Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, February 28, 2019

ኖኪያ አምስት ካሜራ ያለው ተንቀሳቃሽ ስልክ ሠራ

ኖኪያ9


ኖኪያ አምስት ካሜራዎች ያለው ተንቀሳቃሽ ስልክ ሰርቶ ይፋ አደረገ።
ኖኪያ9 የተባለው አዲሱ የኖኪያ ተንቀሳቃሽ ስልክ ባልተለመደ መልኩ ከስልኩ ጀርባ አምስት ካሜራዎች ተገጥመውለታል። አምስቱም ካሜራዎች በአንድ ጊዜ በመናበብ የላቀ ጥራት ያለው ፎቶ ያነሳሉ።

ሦስቱ ካሜራዎች ቀይ፣ አረንጓዴና ሰማያዊ ቀለምን ለማመጣጠን ያገለግላሉ። ቀሪዎቹ ሁለቱ ደግሞ መደበኛ ምስል ይወስዳሉ። ካሜራዎቹ በአጠቃላይ በቂ ብርሃን በመስጠት ምስሉ ላይ ጥራትን ከመጨመር ባሻገር በሚነሳዉ ምስል ላይ ምንም አይነት ጥላ እንዳይኖር ያደርጋሉ።
አምስቱም ካሜራዎች እያንዳንዳቸዉ 12 ሜጋ ፒክስል የጥራት መጠን ሲኖራቸዉ በአንድ ላይ ተናበዉ ያለቀለት ምስል እንዲያወጡ ተደርገው ነው የተሠሩት። የስልኩ የጥራት መጠን በአጠቃላይ እስከ 240 ሜጋ ፒክስል ይደርሳል ተብሏል።

ስልኩ በኖኪያ ስም ቢወጣም ሥራው የተከናወነው ከ2016 ጀምሮ በገበያ ላይ በሚገኘዉ ኤች ዲ ኤም ኩባንያ ነው። ኩባንያዉ በእንግሊዝ ብቻ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከ3 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለው ይነገራል።
ስልኩ ስፔን ባርሴሎና ላይ በተከሄደ አውደ ርዕይ ለእይታ ቀርቧል። ኖኪያ9 የመነሻ ዋጋ የተቆረጠለት ሲሆን ለጊዜውም በ699 የአሜሪካን ዶላር እየተሸጠ ይገኛል።

Tuesday, February 26, 2019

የምድራችን ትልቋ ንብ ተገኘች




የዓለማችን ትልቁ ንብ ለዓመታት ጠፍቷል ተብሎ ሲታሰብ በድጋሚ ተገኘ።
የሰውን አውራ ጣት የሚያክለው ትልቁ ንብ የተገኘው በጥቂቱ በተጠናው የኢንዶኔዥያ ደሴት ላይ ነው።
የዱር እንስሳት ባለሙያዎች ለቀናት ካደረጉት ፍለጋ በኋላ ነበር በመጠኗ ለየት ያለችውን ትልቋን ሴት ንብ አግኝነው የቀረጿት።

የዋላስ ትልቁ ንብ በመባል የሚታወቀው የዚህን ተመሳሳይ የንብ ዝርያን ለመጀመሪያ ጊዜ እኤአ በ1858 ባገኘው እንግሊዛዊ የተፈጥሮ ተመራማሪ አልፍሬድ ረስል ዋላስ ስም ነው የተሰየመው።
እኤአ በ1981 ሳይንቲስቶች ብዙ የዋላስ ንብ ዝርያን ያገኑ ቢሆንም ከዚያ ዓመት በኋላ ታይቶ አያውቅም ነበር።
ይህንን ትልቅ ተመሳሳይ የንብ ዝርያ ለማግኘት በጥር ወር አንድ የጥናት ቡድን የዋላስን ኮቴ ተከትሎ ፍለጋውን ለማድረግ ወደ ኢንዶኔዥያ አቅንቶ ነበር።

የመጀመሪያውን ምስል የወሰደው የተፈጥሮ ታሪክ ፎቶ አንሺ ክለይ ቦልት እንደተናግረው "በህይወት ይኑር አይኑር የማናውቀውን ትልቁን በራሪ ንብ ከፊት ለፊታችን በደን ውስጥ እየበረረ ማየት በጣም ድንቅ ነበር" ብሏል።
"በአካል ሲታይ ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ ማየት፤ በትልልቅ ክንፎቹ ከራሴ በላይ ሲበር የሚያወጣውን ድምፅ መስማት በጣም ድንቅ ነበር።"

የዋላስ ትልቁ ንብ (ሜጋቺል ፕሉቶ)
• ወደ 6 ሳንቲ ሜትር የሚጠጋ የክንፍ እርዝማኔ ያለው ሲሆን የዓለማችን ትልቁ የንብ ዝርያ ነው
• ሴቷ ንብ ቤቷን የምትሰራው በምስጦች ኩይሳ ነው። በትልልቅ መንጋጋዎቿም የሚያጣብቅ ሙጫ ተጠቅማ ቤቷን ከምስጦች ትከላከላለች።
•ትልቁ የንብ ዘር በዝቅተኛ ቦታ ላይ ባሉ ዛፎች ላይ ሙጫ ለማግኘት እና በዛፍ ላይ በሚኖሩ ምስጦች ላይ መኖሪያቸውን ለመስራት ጥገኛ ናቸው።
• ከቻርልስ ዳርዊን ጋር የዝገመታዊ ለውጥን ንድፈ ሃሳብ በጋራ እንደሰራ የሚነገርለት ዋላስ ይህንን የንብ ዝርያ "ትልቅ ጥቁር ንብ መሳይ ሆኖ እንደ ጢንዚዛ ትልቅ መንጋጋ ያለው" በማላት ገልጾታል።

በኢንዶኔዥያ ደሴት ሰሜን ሞሉካስ የተገኘው የትልቁ ንብ ጫካው የዓለማችንን ጥቂት ነፍሳት መገኛ ሊሆን እንደሚችል ተስፋ ሰጥቷል።
ወደ ቦታው ያቀናው የምርምር ቡድኑ አባል የሆነው የንብ ተመራማሪ ኢሊ ቂማን እንደሚለው የትልቁ ንብ ዳግም መገኘት ወደፊት ለሚደረገው የንቡ ታሪክ ጥናት እና እንዳይጠፋ ለሚደረገው ምርምር ተስፋ ይሰጣል ብሏል።

ከምድር ለጠፉ ዝርያዎች ዓለም አቀፍ ፍለጋ የጀመረው ግሎባል ዋይልድ ላይፍ ኮንሰርቬሽን የአካባቢ ጥበቃ ቡድን ወደ ኢንዶኔዥያ ለተጓዘው ቡድን ድጋፍ አድርጓል።
"ዝም ከማለት ይልቅ ለጥበቃው እንዲረዳ የተገኘችውን ትልቋን ንብ ምልክት በማድረግ የንቡን ዘር የወደፊት እጣ ተስፋ የሚሰጥ ማድረግ ይቻላል" በማለት ሮቢን ሞሬ ተናግሯል።
በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ንቦችን በማነብ ያለምንም ስጋት የሚኖረው ቤተሰብ።

ትልቋ ንብ

Monday, February 25, 2019

"በወንድሜ ለአምስት ዓመታት ተደፍሬአለሁ"

