገድልሃለሁና አጅ እቆርጣለሁ የሚል ዛቻ ከመጤፍ ሳይቆጥሩ በብዕራቸዉ ህዝብን እያስተማሩ ቃሊቲ ከገቡት ጀግኖች ጀምሮ ከተማ ዉስጥ ከወያኔ ጋር መኖር በቃኝ ብለዉ ጠመንጃቸዉን ተሸክመዉ ጫካ እስከገቡት ቆራጥ አርበኞች ድረስ ኢትዮጵያ ዳግም ትንሳኤዋን ለማብሰር የተዘጋጁ እልፍ አዕላፋት ጀግኖች አሏት።
በገጠሪቱ ኢትዮጵያም መሬቱን ተቀምቶ የተሰደደዉ ወጣት ልክ እንደ ከተማዉ ወጣት በወያኔ ላይ አምርሮ ዱር ቤቴ ብሎ ጫካ ከገባ ቆይቷል። አባቶቹና አያቶቹ ያቆዩለትን መሬት በወያኔ የተቀማዉ የጋምቤላ ገበሬ መሬቴን አለዚያም ህይወቴን ብሎ ወያኔን ማንቀጥቀጥ ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። የሰሊጥ ማዕከል የሆነዉን ለምለም መሬቱን በወያኔ የተቀማዉና ዛሬም የአባቶቹን አጽም የተሸከመዉን መሬት ለባዕዳን ለመስጠት የሚዶለትበት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በወያኔ ላይ ጥርስ ከመንከስ አልፎ ቃታ መሳብ ጀምሯል። እነዚህ ከትግራይ እስከ ጋምቤላ ከጋምቤላ እስከ ጎንደር በአራቱም ማዕዘናት የሚታዩ ህዝባዊ አመጾች የሚያሳዩን አንድ ትልቅ ነገር አለ፤እሱም ወያኔ በህዝብ የተጠላ ብቻ ሳይሆን ህዝብ አንቅሮ የተፋዉ ከቆሻሻም ቆሻሻ መሆኑን ነዉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዘረኝነት በጉልህ ከሚታይባቸዉና በዘረኝነት ፖሊሲ ላይ ተመስርተዉ ከተዋቀሩ አገራዊ ተቋሞች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የመከላከያ ተቋም ነዉ። የኢዮጵያ መከላከያ ተቋም በተለይ ዋናዉን የዉግያና አገርን የመከላከል ስራ የሚሰራዉ የሰራዊቱ ክፍል የተሰባሰበዉ ከመላዉ የአገሪቱ ክፍሎች ቢሆንም ይህ ተቋም ሁለት ፀረ ኢትዮጵያ የሆኑና ሆን ተብለዉ የጎደሉ ጉድለቶች አሉበት።አንደኛዉ ጉድለት ሠራዊቱን በተለያየ ደረጃ ከሚመሩና ከሚያዝዙ ወታደራዊ መኮንኖች ዉስጥ ከ95% በላይ የአንድ ዘር ተወላጆች መሆናቸዉ ሲሆን ሁለተኛዉ ትልቅ ጉድለት ደግሞ በኢትዮጵያ ሠራዊት ዉስጥ አግአዚ የሚባል የአዉሬዎች ክምችት የሚገኝበት አንድ ቋንቋ ብቻ የሚናገሩና ከአንድ ክልል የመጡ ተዋጊዎች ያሉበት ሠራዊት መኖሩ ነዉ። የአገሬን አንድነትና ዳር ድንበር አስከብራለሁ ብሎ ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰበዉ የኢትዮጵያ ሠራዊት በዘር ተከፋፍሎ የወያኔ መጠቀሚያ መሆን ሰልችቶታል።በተለይ ይህ ሰራዊት ብዛቱን በሚመጥን ቁጥር የመሪነትና የአዛዥነት ቦታ ስለማይሰጠዉ ሁል ግዜ በሚንቁትና በሚያንቋሽሹት የአንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች መመራት አንገሽግሾታል። ዛሬ በየበረሃዉ ለሚገኙት የነጻነት አርበኞች እባካችሁ እንገናኝና አገራችንን አንድ ላይ ሆነን ነጻ እናዉጣ የሚል የትግል ጥሪ በተደጋጋሚ የሚመጣዉ ከዚሁ በዘረኝነት አለንጋ ከሚገረፈዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ነዉ። ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ በተለይ ባለፉትሦስት አመታት በኢትዮጵያ ሠራዊት ዉስጥ ትልቁ የመወያያ አርዕስት አንዴት አድርገን የነጻነት እበኞችን እንቀላቀል የሚለዉ ጥያቄ ነዉ። በሠራዊቱ ዉስጥ ሆኖ በዚህ አርዕስት ላይ የማይወያይ የሰራዊቱ አባል ቢኖር እንደ ዘይትና ዉኃ ቅልቅል በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ ባዕድ አካል ሆኖ የሚታየዉ አዉሬዉ የአግአዚ ሠራዊት ብቻ ነዉ። አግአዚ ደግሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት ሳይሆን በኢትዮጵያ ሰራዊት ዉስጥ እንደ እንክርዳድ የበቀለ ፍጹም ባዕድና ጨካኝ የሆነ የወያኔ መገልገያ ነዉ።
ከዚህ በላይ ለመጥቀስ እንደሞከርነዉ ወጣቱ፤ ገበሬዉ፤ ነጋዴዉ፤ ከተሜዉና ወታደሩ ሁሉም ወያኔን የሚቃወም ብቻ ሳይሆን ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን ለመደምሰስ የተዘጋጁ `ኃይሎች ናቸዉ። ባለፈዉ ግንቦት ወር ወያኔ ዘረኝነትንና ሙሰኝነትን ኢትዮጵያ ዉስጥ የተከለበትን ሃያ ሦስተኛ አመት ሲያከብር የኢትዮጵያ ህዝብ የተዋርድንበትን ቀን አናከብርም ብሎ ወያኔ የራሱን በዐል ብቻዉን አክብሮ ዉሏል። ከዚህ በተጨማሪ እጅግ በጣም ብዙ ኢትዮጵያዉያን ይህንን የባርነት ቀን እንደገና ሲከበር ማየት አንደማይፈልጉ በይፋ ተናግረዋል። በእርግጥም ካሁን በኋላ ወያኔ ግንቦት ሃያን ብቻዉንም ቢሆን እንዲያከብር መፍቀድ የለብንም። ደግሞም ወደድንም ጠላን ወይም አወቅን አላወቅን ወያኔ ግንቦት ሃያን የሚያከብረዉ ብቻ ሳይሆን እንዳሰኘዉ ረግጦ የሚገዛን እኛ አሜን ብለን ስለፈቀድንለት ብቻ ነዉ። ህዝብ በአንድ ድምጽ አልገዛም ብሎ አለመገዛቱን የሚያሳይ እርምጃ መዉሰድ ቢጀምር አይደለም በዐል ማክበር ወያኔዎች ሰኞ ያደሩበት ሚኒልክ ቤ/መንግስት ዉስጥ ማክሰኞ ማምሸትም አይችሉም ነበር።
መሬት አልባዉ የኢትዮጵያ ገበሬ ወያኔ እስካለ ድረስ ልጆቼን ብሎ ስለወደፊቱ ማሰብ ቀርቶ የዕለት ጉርሱን የማግኘት ዋስትናም የለዉም። ነጋዴዉም እንደዚሁ ነዉ። ለወያኔ ሙሰኞች ካላጎበደደና ግማሽ ትርፉን ለእነሱ ካልገበረ ነግዶ መኖር ቀርቶ በልቶ ማደር የማይችልበት ግዜ እየመጣ ነዉ። ከተሜዉ ኢትዮጵያዊስ ቢሆን እስከመቼ ነዉ ሰላማዊ ልጆቹ ከጉያዉ እየተጎተቱ ሽብርተኞች ተብለዉ ዕድሜ ልክ ተፈርዶባቸዉ ቃሊቲ ሲገቡ የሚመለከተዉ? እስከመቼ ነዉ ዬት ገቡ ተብለዉ አድራሻቸዉ የጠፋ ልጆቹ መንገድና ህንጻ ሲሰራ የጅምላ መቃብራቸዉ በግሬደር እየተቆፈረ ሲወጣ የሚመለከተዉ? ከኢትዮጵያ ህዝብ አብራክ የወጡት የመከላከያና ፖሊስ ሠራዊት አባላት እስከመቼ ነዉ እነሱ እራሳቸዉ በወያኔ ዘረኝነት እየተለበለቡ ለወያኔ ዕድሜ መራዘም ሲሉ ወንድሞቻቸዉንናነ እህቶቻቸዉን የሚገርፉትና የሚያዋርዱት?
ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ገዳማትን የእርሻ ቦታ አድርጓቸዋል፤ የእምነት ተቋሞችን የክፋቱ መሠረት አድርጓቸዋል፡ ምሁራንን ደግሞ አገራቸዉን ጥለዉ እንዲሰደዱ አድርጓል። ባጠቃላይ ወያኔ ያልበደለዉ፤ ያላሳቀቀዉ ወይም ተስፋዉን ያላጨለመበት የህብረተስብ ክፍል የለም። የገበሬዉ፤ የከተሜዉ፤ የነጋዴዉ፤ የወታደሩ ፤ የወጣቱና የምሁሩ ጠላት ወያኔ መሆኑን ካወቅን ዉለን አድረናል፤ ታዲያ ለምንድነዉ ይህንን የጋራ ጠላት በገራ የማናስወግደዉ? ከዛሬ በኋላ ወያኔ ስልጣን እንደያዘ በሚቆይባት በእያንዳንዷ ቀን የእኛ ስቃይና መከራ መብዛቱ ብቻ ሳይሆን ጥፋቱም የኛ መሆኑን አጥብቀን ልንረዳ ይገባል። ወያኔ እንደሆነ ቀንበር ለመሸከም የተመቻቸ ትከሻ ካገኘ ምን ግዜም ቢሆን ከመግዛት፤ ከማሰርና ከመግደል ወደ ኋላ አይልም። አልገዛም፤ አልታሰርም ወይም አትገድሉኝም ብሎ በወያኔ ላይ መነሳት የዚህ ትዉልድ ኢትዮጵያዉያን ሀላፊነት ነዉ፤ ይህ ሀላፊነት ደግም በህብረት ቆመን ለአንድ አላማ በአንድነት ከታገልን በቀላሉ ልንወጣዉ የምንችለዉ ሀላፊነት ነዉ። ሰለዚህ የዛሬም ጥሪ እንደትናንቱ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወያኔን ለማስወገድ ሀላፊነቱን ይወጣ የሚል ነዉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