ጀርባዋ የሚታይ ሴት


መገናኛ አካባቢ የሚገኝ ፀጥ ያለ መንደር ነው። ሰባት ወይም ስምንት የሚሆኑ ልጅ ያቀፉ አፍላ ታዳጊዎች እየተሳሳቁ ከአንድ ትልቅ ግቢ በመውጣት ላይ ነበሩ። ሁሉም ልጅ የያዙና በእድሜም ለእናትነት ገና መምሰላቸው ትኩረት ይስባል። ምን እየተባባሉ እንደሆነ ለመስማትም ያጓጓል።
እነሱን አልፈን ወደ ውስጥ ዘለቅን።
የ23 ዓመት ወጣት ነች። ከገፅታዋ ምንም ነገር ማንበብ አይቻልም። ገፅታዋም ሆነ ሁለንተናዋ ፀጥ ያለ ነው። ከዓመታት በፊት ወደ እዚህ ግቢ ስትመጣ የሥራ ማመልከቻ ለማስገባት ወይም ሥራ ለመጀመር አልነበረም። ይልቁንም በእናቷ ልጅ በወንድሟ ተደፍራ ከደረሰባት ከባድ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ለማገገምና መጠለያ ለመሻት ነበር።
የደረሰባት ነገር ሰው እንድትፈራ አድርጓት ነበርና በሙሉ አይኗ ሰው ማየት ያስፈራት፤ ቃላት አውጥቶ መናገርም ይከብዳት እንደነበር ታስታውሳለች።

"ከባድና እጅግ አሳዛኝ ህይወት አሳልፌአለው" ትላለች ጊዜውን በማስታወስ። የጉዳቷ መጣን በህይወት እየኖርኩ ነው የማያስብል ቢሆንም ያን ቀን አልፋ ዛሬ ቀና ብላ መራመድ ችላለች። ዛሬ የምትፈልግበት መድረስና ህልሟን መኖር እንደምትችልም በእርግጠኝነት ትናገራለች።
ዛሬ ያኔ ተደፍራ የተጠለለችበትና ለተደፈሩ ሴቶች ድጋፍ የሚያደርገው 'የሴቶችና የህፃናት ማረፊያ' ውስጥ ለመሥራት ችላለች።
ምንም እንኳ ያን ጊዜ ማስታወስ ቢያማትም ያለፈችበት መንገድ ሴቶች ለፆታዊ ጥቃት እንዳይጋለጡ አስተማሪ ይሆናል የሚል ፅኑ እምነት ስላላት የሆነችውን ትናገራለች።
ሊያስተምራት አዲስ አበባ ያመጣት ትልቅ ወንድሟ ፖሊስ ነበር። ያኔ እሷ የ16 ዓመት ታዳጊ ነበረች። የሚኖሩት ወንድሟ በተከራየው ቤት ነበር።
"ልጅ ስለነበርኩ ብዙ ነገር አላውቅም፤ መናገርም አልችልም ነበር። ሰው ሳይ ተመሳሳይ ጥቃት ያደርሱብኛል ብዬ ፍራቻ ነበረብኝ" በማለት የነበረችበትን የሥነ ልቦና ስብራት ታስታውሳለች።
ሰው አይቷት ሚስጥሯን የሚያውቅ ይመስላት ስለነበር ትምህርት ቤት መሄድና መመለስ፤ ክፍል ውስጥ መቀመጥም እጅግ ስለከበዳት ትምህርት ቤት መሄድ አቆመች።

ወንድሟ ለአምስት ዓመታት አብረው ሲኖሩ ደፍሯታል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ሦስት ጊዜም ፅንስ እንድታቋርጥም እንዳደረጋት ትገልፃለች።
ልጅነትና የሥነ ልቦና ቀውስ እንዲሁም የወንደሟ ማስፈራራት ለማንም ምንም ትንፍስ ሳትል እንድትቆይ አድርጓት ነበር። ይኖሩ ከነበሩበት ቤት ለቅቀው ሌላ የኪራይ ቤት የገቡበት አጋጣሚ ግን ጉዳቷን አውጥቶ ለመናገር እድል ሰጣት።
በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁኔታዋን ያስተዋሉት አዲሷ የቤት አከራያቸው አንድ ቀን "ለምንድነው ሰው የማትቀርቢው? ዘመዱ ነሽ ወይ?" ሲሉ ድንገት ጠየቋት።
ሁለቱም ጥያቄዎች ለእሷ እጅግ ከባድ ነበሩ። ከምትኖርበት ስቃይ መውጣት ትሻ ነበርና አለባብሶ እንደነገሩ መልስ መስጠት አልፈለገችም። በሌላ በኩል እውነቱን መናገርም መከራ ሆነባት።
እንደምንም ከራሷ ጋር ታግላ የሆነችውን ለአከራይዋ ተናገረች። በነገሩ በጣም የደነገጡት አከራይ ይዘዋት በአቅራቢያ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ለመሄድ ምንም አላመነቱም።
ከፖሊስ ጣቢያ በኋላ ነበር የተደፈሩ ሴቶችን ወደሚያስጠልለውና የሕግ አገልግሎት ድጋፍ ወደሚያደርገው የሴቶች ማረፊያ ልማት ማኅበር የተወሰደችው።

"ቤተሰብ በኔ ፈረደ"
ነገሩ ወደ ሕግ ከሄደ በኋላ ጉዳዩን የሰሙ ቤተሰቦቿ 'እሱ እንዲህ አያደርግም፤ ልጅ ስለሆነች ነው እንዲህ ያለ ነገር የምታወራው' በማለት በፍፁም ሊያምኗት አልቻሉም። በተለይም ትልቅ እህቷ ካለማመን አልፋ የወንድማቸውን ስም ለማጥፋት 'ያልሆነውን ሆነ እያለሽ ነው' በሚል ብዙ ሞግታታለች ዝታባታለችም።
"ከእናቴ ውጪ ቤተሰብ ሁሉ እንደ ቆሻሻ ተፀየፈኝ" በማለት ተበዳይ ሆና እንዴት የበዳይ እዳ ተሸካሚ እንደተደረገች ትናገራለች።
በሌላ በኩል ፖሊስ ጣቢያ በሄደችበት ወቅት ያየችው አቀባበል እንደሷ ያሉ የተደፈሩ ሴቶች ይብስ ፈርተው እንዳይናገሩ የሚያደርግ እንደነበር ታስታውሳለች።
ሃዘኔታ በሌለው አንደበት 'ነይ እዚህ ጋር' 'እዛጋ' 'እስከዛሬ ምን ትሰሪ ነበር?' ተብላለች።

ይህ የእሷ ብቻ ሳይሆን የብዙ ሴቶች አስከፊ እጣ ነው። በማህበረሰቡ እንዲህ ስላደረግሽ ነው፣ እንደዛ ባታደርጊ ኖሮ በሚሉ የምክንያት ድርደራዎች ለመደፈራቸው ራሳቸው ጥፋተኛ ተደርገው አንገታቸውን እንዲደፉ የተደረጉ ሴቶችን ቤት ይቁጠራቸው።
በቀድሞ መጠለያዋ በዛሬው የሥራ ቦታዋ በወንድም፣ በአባት፣ በአያቶቻቸውም ጭምር የተደፈሩና የወለዱ ሴቶችም ጭምር አጋጥመዋታል። ሁሉም በቤተሰባቸውና በማኅበረሰባቸው ለመደፈራቸው ጥፋተኛ የተደረጉና የተወገዙ መሆናቸውን ትናገራለች።
"እኔ ስለ ሕግ ብዙ አላውቅም፤ ግን ካለፍኩበትና ካየሁት በሕግ በኩል ያለው ነገርም ደስ አይልም።"
በተለያዩ ምክንያቶች ደፋሪዎች ነፃ ሆነው የመሄድ እድል ያገኛሉ። በተመሳሳይ በእሷ ጉዳይም ክስ ተመስርቶ የነበረ ቢሆንም ክሱ የትም ሳይደርስ፤ ወንድሟም ሳይጠየቅ መቅረቱን ትናገራለች።
"ህመሜን ተቋቁሜ ችሎት ላይ ብቆምም መጨረሻው አላማረም። እዚህ ላይ ብዙ ማለት አልፈልግም" ትላለች።
"ለመረዳት ፍቃደኛ መሆን አለብን"
ባደረገችው ተደጋጋሚ የፅንስ ማቋረጥ የማህፀን ጉዳት ደርሶባት ለረዥም ጊዜ ህክምና ስትከታተል ቆይታለች። በዚሁ ምክንያት ዛሬም ከባድ የወገብ ህመም ስላለባት ለቃለ መጠይቅ ባገኘናት ወቅትም በሃኪም የታዘዘ የወገብ መደገፊያ ቀበቶ አድርጋ ነበር።
ይህ ሁሉ ቢሆንም ግን "በጣም የተጎዳሁት በሥነ ልቦና ነው። በተለይም የቤተሰቦቼ ነገር በእጅጉ ጎድቶኛል ዛሬም አልወጣልኝም" ትላለች።
ወደ ማረፊያው ከገባች በኋላም ምግብ መብላት፣ ሰው እንዲቀርባትና እንዲያናግራትም አትፈልግም ነበር። ፍላጎቷ አንድና አንድ ነበር። ይቺን ዓለም ለመተው ራሷን ለማጥፋትም ሞክራ ነበር።
በመጨረሻ ከዚህ ያወጣት የተደረገላት የሥነ ልቦና ድጋፍ እንደሆነ ትናገራለች።