አብዛኛው ህዝብ ለመንግስት ጥላቻ አለው” ሲል አንድ ከኢህአዴግ የወጣ ሰነድ አመለከተ

አብዛኛው ህዝብ ለመንግስት ጥላቻ አለው” ሲል አንድ ከኢህአዴግ የወጣ  ሰነድ አመለከተ

 ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ለሚገኙ አመራሮችና አባላት የተደረገውን ስልጠና አስመልክቶ ከብአዴን ጽህፈት ቤት በቁጥር ብአዴን 145/10/ኢህ/06 ለኢህአዴግ ጽ/ቤት  አዲስ አበባ በሚል የተጻፈው ደብዳቤ “አብዛኛው ህዝብ አሁንም ለመንግስት ከፍተኛ ጥላቻ” ማሳየቱን ገልጿል።
የብአዴን አመራር እና አባላቱ ከሰላም የዘለለ የልማት ለውጥ አለመምጣቱን፣ ኢህአዴግ ቢቀጥል ባይቀጥል ግድ እንደሌላቸው፣  እንዲሁም መንግስትን በትክክለኛ ዋጋው ሳይሆን በፍርሃት እንደሚያመሰግኑ በሰነዱ ላይ ተዘርዝሮ ቀርቧል።
“የኢትዮጵያ ህዝቦችና አገራዊ ህዳሴያችን” በሚለው የማጠቃለያ ግምገማ ሰልጣኞቹ ” ስለአገራቸው ታሪክ ብዙ ትምህርት መቅሰማቸውን፣ የህዳሴውን ጉዞ ለማሳካት ድርጅቱ እየከፈለ ያለውን መስዋትነት፣ የኢትዮጵያ ገናና ስልጣኔ ለምን እንደወደቀ፣ የህዳሴ ጉዞውን ሊያሳካ የሚችል መንግስት ያለ መሆኑን፣ የብዝህነትና እኩልነት ሀገራዊ ጠቀሜታ ፣ የአማራ ገዢ መደብ ሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦችን ብቻ ሳይሆን አማራውን ጭምር እንደጨቆነ” የሚያሳይ ትምህርት መውሰዳቸውን ሰነዱ ያመለክታል።
በስልጠናው የብአዴን ታሪክ አብሮ መቅረቡንና ሰልጣኞችም የብአዴንን ታሪክ በማወቃቸው መርካታቸውን ሰነዱ አክሎ ይዘረዝራል።
“ግልጽነት ያልተያዘባቸውና በተግባራዊ እንቅስቃሴ ተከታታይ ውይይትና ስራ የሚጠይቁ ጉዳዮች ምንድን ናቸው?” በሚለው ንጹስ ርእስ ስር ደግሞ ” አሁንም ድረስ ብአዴንን የማይቀበሉ እና ከ97 ጋር በተያያዘ በመንግስት ላይ ተቃውሞ የሚያሰሙ ድምጾች አሉ፣ ነገር ግን የመንግስትን የሃይል እርምጃ ተከትሎ በፍራቻ እንዲኖሩ ማድረግ ተችሎአል።” ሲል አስቀምጧል።
“በውይይቱ ወቅት የታዩ የአመለካከት ችግሮች ምንድን ናቸው?” በሚለው ንዑስ ርዕስ ስር በርካታ ችግሮች ተዘርዝረው ቀርበዋል። ” በ1989 ዓም የነበረው የመሬት ክፍፍል ለቢሮክራቶች ለምን 4 ቃዳ መሬት ተሰጠ? በአማራ ክልል ብቻ የአርሶ አደር መሳሪያ ለምን ተነጠቀ? ልማቱ ወደ ትግራይ ይሄዳል፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አስመራንና አሰብን መያዝ ነበረብን” የሚሉት ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰልጣኞች መቅረቡን ያወሳል።
ሰነዱ በስልጠናው የታዩ ደካማና ጠንካራ ጎኖችንም ይዘረዝራል። ሰልጣኙ እርስ በርስ በመተጋገዝ፣ በመማማር ተሞክሮውን በማካፈልና በመተራረም የነበረው ሁኔታ በሚለው ንጹስ ርእስ ስር ደግሞ ” አሁንም ለመንግስት ህዝቡ በአብዛኛው ጥላቻ ማሳየቱ” የሚል ሰፍሮአል።
የብአዴን አመራርና አባላት ” በአብዛኛው ከሰላም የዘለለ የልማት ለውጥ የለም ” ብለው እንደሚያምኑ፣ “ኢህአዴግ ቢቀጥል ባይቀጥል ደንታ እንደማይሰጣቸው”፣ እንዲሁም “መንግስትን በትክክል ዋጋ ሳይሆን በፍርሃት እንደሚያመሰግኑ” በሰነዱ ማብቂያ ላይ ተገልጿል።
ሰነዱን ለኢሳት የላኩትን የኢህአዴግን ከፍተኛ አመራሮች እንደወትሮው ሁሉ በህዝብ ስም ለማመስገን እንወዳለን።

Step Ethiopians can take to protect themselves from government spying

Step Ethiopians can take to protect themselves from government spying

 
The Ethiopian government has at their disposal a formidable collection of surveillance technologies, and can intrusively monitor writers and activists at home and abroad. In late April the government arrested six independent bloggers and a journalist. More than 50 days later they are still being held in custody, and yet no formal charges have been filed. In March Human Rights Watch published a lengthy and detailed report warning that surveillance in Ethiopia could get even worse if the government gains the human capacity necessary to fully leverage the available technologies.
One of the most invasive and potentially life-threatening things that can happen to an Ethiopian blogger, journalist, activist or dissident is to unwittingly download malware that allows the government to monitor keystrokes and passwords, to remotely turn on a computer’s microphone or camera and start recording, and to extract data from the hard drive. The simplest step Ethiopians can take to protect themselves is to limit the number of documents they download from the Internet. One way to do this is by opening documents as Google Docs.
Until recently, however, Google Docs did not support the Ethiopian language Amharic. Now that they do (and it seems a simple and easy thing to add), Ethiopians have a powerful tool with which to protect themselves from unlawful and intrusive government surveillance.
The Electronic Frontier Foundation has an excellent post explaining how to enable Amharic in Google products, and why Ethiopians should use it (namely, if they are worried about their own government’s surveillance but not concerned that Google will supply their data to US court orders).
I have previously written for techPresident about Angolan investigative journalist Rafael Marques, who discovered intrusive malware on his computer with help from hacker and activist Jacob Appelbaum. Months after the discovery Marques was arrested and beaten.
One of the most relevant points Marques makes is that the malware doesn’t need to be sophisticated because the authorities know or anticipate that he does not have the resources to buy a new, clean computer and to thoroughly protect it.
Is the Google Doc trick infallible? Almost certainly not, but it is a free, easy way for Ethiopians to protect themselves. Think of it like wearing a seatbelt in cyberspace.
Source: http://techpresident.com/news/wegov/251 … rveillance
Source: Andenatethiopia2012

Ethiopians in USA charged with Patronizing Prostitution:

በፊላደልፊያ 3 ሃበሾች በሴተኛ አዳሪዎች ወጥመድ ተያዙ

Police have announced the arrested of seven men in connection to a prostitution bust in Southwest Philadelphia.
Authorities say on June 20th officers from the City Wide Vice Enforcement Unit conducted an operation targeting prostitution in the 12th District.
Undercover decoy officers arrested the following men and charged them with Patronizing Prostitution:
1) James Walker, 45, from the 1000 block of Bullock Avenue in Yeadon, Pa.
2) Mitchell Ballah, 22, from the 100 block of McDade Blvd in Folsom, Pa.
3) Mullugeta Goniche, 30, from the 2500 block of South 70th Street in Philadelphia
4) Shimless Badane, 39, from the 2500 block of South 67th Street in Philadelphia
5) Rudy Lagasca JR, 53, from the 500 block of Devon Road in Norwood, Pa.
6) Oldman Kabban, 37, from the 7100 block of Greenwood in Upper Darby, Pa.
7) HabteMariam Embaye, 32, from the 2500 block of South Claymont Street in Philadelphia
ethiotube

Gov't fails to secure loans for three railway projects

Workneh GebeyehuWorkneh Gebeyehu

- Blames contractors for road sector development poor performance
The Ethiopian government has failed to secure financing for three major railway projects incorporated in the five-year Growth and Transformation Plan (GTP). 
Work on the three projects were supposed to commence in 2013-2014 fiscal year. Presenting a ten-month performance report on Tuesday to the House of Peoples' Representatives, the Minister of Transport, Workneh Gebeyehu, said that the Ethiopian Railway Corporation was not able to embark on the construction of  Awash-Woldiya (Hara Gebeya), Woldiya (Hara Gebya)-Mekelle and Woldiya (Hara Gebya)-Tajura railway projects.
According to Workneh, contact was prepared for the three railway projects and it was planned that financing would be secured and work on the project would commenc in the current year. The minister said the financing could not be secured adding that work on the projects did not commence due to the dearth of financial resource. 
The minister, however, said that the government had been exerting efforts to secure financing for the stated projects. According to him the government was trying to secure loans from the Turkish government and the Swiss Bank. He expressed his hope that loans would be secured from both parties.
Speaking of the ongoing railway projects, Workneh said there was a mid-level accomplishment. According to him, 40 percent of the Addis Ababa-Meiso-Dewele railway line is completed. He also claims that 71 percent of the Addis Ababa light railway line project is finalized. However, sources close to the project reject the performance repot presented by the minister. These sources said that only 40 percent of the work on the Addis Ababa light railway project was done so far.
Regarding the road construction projects, Workneh said low performance rates were registered. Members of parliament asked the reason for the low performance registered in the road development sector. The minister said poor performance of the contractors and problems related to right of way were the major factors contributing to the low performance.

Monday, June 23, 2014

መምህራንን ያገለለው የአሁኑ የወያኔ የደመወዝ ጭማሪ


ለርዕሰ መምሀራን፣ ምክትል ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የደመወዝ ጭማሪ ተደረገ
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ ባገኘው መረጃ መሠረት ለርዕሰ መምሀራን፣ ምክትል ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የደመወዝ ጭማሪ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ኤጀንሲ በ14/9/06 ዓ.ም ለሁሉም ክፍለ ከተሞች በላከው ደብዳቤ እንዳስታወቀው ከሆነ የርዕሰ መምሀራን፣ ምክትል ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች ደመወዝ ላይ ጭማሪ እንዲደረግ በዚህም የተነሳ ለምሳሌ መሪ ርዕሰ መምህር እና ከፍተኛ ሱፐርቫይዘሮች አሁን ከሚያገኑት ደመወዝ ከፍተኛ ጭማሪ ተደርጎ 7768 (ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ስምንት) የኢትዮጵያ ብር እንዲከፈላቸው የተወሠነ ሲሆን መሪ ምክትል ርዕሰ መምህራን ደግሞ 5554 (አምስት ሺህ አምስት መቶ አምሳ አራት) ብር እንዲከፈላቸው ተወስኗል፡፡
የደመወዙን ጭማሪ አስገራሚ የሚያደርገው በአሁኑ ሠዓት ከመምህሩ በላይ በኑሮ ውድነቱ እየተሰቃየ ያለ የመንግስት ሠራተኛ እንደሌለ እየታወቀ መምህራንን ያገለለ የደመወዝ ጭማሪ ማድረግ እጅግ አሳዛኝ ሲሆን ይህንን የተመለከቱ አንዳንድ መምህራን ለኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ እንደገለፁት ከሆነ መንግስት በመምህራን እና በትምህርት ጥራት ላይ እየፈፀመ ያለውን አሻጥር ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ለርዐሰ መምህራኑ ደመወዝ መጨመሩ ተገቢ ሆኖ ሳለ ከ1200 ብር ጀምሮ እየተከፈለው ያለውን መምህር ችላ ማለት ከጀርባው ሌላ እኩይ አላማ እንዳለው ማሳያ ነው፡፡ መንግስት የመምህራኑን ድምፅ ለማፈን ከሚጠቀምባቸው ኃይሎች መካከል ዋነኞቹ የሆኑት ርዕሰ መምህራን እና ሱፐር ቫይዘሮች ሲሆኑ እነርሱን በማስደሠት መምህራኑን ደፍጥጬ እይዛለው የሚል ኋላቀር አስተሳሰብ ውስጥ እንደገባ ማሳያ ሆኗል፡፡
ክቡራን የኢትዮጵያ መምህራን ሆይ
ከዚህ የበለጠ ምንም አይነት መዓት አይመጣም ይህ ከጫካ ይዞት በመጣው አስተሳሳብ ሐገር እየመራ ያለን አምባገነናዊ መንግስት በጋራ እስካልታገልን ድረስ ከዝንብ ማር እንደማይጠበቅ ሁሉ ከወያኔም መልካም ነገር ስለማይጠበቅ መጪው ጊዜ አስፈሪ ነው ስለሆነም በጋራ ከመሞታችን በፊት ስለሐገራችን፣ ስለሙያችን፣ ስለእራሳችንና ስለቤተሠቦቻችን እንዲሁም ስለቀጣዩ ትውልድ ብለን ወያኔ ኢህአዴግን ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅመን ልንቃወመው እና ወያኔን ከመርዳት ልንቆጠብ ይገባል፡፡
የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን እንዳን
ክብር ለኢትዮጵያውያን መምህራን
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
ሠኔ 15/2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በከበባ ተጀምሮ በከበባ የተጠናቀቀው የኢ.ጋ.መ የፓናል ውይይት