ደህና ሆና ወደ ራሷ ከተመለሰች በኋላ ደግሞ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን ወስዳለች። የሴቶች ማረፊያ ልማት ማኅበር ከሙያ ስልጠና በተጨማሪ ለተደፈሩ ሴቶች ራሳቸውን ከጥቃት መከላከል ይችሉ ዘንድ የቴኳንዶ ስልጠና የሚሰጥ ሲሆን እሷም ይህን ስልጠና ወስዳለች።
ሰዎች በጣም ሲጎዱ ብዙ ነገር አይፈልጉም። ምንም ነገር መስማትም መረዳትም ላይፈልጉ ይችላሉ። "ቢሆንም ግን ሰውን መርዳት የሚፈልጉ ብዙ ሰዎች ስላሉ መጀመሪያ እኛ ለመረዳትና ወደፊት ለመራመድ ፍቃደኛ መሆን አለብን" ትላለች።
ካጋጠማት አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጥቃትና ሰቆቃ ለመውጣትና ከባዱን ቀን ለማለፍ ብርታት ያገኘችው ከእራሷ ነበር። "ራሴን ማመኔ፣ የተበላሸ ህይወቴን ማስተካክል እንደምችል ማመኔ ረድቶኛል" ትላለች።
ባይናገሩም ከእሷ የበለጠ ከባድ ነገር ያሳለፉ ሴቶች ይኖራሉ ብላ ታስባለች። ማህበረሰቡ የእንደዚህ ያሉ ሴቶችን ታሪክ ሰምቶ መጠቋቆሚያ እያደረገ እንደገና ቁስላቸውን ባያደማ በታሪካቸው ብዙዎች እንዲማሩና የተሰበሩትም ቀና እንዲሉ ማድረግ ይቻል ነበር የሚል እምነት አላት።
"ሻርፕ ጠምጥመው ስብር ብለው የሚሄዱ ሴቶች ሳይ ሁሌም የእኔ ታሪክ ይመስለኛል" የምትለው ወጣቷ በእንደዚህ ያለ አጋጣሚ ለምታገኛቸው ሴቶች ምንም ባታደርግላቸው እንኳ ገፍታ እንደምታናግራቸውና እንደምትሰማቸው ትናገራለች።
ማኅበረሰቡ የሴቶች ጉዳይ ግድ እንደሚለው ከተማረና ካመነ በብዙ መልኩ እንደ እሷ የተደፈሩ ሴቶችን ሊያግዝ የሚችልበት መንገድ እንዳለ ታምናለች። ከሁሉም በላይ ደግሞ በዚህ ጥቃትን መከላከልም እንደሚቻል ይሰማታል።

ህፃናትም ይሁኑ ታዳጊዎች ያሉት ቤተሰብ በሉ፣ ጠጡ፣ ለበሱ እና ትምህርት ቤት ሄደው መጡ፤ ከሚለው ባሻገር ቤት ውስጥም ሆነ ውጪ ልጆቹ ላይ ጥቃት ሊፈፀም እንደሚችል ማወቅ አለበት። ይህም ልጆችን ለመጠበቅ ያስችላል ትላለች።
"ማን ይፈልገኛል?"
የቀድሞው ፆታዊ ጥቃት ተከላካይ ማኅበር የአሁኑ የሴቶች ማረፊያ ልማት ማህበር በደረሰባቸው ጥቃት የተጎዱ፣ የተሰበሩና 'ማን ይፈልገኛል?' ብለው ራሳቸውን ማጥፋት የፈለጉ በርካታ ሴቶችን ለመደገፍ ጥረት ያደርጋል። ለተደፈሩ ሴቶች የሕግ ድጋፍና የሙያ ስልጠና በመስጠት ከ15 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል።
የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ማርያ ሙኒር ማን ይፈልገናል? በሚል ራሳቸውን ለማጥፋት ሞክረው የነበሩ ሴቶች ከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው ህይወታቸው ተቀይሮ ማየት ለሳቸው ትልቅ ነገር እንደሆነ በየጊዜው ምሳሌ የሚሆኑ ሴቶችን ታሪክ ለሚያወጣው 'ተምሳሌት ገፅ' ተናግረዋል።
ማኅበሩ በአዲስ አበባ፣ በደሴና በሌሎች ቅርንጫፎቹ እያገለገሉ የሚገኙ ኢንጅነሪንግ፣ ማኔጅመንትና ሌላ ሌላም ያጠኑ ወጣት ሴቶችን አቅፏል። ታሪኳን የነገረችን ወጣትም አዲስ አበባ ውስጥ በሙያ አሰልጣኝነትና በሃላፊነት እያገለገለች ነው።

Sunday, February 24, 2019

መጠጥ የ130 ሰው ህይወት ቀጠፈ

በመጠጡ ጉዳት የደረሰባቸው ሕንዳውያን ሠራተኞች


በሻይ ቅጠል ልማት ላይ የሚሠሩ ሕንዳዉያን ባለፈዉ ሀሙስ ለደስታ ብለዉ የተጎነጩት አልኮል ህይወታቸዉን አሳጥቷቸዋል።
እቅዳቸዉ የተለያየ መጠን ያለዉ የታሸገ አልኮል ገዝተዉ ከጓደኞቻቸዉ ጋር መደሰት ነበር።
አልኮሉ የተመረዘ በመሆኑ ግን ከጠጡት ሰዎች መካከል ቢያንስ 130 የሚሆኑት እስከ ትናንት እሁድ ድረስ በተለያዩ ሆስፒታሎች እርዳታ ቢደረግላቸዉም መትረፍ አልቻሉም።
ቢቢሲ ጎላግሃት ሆስፒታል ሲታከም ያገኘዉ ተጎጅ እንደሚናገረዉ፤ መጀመሪያ ምንም የተለየ ስሜት አልነበረዉም። ከደቂቃዎች በኋላ ግን የራስ ምታቱ እየጨመረ በመምጣቱ ለመተኛትም ሆነ ለመመገብ ከተቸገረ በኋላ ራሱን ስቷል።