ከአምስት ወር በፊት በአስታራ ሆቴል የተመሰረተው የኢትዮጵያ የጋዜጠኞች መድረክ(ኢ.ጋ.መ) ትላንት ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት “የፕሬስ ነፃነት፣የጋዜጠኞች ደህንነት እና ልማት” በሚል ርዕስ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበተት የፓናል ውይይት በአዲስ ቪው ሆቴል አከናውኗል፡፡
የእለቱን መርሀ ግብር በንግግር የከፈተው የኢ.ጋ.መ ም/ፕሬዝዳንት ጋዜጠኛ ስለሺ ሃጎስ ሲሆን በመቀጠልም ሁለት ምሁራን የውይትት መነሻ ሀሳብ አቅርበው በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡
“የኢትዮጵያ ፕሬስ አተገባበሩ፣ተግዳሮቶቹና መፍትሄው” በሚል ርዕስ የመጀመሪያውን የውይትት መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት ዲን ዶ/ር አብዲሳ ዘርአይ ሲሆኑ፤ “የፕሬስና የፀረሽብር ህጉ ከፕሬስ ነፃነት አንፃር” በሚል ርዕስ ሁለተኛውን የውይትት መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት ደግሞ ታዋቂው የህግ ጠበቃና ተንታኝ አቶ ተማም አባቡልጉ ናቸው፡፡
ሁለቱም ፓናሊስቶች በሀገራችን ያለውን ለጋዜጠኞች ደህንነት እና ለፕሬስ ነፃነት ምቹ ያልሆነ ሁኔታ ለማስተካከል ጋዜጠኞች ሙያቸውን ማዕከል አድርገው መሰባሰብና መንግስትን ማስገደድ እንዳለባቸው አበክረው ተናግረዋል፡፡
ውይይቱ እስኪጀመር ማንነታቸው ያልታወቀ ግለሰቦች የስብሰባ አዳራሹን በአይነቁራኛ ሲከታተሉ ቆይተው፤ ዶ/ር አብዲሳ ዘርአይ መነሻ ሀሳብ በማቅረብ ላይ እያሉ አንድ የአካባቢው የፖሊስ ሃላፊ “የውይይቱን አስተባባሪዎች እንፈልጋለን” በማለት የኢ.ጋ.መ ም/ፕሬዝዳንት ስለሺ ሃጎስንና የማህበሩን ጸሀፊ ነብዩ ኃይሉን በአስቸኳይ ውይይቱ ቆሞ ተሰብሳቢዎቹን እንዲበትኑ ቀጭን ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር፡፡ ሆኖም የኢ.ጋ.መ አመራሮች ስብሰባውን እንደማይበትኑ ገልፀው “እራሳችሁ ገብታችሁ በትኑ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አዛዡም በስልክ ከአለቆቻቸው ጋር ከተወያዩ በኋላ “ፖሊስ ለዚህ ስብሰባ ጥበቃ ማድረግ ነበረበት፤ ስብሰባ እንዳላችሁ ልታሳውቁን ይገባ ነበር፡፡ የበላይ ትዕዛዝ ስለሆነ ከዚህ በላይ አንወያይም በአስቸኳይ ስብሰባውን በትኑ” የሚል ማስፈራሪየ አዘል ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ የኢጋመ አመራሮችም “ለጊዜው የፖሊስ ጥበቃ አላስፈለገንም ስለዚህ አላሳወቅናችሁም፤ ውይይቱን ስለማቋረጡ ደግሞ ተነጋግረን ምላሽ እንሰጣችኋለን” በማለት ወደ ስብሰባ አዳራሹ ከተመለሱ በኋላ የውይይቱ መንፈስ እንዳይደፈርስ ለተወያዮቹ ፖሊስ የፈጠረውን ወከባ ሳይናገሩ ቀርተዋል፡፡
ውይይቱ በመቀጠሉ ያልተደሰቱት የፖሊስ አዛዥ ከስብሰባ አዳራሹ በር ላይ ቆመው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ተወያዩ እንዲበተን በማሳሰብ የስብሰባውን መንፈስ እንዲታወክ ሲሞክሩ ጋዜጠኛ ስለሺ ሃጎስ “ገብታችሁ መበተን ትችላላችሁ የቴሌቪዥንም የእኛም ካሜራ አለ ያደረጋችሁት ለህዝብ ይፋ ይሆናል” የሚል ምላሽ ሰጥቷል፤ የፖሊስ አዛዡም “ኢቲቪ አለ እንዴ? እንደውም የኢቲቪ ጋዜጠኞች ካሉ የአንዳቸውን መታወቂያ አሳዩኝና ስብሰባችሁን ቀጥሉ” በማለት አስገራሚ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በፓናል ውይይቱ ላይ ተገኝነው የመንግስታቸውን አቋም እንያስረዱና የውይይት መነሻ ሀሳብ እንዲያቀርቡ በኢ.ጋ.መ የተጋበዙት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማልና የጠ/ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በውይይቱ ላይ ሳይገኙ ቀርተዋል፡፡
ውይይቱ በተሳካ ሁኔታ ከተከናወነ በኋላ ተሳታፊዎቹን በእስር ላይ ለሚገኙ 16 ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችና ብሎገሮች እንዲፈቱ የሚጠይቁ ጽሁፎችን በመያዝና ፎቶግራፍ በመነሳ ለሙያ ባልደረቦቻቸው አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር(ኢ.ጋ.መ) ወደፊትም ተከታታይ የውይይት መድረኮችን እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል፡፡
Nebiyu Hailu's photo.

NO COUNTRY FOR ETHIOPIAN HUMAN RIGHTS ABUSERS

NO COUNTRY FOR ETHIOPIAN HUMAN RIGHTS ABUSERS

By Alemayehu G Mariam
The U.S. Justice Department encourages Ethiopians to report human-rights abusers hiding in plain view in America.
They are hidden in plain view. They have been hiding in plain view in the U.S. for over 30 years. They have been hiding in plain view in the U.S. for just three years.
They skulk around most of the major urban centers from New York City to Los Angeles. They swagger about in public places and places of worship in designer suits with an air of untouchability. They slither in and out of popular coffee shops. They creep in the shadows and alleys. They are highly educated. They are barely literate. They are loaded with cash they stole when they held power. They own property and operate businesses in the U.S. They are service workers eking out a living and struggling to make ends meet. They signed death warrants against innocent victims. They executed innocent victims.
They conceal their true identities by taking aliases to avoid detection. They are known by the victims they tortured and abused, but their victims do not know what they can do to bring their victimizers to justice in American courts. They live in peace and security certain in their knowledge that they have gotten away with murder, torture and various other crimes against humanity while their victims live each day the nightmare of the abuses they have suffered.
THEY are former high-level and low-level Ethiopian junta Derg officials who have committed gross human rights violations and are now hiding out in the U.S. in plain view.
THEY are high-level officials and low-level functionaries of the Tigrean Peoples Liberation Front (TPLF) and its handmaiden the “Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front”.
THEY have gamed the liberal American asylum system and obtained residency or citizenship fraudulently.
THEY believe they have gotten away with murder and will live in the lap of luxury in the United States of America.
THEY need to be brought to justice in American courts!
Worku1 (3)Occasionally, these Ethiopian criminals against humanity hiding out in the U.S. make chance encounters with their victims. In May 2011, Kefelgn Alemu Worku (a/k/a Habteab Berhe Temanu, “TUFA”, Kefelegn Alemu) came face to face with one of his victims in Denver, CO. Worku came to the United States in July 2004 as a refugee using the false identity of Habteab B. Temanu. In the late 1970s, a ruthless military junta known as “Derg” launched a “Red Terror” campaign in Ethiopia resulting in the extrajudicial killings and persecution of hundreds of thousands of citizens. Worku served as a prison guard during that period. Samuel Ketema, an Ethiopian political prisoner in Ethiopia in 1978 testified that Worku tortured and executed fellow prisoners. Abebech Demissie, a 16-year-old high school student detainee in 1977, “watched Worku shoot and kill people, including a teenage boy.” Worku ordered other prisoners to “clean the blood off the floor with anything we could find, including our tongues.” Worku “pointed an AK-47 assault rifle at Abebech’s head but for some reason spared her life.
According to court records, in October 2013 Worku was indicted on various charges including unlawful procurement of citizenship or naturalization, aggravated identity theft, and fraud and misuse of Visas, Permits and Other Documents. Following a five-day trial in U.S. District Court, Worku was convicted on all counts and given a 22-year sentence on May 23, 2014. Generally, similar immigration violations are punished by no more than 18 months in federal prison. But the sentencing judge, U.S. District Judge John L. Kane, was so outraged by Worku’s criminality, he “maxed” him out. Judge Kane explained, “The risk that this country becomes regarded as a safe haven for violators of human rights is such that the maximum sentence is required.”
Assistant U.S. Attorney John Walsh who prosecuted Worku declared, “Our system of justice has successfully removed the defendant from the immigrant community he once terrorized, and in so doing vindicated not only our laws, but the rights of the defendant’s many victims now living here in our country. Today, justice was done. By sentencing defendant Worku to the maximum possible term for his crime, Judge Kane sent a stern, determined message that the United States will not allow its generous asylum laws to be manipulated to create a safe haven for murderers and torturers from abroad.”
Beharu1Last week, famed exiled Ethiopian investigative journalist, Abebe Gellaw, identified one Tewodros Beharu, as “Ethiopia’s prosecutor from hell (hiding in plain view) in America.” Abebe accused Beharu, a resident of Silver Spring, MD., of being a “wilful participant in the unjust and arbitrary prosecution of dissidents, independent journalists and opposition figures using the so-called anti-terrorism proclamation.” According to Abebe, Beharu “fabricated countless treason and terrorism charges against innocent people whose only crime was exposing and challenging the corruption and tyranny of the TPLF.” (Click here to view the ENGLISH copy of the charging document; click here for the AMHARIC version.)
Abebe alleged that “Tewodros Beharu was one of TPLF’s (ruling regime’s party in Ethiopia) prosecutors trained and employed to fabricate terrorism charges against political prisoners like Eskinder Nega, Andualem Aragie, Nathaniel Mekonnen, Reeyot Alemu, Wubishet Taye, Bekele Gerba, Olbana Lelisa, the Muslim community leaders and the two Swedish journalists Johan Persson and Martin Schibbye.” Abebe stated that Baharu had charged him in absentia with “terrorism” as a U.S. citizen along with others including Obang Metho, Neamin Zeleke, Dr. Berhanu Nega, Ephrem Madebo, Fasil Yenealem, Mesfin Negash, Abiy Teklemariam.”
In an electronic communication, Beharu told Abebe that he “was following orders” when he brought the trumped up charges against Eskinder Nega and the rest of the defendants mentioned above. Incredibly, Beharu invoked the “Nuremberg defense” used byNazi perpetrators of war crimes and crimes against humanity. Adolf Eichmann at his trial testified, “I am guilty of having been obedient, having subordinated myself to my official duties and my oath of office. I did not persecute Jews with avidity and passion. That is what the government did.” Likewise, Beharu was just doing his official duty. He is guilty of being obedient and doing his official duties. He did not persecute Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye or dozens of others “with avidity and passion.” That is what the government did.
Serkalem Fasil’s accusations against Tewodros Beharu
The most damning allegations against Tewodros Beharu come from Serkalem Fasil, Ethiopia’s foremost female journalist and publisher until the ruling TPLF regime in Ethiopia imprisoned her and her husband Eskider Nega. Both Serkalem and Eskinder (who is currently serving an 18 year term on trumped up terrorism charges at the infamous Meles Zenawi Kality Prison a few kilometers outside the capital) are arguably the most persecuted and most celebrated dissident journalists in modern African history. Eskinder has been the recipient of practically every major international press award over the past three years including the prestigious 2014 Golden Pen of Freedom which he received a couple of weeks ago. Serkalem is also a recipient of international press awards including the prestigious “Courage in Journalism Award” given by the International Women’s Media Foundation to women journalists that have shown extraordinary bravery in the face of danger.