በዛው ሆስፒታል የሚሰሩት ዶ/ር ራቱል ቦርዶሎይ እንተናገሩት፤ ተጎጂዎቹ ወደ ሆስፒታል ሲሄዱ ከፍተኛ ማስመለስ፣ የደረት ህመም እና የመተንፈስ ችግር ገጥሟቸዉ ነበር።
አብዛኛዎቹ ተጎድተዉ ስለነበርና አልኮሉ መርዛማ ስለሆነ ማትረፍ አልተቻለም። ጉዳዩ በተከሰተበት ሰሜናዊ ሕንድ እስካሁን ከሞቱት 130 ሰዎች በተጨማሪ 200 ሰዎችም በዚሁ የተመረዘ አልኮል ሳቢያ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸዉ ይገኛል።
የተመረዘውን አልኮሉን አሰራጭተዋል የተባሉ ግለሰቦችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል።
ከ2011 ወዲህ ይህን ያህል ሰዉ በተመረዘ አልኮል ምክንያት ሲሞት ለመጀመሪያ ጊዜ ነዉ። በ2011 ዌስት ቤንጋል በተባለዉ የሕንድ ግዛት ውስጥ በተመሳሳይ ክስተት 170 ሰዎች መሞታቸዉ ይታወሳል።

Saturday, February 23, 2019

ሳምሰንግ እንደ መጽሐፍ የሚገለጥ ስልክ አመረተ

እንደ መፅሐፍ የሚገለጠው ሳምሰንግ ተንቀሳቃሽ ስልክ


የሳምሰንግ አዲሱ ምርት ዋጋው ከ50ሺህ ብር በላይ ነው። የተንቀሳቃሽ ስልክ አምራቹ ሳምሰንግ ሦስት በዓይነታቸው ልዩ ያላቸውን የስልክ ናሙናዎች ይፋ አድርጓል።
ከነዚህ ውስጥ አነጋጋሪ የሆነው እንደ መጽሐፍ ይገለጣል የተባለለት ስልክ ነው። በሁለት ወር ውስጥ ለገበያ ይቀርባል ተብሏል።
በኅዳር 2010 "ጋላክሲ ኤስ" ምርቶችን ለገበያ ማቅረብ የጀመረው ሳምሰንግ 10ኛው ኤስ ሰፊ ገበያ ያስገኝልኛል ሲል ተልሞ ነው የተነሳው።
ከዚሁ ታጣፊ ስልክ ጋር አብሮ የቀረበው "ጋላክሲ ኤስ10 5ጂ" ታጣፊ ያልሆነ ቢሆንም ፈጣን ኢንተርኔንትን ለመጠቀም ግብ አድርጎ የተፈበረከ ነው ተብሏል።

ከነዚህ በኤስ10 ስም ከሚቀርቡ ሦስት ምርቶች አንዱ ደግሞ በዋጋ ደረጃ የደንበኞችን ኪስ የማይጎዳ እንዲሆን ታስቧል።
የሳምሰንግ የመጨረሻ ምርት የነበረው 'ኤስ-9" በዋጋው መናር ምክንያት ሽያጩ ከተጠበቀው በታች ስለነበረ ድርጅቱ ትምህርት ወስጃለሁ ብሏል።
ይህ እንደ መጽሐፍ ይገለጣል የተባለለት ቅንጡ ስልክ የሁለት መጠነኛ ስልኮች ስፋት ሲኖረው ወደ ጎን 18.5 ሴ.ሜ ይረዝማል።
ሲዘረጋም ታብሌት እንጂ ስልክ አይመስልም። ዋናው አገልግሎቱ ደንበኞች በአንድ ጊዜ ሦስት መተግበሪያዎችን መጠቀም እንዲችሉ ነው።
እንደ መጽሐፍ የሚገለጥ ሳምሰንግአንድ ሰው በዚህ ታጣፊ ስልክ ዩቲዩብ ቪዲዮ እያየ፣ ማየቱን ሳያቋርጥ ስለፊልሙ ከወዳጁ ጋር በአጭር መልዕክት እየተላላከ ከጎን ሌላ ተጨማሪ መተግበሪያን ከፍቶ ያሻውን ማድረግ ያስችለዋል።
ይህ ታጣፊ ስልክ 6 ካሜራዎች ሲኖሩት ሦስቱ ከጀርባ፣ ሁለት ከጎን አንድ ደግሞ ከፊት ለፊት ይገኛሉ። ይህም ስልኩን በየትኛውም ሁኔታ ይዞ ፎቶ ማንሳት ያስችላል ተብሏል።
ከዚህም ባሻገር አንድን ምሥል አቅርቦና አርቆ ፎቶ ለማንሳት የሚያስችሉ መተግበሪያ ቁልፎች ተዘጋጅተውለታል።
ሳምሰንግ "ኤስ 10" ገመድ አልባ ቻርጀር ስላለው አብረው የሚሸጡትን የጆሮ ማዳመጫዎችንና ሌሎች ባትሪ የሚሹ ቁሶችን ቻርጅ ማድረግ ይችላል።
ይህ ስልክ ዋጋው በብር እስከ 56 ሺህ ይጠጋል። ቁርጥ ያለው ዋጋው በዶላር 1ሺህ 9መቶ 80 እንደሆነ ሲነገር በአዳራሹ የነበሩ ታዳሚዎችን አስደንግጧል።

የዛሬ 74 ዓመት የተሳመው 'ከንፈር' ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

የአውድ ርዕይ ጎብኚ ምሥሉን በተንቀሳቃሽ ስልኩ ሲያነሳ

Image copyright AFP
አጭር የምስል መግለጫ ምሥሉ በዓለም ዙሪያ በትልልቅ አውደ ርዕዮች ቀርቦ አድናቆትን አትርፏል
እጅግ ከሚወደዱና ከተጨበጨበላቸው ፎቶግራፎች አንዱ ነው። በአሜሪካ ብቻም ሳይሆን በዓለም ዙርያ ይህ ምስል ተወዳጅ ነው። ዝነኛም ነው። ስሜት ኮርኳሪም ነው። ያለ ምክንያት ግን አይደለም።
2ኛው የዓለም ጦርነት ማብቃቱን ተከትሎ አንድ የአሜሪካ ጦር መርከበኛ ድንገት በኒውዮርክ ጎዳና ላይ የነበረችን ቆንጆ ጎተት አድርጎ ከንፈሯን ጎረሰው። ምንም አላስተረፈም።
ያን ቅጽበት የፎቶ ጥበበኛው አልፍሬድ አይዠንስታድ በካሜራው አስቀረው። ያ ምሥል 'ላይፍ' በተባለው መጽሔትም ታተመ። ከዚያ ወዲህ በመጽሔቱ ብቻ ሳይሆን በሚሊዮኖች ልብ ላይ የታተመ የዓለማችን እጹብ ድንቅ ፎቶ ሆኖ ኖረ።

ያ ጎበዝ ሳሚ መርከበኛ ስሙ ጆርጅ ማንዶሳ ይባላል። በተወለደ በ95 ዓመቱ ትናንት ማረፉ ተሰምቷል።
የ21 ዓመቷ ተሳሚ ቆንጆ ግሬታ ዚመር ፍሬድማን ትባላለች። በ2016 ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው። ኖራ ኖራ በ92 ዓመቷ ማለት ነው።
የፎቶግራፍ ጥበበኛው አልፍሬድ አይዠንስታድ ያኔ ሳሚና ተሳሚዎቹ እነማን እንደሆኑ ሁሉ አልገለጸም ነበር። ኋላ ነው ነገሩ ይፋ የሆነው።
እንደመታደል ኾኖ መርከበኛው የደንብ ልብሱን ለብሶ ድንገት እየበረረ አንዲትን ቆንጆ ሲስም ቅጽበቱን በካሜራ ቀለበው። ነገሩ ችሎታ ከምንለው ዕድል ብንለው ይቀላል። ይህ የሆነው ነሐሴ 14 ቀን 1945 ነበር።
"ድንገት በካሜራዬ ሌንስ ውስጥ አንድ ጉብል [ከሰልፍ መስመር ወጥቶ] ድንገት አንዲት ኮረዳን እንቅ አድርጎ ሲስማት ተመለከትኩ። የካሜራዬን ቁልፍ ተጫንኩት። ኮረዳዋ ነጣ ያለ የነርስ ደንብ ልብስ ነበር የለበሰችው። [ጎልታ ትታየኝ ነበር] እንዲያ ባትለብስ ኖሮ ይህን ምስል ስለማግኘቴ እጠራጠራለሁ" ብሎ ነበር፤ አልፍሬድ።