In a recorded audio interview, Serkalem stated that Tewodros Beharu was not merely “following orders”. He was the one giving the orders in and out of court. Serkalem specifically stated that Beharu persecuted her husband and the others “with avidity and passion.” Beharu was an angry, fierce, harsh, ruthless and pitiless persecutor, according to Serkalem. He went after the defendants not like a professional prosecutor but as political persecutor. Beharu took every opportunity in court to belittle the defendants. He made countless objections to prevent the defendants from introducing exculpatory evidence to show their innocence. He abused procedure to prevent the defendants from receiving a fair trial and to prolong the pretrial detention of the defendants by applying for endless continuances. He fabricated and falsified evidence to obtain a wrongful conviction.
Serkalem specifically alleged that Tewdros Beharu in his individual capacity as a lead state prosecutor knowingly, intentionally and maliciously used his powers to deny her and her husband of due process of law. In 2011, Beharu brought false and unfounded charges against her husband, fabricated evidence, suborned perjury and made allegations and statements he knew to be factually false to secure her husband’s conviction. Serkalem alleged that Beharu falsely alleged Eskinder was a leader of the Ginbot 7 organization and that he had mobilized and recruited youth to engage in terroristic acts. He produced no evidence whatsoever to support this allegation but connived with the judges to convict her husband. She further alleged that prosecutors Beharu and Berhanu Wondimagegn were personally involved in depriving her family of property including homes, cars and other personal property without due process of law. Beharu grossly abused his powers by knowingly, intentionally and maliciously prosecuting other independent Ethiopian journalists and denying them a fair trial and due process including international press award winners Reeyot Alemu, Woubshet Taye and others, according to Serkalem.
Serkalem’s allegations against Tewodros Beharu raise serious legal questions of far reaching implications particularly with respect to the maintenance of the rule of law and the central role played by government prosecutors in protecting innocent victims from human rights abuse. International human rights law requires that prosecutors be active protectors of human rights and must maintain the highest level of integrity under national and international law and ethical standards. Prosecutors are essential to the right to a fair trial and if they abuse and misuse their prosecutorial powers for political ends, they would have committed not only a violation of the principle of the rule of law but also a gross miscarriage of justice for which they must be held accountable.
Both the Universal Declaration of Human Rights (UDHR) and the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR) (the U.S. ratified the ICCPR in 1992 ; incorporated as part of the Ethiopian Constitution under Article 13(1)) guarantee that “everyone is entitled in full equality to a fair and public hearing by an independent and impartial tribunal, in the determination of his rights and obligations and of any criminal charge against him’. (ICCPR, Article 14; African Charter on Human and Peoples’ Rights (ACHPR), Arts. 6-8.) The Rome Statute on the International Criminal Court (ICC), also defines in detail principles of criminal justice (Articles 22-33) and principles of fair trial (Articles 62-67). The Basic Principles and Guidelines on the Right to a Remedy and Reparation for Victims of Gross Violations of International Human Rights Law and Serious Violations of International Humanitarian Law (Adopted and proclaimed by General Assembly resolution 60/147 of 16 December 2005), prescribe that states have an obligation to prosecute individuals suspected of gross violations of international human rights law and serious violations of international humanitarian law that constitute crimes under international law.”
A call to report Ethiopian criminals against humanity hiding in the U.S.
In January 2012, in a commentary entitled, “African Dictators: Can’t Run, Can’t Hide!” I put out a call for Ethiopians in the United States to report Ethiopians living in the U.S. who have committed gross human rights violations to U.S. authorities. In light of the increasing numbers of investigations and prosecutions of human rights violators who have entered the U.S. fraudulently, it is important for Ethiopians in particular to report such suspects to the U.S. Immigration and Customs Enforcement’s (ICE) Homeland Security Investigations (HSI) which operates the Human Rights Violators and War Crimes Unit (HRVWCU) within the National Security Investigations Division (NSID).
HRVWCU “conducts investigations focused on human rights violations in an effort to prevent the United States from becoming a safe haven to those individuals who engage in the commission of war crimes, genocide, torture and other forms of serious human rights abuses from conflicts around the globe. When foreign war crimes suspects, persecutors and human rights abusers are identified within U.S. borders, the unit utilizes its powers and authorities to the fullest extent of the law to investigate, prosecute and, whenever possible, remove any such offenders from the United States.”
Over the past decade, HRVWCU has been quite successful in investigating and arresting hundreds of individuals for human rights-related violations under various criminal and/or immigration statutes. Its large data base contains the names of thousands of known and suspected human rights violators. The data base has been instrumental in preventing identified human-rights violators from attempting to enter the United States. Currently, ICE is pursuing thousands of leads that involve suspected human rights violators from nearly 100 different countries. Over the past 8 years, ICE has arrested hundreds of individuals for human rights-related violations under various criminal and/or immigration statutes and deported hundreds of other known or suspected human rights violators from the United States.
Ethiopian criminals against humanity living in the U.S. must be reported to ICE HRVWCU for investigation