ወይዘሪት ፍሬድማን ያኔ የጥርስ ሐኪም ረዳት ነበረች። ስለዚያ አስደናቂ ፎቶግራፍ ያወቀችው ግን ምስሉ ከወጣ ከ16 ዓመት በኋላ በ1960 ነበር።
"ያን ያህልም እኮ የፍቅር መሳሳም አልነበረም። እንዲሁ በፈንጠዚያ ላይ ነበርን፤ በቃ ይኸው ነው" ብላ ነበር፤ ስለዚያ ፎቶግራፍ ስትናገር።
ዓለም ግን ይህን ፎቶግራፍ በዚያ መንገድ አልወሰደውም። ከብዙ እልቂት በኋላ ጃፓን ለአሜሪካ ጦር እጅ የሰጠችበትና የአሜሪካ አሸናፊነት የተበሰረበት ዕለትም በመሆኑ የዚያ ፎቶግራፍ ትርጉምና ዝና በአያሌው ገዝፎ ኖሯል።

የኦነግ አባላት ከነበሩባቸው ቦታዎች እየተመለሱ ነው ተባለ


በመንግሥትና በኦነግ መካከል በአባገዳዎችና በሽማግሌዎች አማካይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የግንባሩ አባላት ከነበሩባቸው ቦታዎች በሰላም እየተመለሱ መሆናቸው ተነገረ።
በምዕራብ ኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው የኦነግ ኃይል አዛዥ ኩምሳ ድሪባ ወይም በትግል ስሙ  መሮ በመባል የሚታወቀው ግን ይህንን ለመፈፀም ዝግጁ አይደለም ተብሏል።

በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተሰማርተው የሚገኙ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጦር አባላት የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትለው ትጥቅ ፈትተው ወደ ጦር ካምፖች ከመግባታቸው በፊት ወደተዘጋጁላቸው ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራዎች እየገቡ መሆኑ ታውቋል።
ለዚሁም አባገዳዎችባ የየአካባቢዎቹ ባለስልጣናት ለውሳኔው ተገዢ  የኦነግ አባላት  ወደተዘጋጁላቸው ስፍራዎች ከነትጥቃቸው ሲመጡ አቀባበል እያደረጉላቸው መሆናቸው ነው የተነገረው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትሎ ሁሉም የኦነግ ጦር አባላት እየተመለሱ አለመሆናቸው ተነግሯል።
ለዚህም እንደምክንያት የሚጠቀሰው የምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ የሆነው ኩምሳ ድሪባ ወይም በትግል ስሙ መሮ የአባገዳዎችን ጥሪ አለመቀበሉ ታውቋል።
በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኘው የኦነግ ጦር አዛዥ እንደሆነ በስፋት የሚነገርለት ኩምሳ ድሪባ (መሮ) ከቢቢሲ ጋር የስልክቃለምልልስ ማድረጉ ነው የተነገረው።
በዚሁቃለምልልስም መሮ ባለው ሁኔታ ስምምነቱን ተቀብሎ ለመግባት ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።
የአባገዳዎችን ጥሪ ለመቀበል እና እርቅ ለማውረድ ዝግጁ ስለመሆኑ ተጠይቆ “የእርቅ  ኮሚቴው  አባላት እኔን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ፍላጎት የላቸውም ብሏል።
ትኩረት ያደረጉት ጦሩን አንድ በአንድ እጁን እንዲሰጥ ማድረግ ላይ ነው” በማለት እሱም እነሱን ለማግኘት ያደረገው ጥረት አለመሳካቱንም ነው የገለጸው።
እንዲያውም “ጦሩን የመበታተን ዓላማ ይዘው ነው እየተንቀሳቀሱ ነው ሲል የእርቅ ኮሚቴ አባላትን ወቅሷል።
“ወደፊት መራራ ትግል ማድረጋችንን እንቀጥላለን” ያለው መሮ “ብቻዬን ብቀር እንኳ ትግል ማድረጌን እቀጥላለሁ እቅዴም ይሄው ነው” በማለት በትጥቅ ትግሉ እንደሚቀጥል ገልጿል።
በተያያዘ ዜናም የኦነግ አባላት ትጥቅ ፈተው በሰላማዊ መንገድ ወደ ካምፕ እንዲገቡ ለማድረግ ወደ አካባቢው የተጓዙት አባገዳዎች መታገታቸው ተሰምቷል።
ከአባገዳዎቹ መካከልም ድብደባ የተፈጸመባቸው መኖሩም ነው የታወቀው።
ቁጥራቸው በውል ያልታወቀውና ታግተዋል የተባሉት አባገዳዎች ይሄ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ የታወቀ ነገር የለም።

Thursday, February 21, 2019

በለገጣፎ አንድም የተፈናቀለ ዜጋ የለም ተባለ

በለገጣፎ ተፈናቅሎ ሜዳ ላይ የተጣለ አንድም ዜጋ የለም ሲሉ የለገጣፎ ከተማ ከንቲባ ገለጹ።
እስካሁንም ህገ ወጥ በሚል የፈረሰ ቤት የለም፣ የፈረሱትም በመንግስት ቦታ ላይ የተገነቡ ቤቶች ናቸው ብለዋል።

የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው ግን ክልሉ ለከተሞች ልማት ከሰጠው ትኩረት ጋር በተያያዘ በህገወጥ የተገነቡ ቤቶች እየፈረሱ መሆኑን ገልጸዋል።
ሕጋዊ ከሆኑ ደግሞ መራጃ እንዲያቀርቡ አስቀድሞ ተጠይቀዋል ብለዋል።
ተፈናቃዮቹ በበኩላቸው ለሚመለከተው አካል ማስረጃችንን ካቀረብን በኋላ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ቤታቸው መፍረሱን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል እስካሁን በህገወጥ መንገድ ተገንብተዋል የተባሉ ከ3ሺ ቤቶች በላይ መፈረሳቸውን ነው ከክልሉ ያገኘንው መረጃ ያገኘንው።
በቅርቡ በኮልፌና በኦሮሚያ ክልል መካከል በሚገኘው አካባቢ ህገወጥ ተብለው የተፈናቀሉት ከ1 ሺ በላይ ነዋሪዎች ሰሞኑን ደግሞ በለገጣፎ ሜዳ ላይ እንዲወድቁ የተደረጉትናቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ዜጎች የተፈናቀሉትም ከዚሁ ከህገወጥ ግንባታ ጋር በተያያዘ ነው ተብሏል።
የለገጣፎ ከንቲባ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ ደግሞ አንድም ዜጋ በለገጣፎ ሜዳ ላይ አልወደቀም፣ሕገ ወጥ በሚልም የፈረሱ ቤቶች የሉም ብለዋል ለኢሳት በሰጡት ምላሽ።
ቤቶቹ በሰባት ቀን እንዲፈርሱ የተደረገበት ምክንያትም አግባብነት አለው ብለዋል ወይዘሮ ሃቢባ።
የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊው አቶ አድማሱ ዳምጠው ለኢሳት እንዳሉት ደግሞ በህገወጥ መንገድ የተገነቡ ቤቶች ፈርሰዋል። ይሄ ደግሞ ክልሉ በእቅድ ይዞት እያከናወነው ያለ ተግባር ነው።
የኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊው አቶ አድማሱ እንደሚሉት ከሆነ ህገወጥ ቤቶቹ ከመፍረሳቸው በፊት ማስጠንቀቂያ ተሰቷል።አማራጭ የሚሆኑ ቦታዎችም ተዘጋጅተውላቸዋል እነሱ ግን ፈቃደኛ አልሆኑም ነው ያሉት።
የተደረጉትን ጥናቶች መሰረት በማድረግ ህገወጥ ግንባታዎችን የማፍረሱ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት አቶ አድማሱ ከዚህ በፊት እንደተደረገው ሁሉ ቤቶቹ ከመፍረሳቸው በፊት ግለሰቦቹ ህጋዊ ማስረጃዎችን እንዲያቀርቡ ጠጠይቀዋል ብለዋል።
ተፈናቃዮቹ በበኩላቸው ህጋዊ ማስረጃ ብናቀርብም ቤታችን ከመፍረስ አልዳነም ይላሉ።

አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ


አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ለ3ኛ ጊዜ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በጥረት ኮርፖሬት ተፈፅሟል በተባለ የሀብት ምዝበራ የተጠረጠሩት አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ለሶስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ተጨማሪ የ14 ቀን ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ በጥያቀው ላይ ወሳኔ ለመስጠት ለ ሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቢ ህግ ተጨማሪ ምርመራዎችን ለማድርግ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
አቃቤ ህጉ ዳሽን ቢራ ዲዮት ለተባለው የእንግሊዝ ኩባንያ የአክሲዮን ድርሻ የሸጠበትን 96 ሚሊዮን ዶላር የት እንዳደረሰው አልታወቀም ሲል እነ አቶ በረከትን ሲወነጅል እንደነበር ይታወሳል።
እነ በረከት ስምዖን እና ታደሰ ካሳ የጥረት አመራር በነበሩበት ጊዜ የኩባንያውን ሀብት በማባከንን በሌብነት ተጠርጥረው መታሰራቸው ይታወሳል።
የክልሉ ጸረ ሙስና አቃቤ ህግ ይ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀው የዳሽን ቢራ የሂሳብ ኦዲት አለመጠናቀቅ የጥረት ኮርፖሬት የአክሲዮን ሽያጭ ህጋዊነት በባለሙያ ማስፈትሽ ስላስለፈለገ ነው ብሏል።
ከዢህ ጋር በተያየዘም 2 ዋነኛ ምስክሮች ከሀገር ውጪ ስለሆኑ የሚመለሱበትን ቀን ታሳቢ በማድረግ ጥያቄው መቅረቡንአቃቤ ህግ  በምክንያትነት ገልጿል።
እነ አቶ በረከት ግን ኦዲቱ ባልተጠናቀቀ ጉዳይ ነው ወይ መዝብረዋል በሚል የተከሰስነው ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል ተብሏል።
ይህ ተገቢ አይደለም አቃቢ ህግ ሆን ብሎ እኛን በእስር ለማቆየት የሚያቀርበው ምክንያት ነው ሲሉም ተጨማሪ ይ 14 ቀን የምርመራ ጊዜውን ተቃውመዋል ።
ጉዳዩን እየተመለከተ ያለው ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ያስፈልጋል ወይ የሚለውን ለመወሰን ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።
ይሕ በእንዲህ እንዳለም አቶ በረከት ስምዖን የእስር አያያዛቸውን በተመለከተ ጠባቂዎችን እያሰቸገሩ መሆናቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
የታሰረነውም ሆነ ፍርድ አየተሰጠን ያለው በማህበራዊ ሚዲያ ሰለሆነ ይሕንን ለመከታተል እንድንችል ኢንተርኒት ይግብላን የሚሉት አቶ በረከት ጠባቂዎችን ኢሳት ምን አለ እያሉ መረጃ ለማግኘት እንደሚያስቸግሩ ለማወቅ ተችሏል።
አቶ በረከት ስምኦን እና አቶ ታደሰ ካሳ በአሁኑ ጊዤ የተፈቀደላቸው  ሬዲዮ ብቻ መሆኑም ምንጮች ገልጸዋል።

Wednesday, February 20, 2019

በምዕራብ ጎንደር 138 ግለሰቦች በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው ታሰሩ

በምዕራብ ጎንደር ዞን ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ 138 ግለሰቦች በሕይወት ማጥፋትና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው መታሰራቸው ተነገረ።
በግጭቱ ሳቢያ 37 ሰዎች በነፍስ ግድያ፣ 101 ግለሰቦች ደግሞ በስርቆትና በሌሎች ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር አስታውቋል ።

በምዕራብ ጎንደር  ግጭት ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ የቡድን የጦር መሣሪያ ጥይቶችና መሳሪያዎች  መያዛቸውም ተነግሯል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ 138 ግለሰቦች በነፍስ ግድያና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው የተያዙት በመከላከያ ሰራዊት አባላት ነው።
ጥይቶቹ የተያዙትማ በመተማ ዮሐንስ ከተማ በተቃጠሉ ግለሰቦች ቤት ውስጥ መሆኑን የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር 1ኛ ብርጌድ 1ኛ ሻለቃ አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል አንገሶም አርአያ ተናግረዋል ።
ከጦር መሳሪያ ጥይቶቹ በተጨማሪ ሃሰተኛ የብር ኖቶች፣ አደንዛዥ ዕፆች፣ የቅስቀሳ መሣሪያዎች (ድምጽ ማጉያ) እና የተለያዩ ሰነዶች በቁጥጥር ስር ውለዋል ነው ያሉት ።
ከዚህ ባለፈም የእጅ ቦንብም፣ የቅንቡላ፣ የአርፒጂ (የላውንቸር) እና የብሬንና ጥይቶችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ሌተናል ኮሎኔል አንገሶም አንስተዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት የጦር መሳሪያ ጥይቶችን ለታንክ እና ለከባድ ምሽግ ማጥቂያ የሚያገለግሉ ሆነው ለሃገር መከላከያ ሠራዊት እና ለተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ብቻ የሚፈቀዱ እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡
ክላሽ፣ ሽጉጦች፣ ስለታማ መሣሪያዎች፣ የፌዴራል ፖሊስና የሀገር መከላከያ የደንብ ልብሶችም በተቃጠሉ ቤቶች ውስጥ መገኘታቸውንም  ሌተናል ኮሎኔሉ አረጋግጠዋል።
አሁን የተገኙት የቡድን መሣሪያዎቹ ጥይቶች ናቸውም ብለዋል።
አሁንም ተጨማሪ የጦር መሳሪያዎች በግለሰቦቹ እጅ እንዳሉ እንደሚታመን ጠቁመዋል።
በምዕራብ ጎንደር የህብረተሰቡን ሰላም ለመጠበቅ መከላከያ ሰራዊት ከክልሉ ፖሊስና ከአካባቢው የፀጥታ አካላት ጋር  ተቀናጅቶ እየሠራ መሆኑን ነው የገለጹት።
ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር በሚውሉበት ጊዜ መንግሥት በቶሎ ለህግ እያቀረበ አለመሆኑን የአማራ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል ።

በጎንደር የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የሚከልከል መመሪያ ወጣ


በጎንደር በተወሰኑ አካባቢዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የሚከልከል መመሪያ በአማራ ክልል ይፋ ተደረገ።
መመሪያውን ለማስፈጸም ከመከላከያ ሰራዊት ፥ከክልሉ ፖሊስና የጸጥታ ሐይሎች የተወጣጣ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ዘላለም  ልጅአለም ከኢሳት ጋር ባደርጉት ቃለ ምልልስ አስታወቋል።