The evidence of widespread crimes against humanity and war crimes in Ethiopia is fully documented, substantial and overwhelming. An official Inquiry Commission report of the TPLF ruling regime in Ethiopia in 2007 documented the extrajudicial killing of at least 193 persons, wounding of 763 others and arbitrary imprisonment of nearly 30,000 persons in the post-2005 election period in that country. There are at least 237 individuals identified and implicated in these crimes. In December 2003, in Gambella, Ethiopia, 424 individuals died in extrajudicial killings by security forces loyal to the TPLF. In the Ogaden, reprisal “executions of 150 individuals” and 37 others were documented by Human Rights Watch in 2008 which charged, “Ethiopian military personnel who ordered or participated in attacks on civilians should be held responsible for war crimes. Senior military and civilian officials who knew or should have known of such crimes but took no action may be criminally liable as a matter of command responsibility. The widespread and apparently systematic nature of the attacks on villages throughout Somali Region is strong evidence that the killings, torture, rape, and forced displacement are also crimes against humanity for which the Ethiopian government bears ultimate responsibility.” These are only the tip of the iceberg.
Why we must take individual initiative to report Ethiopian criminals against humanity hiding in the U.S.
Perhaps the question I have been asked most frequently by Ethiopians over the past several years is, “What can I do as an individual to help improve human rights in Ethiopia?”
Too many Ethiopians, particularly in the Diaspora, feel frustrated by a sense of individual powerlessness. Observing the lack of cohesion among opposition groups and the endless bickering, they stand aside overwhelmed by disappointment. But there are many things Ethiopians can do as individuals to help bring about significant improvements in human rights in Ethiopia.
Last week I called for a boycott of Coca Cola and its 114 different products. When Coca Cola commissioned 32 local versions of the world soccer cup song, released 31 of them and “dumped” the Ethiopian version, I told Coca Cola, “GO TO HELL!!!” I will never, never buy, use or encourage others to buy or use a Coca Cola product. There is no doubt that individuals acting by themselves and collectively can make a difference. Say NO too Coke!
Just last week, it was reported that “Coca-Cola sales nosedived in Spain after boycott call.” Sales of Coca-Cola in Spain slumped by half because the people of Spain told Coca Cola to go to hell!!! (There is substantial anecdotal evidence that a silent boycott of Coca Cola is well underway in Ethiopia.)
If the Spanish can do it to Coca Cola, why can’t Ethiopians?
There are many reasons why Ethiopians with evidence and information on Ethiopian human rights violators hiding in the U.S. should report them to the U.S. Immigration and Customs Enforcement’s Human Rights Violators and War Crimes. First, it is the inescapable moral duty of any Ethiopian who is directly victimized or has personal knowledge of others who are victimized to report human rights abusers hiding in the U.S. Such criminals against humanity must be exposed and removed from American society. Second, reporting such abusers sends a strong message to those violators in official positions in Ethiopia that America will not be a safe haven for them if they should seek asylum fraudulently by concealing their criminal past. If they enter the U.S. they should be prepared to go to jail because they will be fingered and brought to justice. Third, broad participation in such reporting will send a strong message to the regime leaders in Ethiopia who have committed atrocities that if they step inside the U.S., they risk losing not only their fat bank accounts but also their liberty. They should be prepared to spend their last days in an American federal prison. Fourth, if Ethiopian human rights abusers believe that America is not a safe haven for them, they are less likely to engage in crimes against humanity in Ethiopia. There is no question that nearly all of the regime leaders and their cronies today believe they will relocate to the U.S. if things change in Ethiopia. They had better think again!
Knowingly allowing Ethiopian criminals against humanity to live freely in the U.S. is itself a crime against humanity. It is tantamount to being an accomplice after the fact. These human rights abusers hiding in the U.S. should know that justice is like a delayed train. Victims may have to wait a while, but in the end justice shall arrive with its full might. That is the lesson Kefelgn Alemu Worku learned on May 23, 2014. That is a lesson every Ethiopian human rights abuser hiding in plain view in the U.S. should be taught every day. That is a lesson every human rights violator in Ethiopia who plans to relocate to America should learn today.
A lesson in justice for ALL Ethiopians
Last week, 89-year-old Johann Breyer, who lived in Philadelphia for nearly 65 years was arrested and is facing extradition for crimes he committed during WW II as a Nazi guard at the notorious Auschwitz II-Birkenau concentration camp and at another locations. Breyer migrated to the United States in 1952 and claimed citizenship as a displaced person. He deliberately made false statements to minimize his role in the Holocaust in which over 1.1 million men, women, and children were exterminated. German authorities have charged Breyer “with complicity in the murder of more than 216,000 European Jews.”
Kefelgn Alemu Worku is no different from Nazi prison guard Johann Breyer. Worku was a prison guard for the “Derg” junta. Like Breyer, he committed or was complicit in the commission of untold atrocities. He tortured and killed innocent victims. Like Breyer, Worku tried to conceal his identity and criminality when he sought asylum in the U.S. and tried to minimize his role in the Red Terror massacres. Worku, like Breyer, tried to escape justice; but unlike Breyer, justice caught up with Worku in 10 years.
The fact of the matter is that the Ethiopian human rights abusers hiding out in America are not only those who did their dastardly deeds under the Derg regime. There are many who have committed similar human rights abuses as former members or functionaries of the TPLF ruling regime in Ethiopia today. They must ALL be reported.
Whether it takes 6 or 65 years, these abusers who were TPLF or Derg members must be brought to justice. They should know that there is no statute of limitations on justice! Indifference to such criminals living freely in our midst in plain view must end!
I ask ALL Ethiopians one simple question: When the U.S. Justice Department is willing to do ALL of the heavy lifting to prosecute criminals against humanity hiding in the U.S., is it too much to ask Ethiopians to finger these suspects for investigation and prosecution and cooperate with the Department?
It is easy to report human rights abusers hiding out in America- You do NOT have to give your name when you report.
If you have evidence or information about foreign nationals suspected of engaging in human rights abuses or war crimes, call the ICE HSI tip line at 1-866-347-2423 and complete its online tip form.
You do NOT have to give your name when you report.
You may also submit evidence and information to the Human Rights Violator and War Crimes Unit by emailing HRV.ICE@ice.dhs.gov.
Assistance is available to victims of human rights abuses. Call ICE’s confidential victim/witness hotline toll-free number at 1-866-872-4973.
“The United States will not allow its generous asylum laws to be manipulated to create a safe haven for murderers and torturers from abroad.” Assistant U.S. Attorney John Walsh
=====================
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

wanted officials