ይህ ጸጥታን በጥምር ወታደራዊ እዝ የማስከበሩ ስራ በመመሪያ መልክ የወጣ እንጂ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አለመሆኑንም አቶ ዘላለም ገልጸዋል።
በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች የተከሰተውን ግጭት ለማርገብ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን በተመለከተ የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጎንደር ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
መግለጫውን የሰጡት የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል አለምነው አየነ እና የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጃለም ናቸው፡፡
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ዘላልም ልጅ አለም ለኢሳት እንደገለጹት በጎንደር  በተወሰኑ አካባቢዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የሚከልከል መመሪያ በአማራ ክልል ትግባራዊ መሆን ጀምሯል።
መመሪያውን ለማስፈጸም ከመከላከያ ሰራዊት ፥ከክልሉ ፖሊስና የጸጥታ ሐይሎች የተወጣጣ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ዘላለም  ልጅአለም ከኢሳት ጋር ባደርጉት ቃለ ምልልስ አስታወቋል።
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር መሰማራቱን  በመግለጫው ይፋ ተደርጓል፡፡
በዚህም መሠረት ከጎንደር-መተማ መስመር ከመንገድ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም፤ በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ ክልከላ ተደርጓል፡፡
በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሣሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ እንደማይችልም ነው የገለጹት፡፡
የክልሉ አስተዳድር ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም እንዲያስከብር ተድርጓልም ብለዋል፡፡
የፖሊስ ኮሚሽነሩ አቶ ዘላለም ልጃለም እንዳሉት ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል እርምጃ እንደሚወሰድበትና ‹‹ሰላም ለማስከበር›› በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፈቃድ ውጭ መሣሪያ ይዞ እንዳይንቀሳቀስ እገዳ ተላልፏል፡፡
እናም ከኮሚሽኑ ፈቃድ ውጭ መሣሪያ ይዞ እንዳይንቀሳቀስ እገዳ  ነው ያሉት።
በመግለጫው የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋልም ብለዋል፡፡

ኦዴፓ በብሔሮች ራስን የማስተዳደር መብት ላይ አልደራደርም አለ


በፌደራል ስርዓቱ በብሄሮች ራስን የማስተዳደር መብት ላይ ከማንም ጋር እንደማይደራደር  የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) ገለጸ።
ፓርቲው  ባወጣው መግለጫ በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እየተካሄደ ነው ብሏል።

የአዲስ አበባ ልዩ ጥቅም እና የአፋን ኦሮሞ ሁለተኛ ብሄራዊ ቋንቋ እንዲሆንም እየተሰራበት  መሆኑን ኦዲፒ ገልጿል።
ኦዴፓ በአጀንዳነት ይዞ ከሚታገልባቸው ጉዳዮች መካከል ዋነኛው የፌደራል ስርዓቱ ነው ብሏል።
እንደ ድርጅቱ መግለጫ ለፌደራል ስርዓቱ መምጣት ብሄረሰቦች ከፍተኛ ዋጋ ከፍለዋል።
እናም የፌዴራል ስርአቱ እና ብሔሮች ራሳቸውን የማስተዳደር መብት ለድርድር አይቀርብም ነው ያለው ።
በአሁኑ ወቅትም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የፌዴራል ስርዓቱን ሊያፈርስ እንደሆነ ለማድረግም እየተሰራ ነው ብሏል።
ህብረተሰቡ በፌዴራል ስርዓት ላይ ያለውን እምነት እና ተስፋ እንዲቀንስ ከፍተኛ የሆነ የሀሰት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጿል።
ኦዴፓ እንደሚለው የሀሰት ዘመቻው ሁለት ዓላማ ያለው ነው ።
አንደኛው የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሁን ያለውን ለውጥ በጥርጣሬ እንደሚመለከቱ ማድረግ መሆኑን ነው የገለጸው።
ብሔሮችና ብሄረሰቦች የራሳቸውን ባህል፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ታሪክ ማሳደግን በትግል እና በመስዋዕትነት ያገኙት ቢሆንም የፌደራል ስርዓቱ ሊፈርስ ነው በሚል በጥርጣሬ ተቃውሞ እንዲያስነሱ ታስቦ የሚደረግ ሴራ መሆኑንም ገልጿል።
የኦሮሞን ህዝብ “ተጨማሪ መብት ማግኘት ቀርቶ ከዚህ ቀደም የተገኘውን መብት ልታጣ ነው” በሚል በማደናበር እርስ በርስ ለማጋጨት ያለመ መሆኑንም ኦዲፓ አስታውቋል።
የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄን በመግለጽ የአዲስ አበባ ልዩ ጥቅም እና የአፋን ኦሮሞ ሁለተኛ ብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆንም እየተሰራበት  መሆኑን ኦዴፓ ገልጿል።
ከፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጥያቄዎች ላይም ትኩረት በመስጠት እየሰራበት መሆኑን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል።
ኦዴፓ ለተጨማሪ ድል ይሰራል እንጂ ከዚህ ቀደም የተገኙ ድሎችን አያከሽፍም ያለው ፓርቲው፥ በፌደራል ስርዓት ጉዳይ ላይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ በመግለጫው አስታወቋል።

የማረሚያ ቤት የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ


ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ላይ በደረሰው ቃጠሎ በተነሳው ረብሻ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል በሚል የተጠረጠሩ የማረሚያ ቤት የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ።
ተከሳሾች በፌደራል ማረሚያ ቤቶች የቂሊንጦ፣ የዝዋይ እና የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት በተለያየ የሃላፊነት ደረጃ ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውም ተገልጿል።
ፋይል
የክሱ ዝርዝር እንደሚያስረዳው ነሃሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም ጠዋት በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ላይ በደረሰው ቃጠሎ በተነሳው ረብሻ ምክንያት ከኃላፊዎች በተሰጠ ትዕዛዝ በማረሚያ ቤት የፖሊስ አባላት በተተኮሰ ጥይት በታራሚዎች ላይ ከባድ አካላዊ ጉዳትና ህይወታቸው እንዲያልፍ ተደርጓል።
ተከሳሾች ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ አብርሃ፣ ሱፐር ኢንተንደንት አስገለ ወልደጊዮርጊስ ወልደማርያም፣ ዋና ሱፐር ኢንተንደንት  አሰፋ ኪዳኔ ተድላ፣ ሱፐር ኢንተንደንት ገብረእግዚአብሄር ገብረ ሃዋርያት፣ ሱፐር ኢንተንደንት ተክላይ ሀይሉ ተክለ ሃይማኖት፣ ሱፐር ኢንተንደንት አቡ ግርማ ወልደሚካኤል፣ ሱፐር ኢንተንደንት አዳነ ሀጎስ ህሻ እና ሱፐር ኢንተንደንት ገብራት መኮንን ገብሩ ናቸው።
በክሱ እንደተመለከተው በማረሚያ ቤት ቃጠሎ ምክንያት ከ400 በላይ የሚሆኑ ታራሚዎችን ወደ ሸዋሮቢት ተሃድሶ ልማት ማረሚያ ቤት እንዲወሰዱ ተደርገዋል ።
በዚሁ ጊዜም የነበራቸውን ንብረት በመቀበል በባዶ እግራቸው በቁምጣ ብቻ በተሽከርካሪ ላይ እንዲጫኑ በማድረግ፤ ሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ሲደርሱም በመስመር በማሰለፍና በማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት በዱላ ተደብድበዋል ነው የተባለው።
175 የሚሆኑ ታራሚዎችን ደግሞ ባዶ ቤት የሲሚንቶ ወለል ላይ እንዲተኙ በማድረግ፣ ለሁለት ለሁለት በካቴና በማሰር ለረዥም ጊዜ በማቆየትና በባዶ እግራቸው ሽንት ቤት እንዲጠቀሙ በማስደረግ፣ እጃቸውን ሳይታጠቡ ምግብ እንዲመገቡ እና ህክምና በመከልከል እንዲሁም ከቤተሰብ ጋር እንዳይገናኙ አድርገዋል ይላል ክሱ።
በተጨማሪም ምርመራ ጨርሰው ወደ ሌላ ክፍል ሲዘዋወሩ ለ42 ቀናት ከአልጋ ጋር ለ24 ሰዓት በካቴና በማሰር፣ 37 የሚሆኑ ተበዳዮች ፍርድ ቤት ረበሻችሁ በማለት ከ3 እስከ 6 ወር እጃቸውን በካቴና አስሮ ጨለማ ቤት ውስጥ በማሰር፣ ግለሰቦች የለበሱትን ልብስ በማስወለቅ በቲሸርትና በቁምጣ በማስለበስ እና በፌሮ ብረት እንዲደበደቡ በማድረግ ኢ- ሰብአዊ ድርጊት እንዲፈጸምባቸውም አድርገዋል ተብሏል።
እናም  በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም ወንጀል መከሰሳቸው ነው የተነገረው።
የተከሳሽ ጠበቆች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር የተከራከሩ ቢሆንም የተከሰሱበት ወንጀል የዋስትና መብት የሚያስከለክል በመሆኑ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
ተከሳሾችም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት ዐቃቤ ህግ የመሰረተባቸው ክስ በችሎቱ ተነቦ ለቀረበባቸው ክስ መልስ ይዘው ለመቅረብ ለየካቲት 27/ 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መያዙን ከፌደራል ከጠቅላይ አቃቤ ህግ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Tuesday, February 19, 2019

ሕወሃት 7 ሺ የልዩ ሃይል አባላቱን በራያ ኮረም አሰፈረ


ሕወሃት 7 ሺ የልዩ ሃይል አባላቱን በራያ ኮረም አካባቢ ማስፈሩ ተነገረ።
ይህንኑ ተከትሎም የራያ ማንነት አስመላሽ አብይ ኮሚቴ እልቂት ከመፈጠሩ በፊት  የፌደራል መንግስቱ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቅርቧል ።
ፋይል
ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ ከ37 ሺ በላይ የሚሆኑ የትግራይ ልዩ ሃይል በአካባቢው መስፈሩን ኮሚቴው አስታወቋል።
ይህ በእንዲህም ሕወሐት ሚሊሻዎቹን እያሰፈረ የሚገኘው ከክልል ሶስት ጋር ጦርነት ለማካሄድ እንደሆነ ከስልጠናው ጠፍተው የወጡ ሚሊሻዎች ለኢሳት ገልጸዋል።
የራያ ማንነት አስመላሽ አብይ ኮሚቴ ሕወሃት በራያና በአካባቢው ያለውን ችግር በተመለከተ ለፌደራል መንግስቱ አብተደጋጋሚ ልናሳውቅ ሞክረናል።
ነገር ግን ጉዳዩ ምንም ምላሽ ሳያገኝ አሁን የከፋ አደጋን ደቅኗል ይላሉ የራያ የማንነት አስመላሽ አብይ ኮሚቴ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ደጀኔ አሰፋ።
እንደ አቶ ደጀኔ አባባል ከሆነ የህወሃት ዝግጅት ሶስት ወር አልፎታል።በሳምንታት እንኳን በርካታ ሃይልን ሲያሰማራ አይተናል።
አሁን ይሄን መረጃ ለእናንተ እየሰጠሁ ባለሁበት ሰአት ህወሃት ሰራዊቱን ወደ ኮረም እያስገባ ነው ብለዋል።
አሁን በአካባቢው የተደቀነውን አደጋ የአማራም ሆነ የትግራይ ክልላዊ መንግስቶች የሚያስቆሙት አይደለም።
ስለዚህ የፌደራል መንግስቱ አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋል ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም የህወሃት ሰራዊት ስልጠና ዋነኛ አላማ ከክልል ሶስት ጋ ጦርነት ለመግጠም ነው ሲሉ የተናገሩት በስልጠናው ሲሳተፉ የነበሩና በኋላም ጠፍተው ከተመለሱት ሚሊሻዎች አንዱ ናቸው ለኢሳት መረጃውን የሰጡት።
እሳቸው እንደሚሉት ስልጠናውን ረግጠው እንዲወጡ ያደረጋቸው የራያ ማንነት የሚባል ጉዳይ ማንሳት አትችሉም የሚል ርዕስ ሲመጣ ነው።
አሁንም ህወሃት ወጣቱን መመልመል መቀጠሉን ይናገራሉ።አብዛኛው ሰልጣኝ ግን በግዴታ የሚሳተፍ መሆኑን ሳይናገሩ አላለፉም።
ሁለቱም ወገኖች በማያውቁት መንገድ እንዲያልቁ እየተደረገ ነው የሚመለከተው አካል ደግሞ ለዚህ አደጋ አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጥ ይገባል ብለዋል።

አስር የቀድሞ መርማሪዎች አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀረበባቸው።



ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስሩ የቀድሞ መርማሪዎች በአጠቃላይ 78 ክሶች እንደተመሰረተባቸው አስታውቋል።

ከክሶቹ መካከል እስረኞችን እጃቸውን በካቴና በማሰር፣ በጣት እንዲቆሙ በማድረግ፣ በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍና በግንባር ግድግዳ በማስገፋት እና በኤሌክትሪክ በማስነዘር ይርገኝበታል።
በብልታቸው ላይ 2 እስከ 4 ሊትር ሃይላንድ ውኃ በማንጠልጠል ከ2 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት እንዲቆዩ በማስደረግ፣ ፣ ብልታቸውን በፒንሳ በመሳብ የጭንቀት ህመም እና ተያያዥ ድብርት እንዲደርስባቸው አድርገዋል የሚሉትም ከኽሶች መካከል ናቸው።
አስሩ ተከሳሽ መርማሪዎች  «በቀዝቃዛና ጨለማ እስር ቤት ውስጥ በማሰር፣ በእግራቸው መሀል እንጨት አስገብቶ በመገልበጥ የውስጥ እግራቸውን በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍ፣ በምርመራ ክፍሉ በተዘጋጀ ሚስማር ላይ በማንጠልጠል ለረዥም ሰዓት እንዲቆዩ በማድረግ ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ፈጽመዋል
ከዚህ በተጨማሪም  አድካሚ እና ከባድ ስፖርት በማሰራት፤ አፍንጫ ውስጥ እስክሪብቶ በመክተት፣ መቀመጫቸውን እና ጀርባቸውን ውኃ እየደፉ በኤሌክትሪክ ሽቦ በመግረፍ፣ ጺማቸውን በመንጨት ፣ብልታቸውን በቀጭን ሲባጎ በማሰር በግል ተበዳዮች ላይ ሞራላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት አስከትለዋል» ብሏል የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ክስ።
አስሩ ተከሳሾች ኮማንደር ዓለማየሁ ኃይሉ፣ ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፋይኔ ወልደ ሚካኤል፣ ዋና ሳጅን ኪዳኔ አሰፋ ሸማ፤ ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን፣ ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ በዳዳ፣ ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሐሰን መኮንን፣ ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን፣ ረዳት ኢንስፔክተር መንግሥቱ ታደሰ አየለ፣ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይሉ ሁንዴ እና ኢንስፔክተር ስንታየሁ ፈጠነ ለገሰ ናቸው።
ተከሳሾች በፌድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 12ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ክስ መቀበላቸውን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በመጪው የካቲት 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ክሱ በችሎት የሚነበብ ሲሆን በተከሳሾች የዋስትና መብት ላይ ክርክር እንደሚደረግ ዘገባዎች አመልክተዋል።

የሲዳማ ዞን ክልል የመሆን ጉዳይን የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ


የሲዳማ ዞን ክልል የመሆን ጥያቄን በህገ መንግስቱ መሰረት ተግባራዊ እንዲሆን የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ ከተማ ተካሄደ።
በሲዳማ ዞን በሚገኙ 36 ወረዳዎችና ከተማ አስተዳድሮች የተውጣጡ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ ሕገምንግስቱ ይከበር የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።

የደቡብ ክልል ምክር ቤት በጥቅምት ወር ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የሲዳማ ዞን ክልል የመሆን ጥያቄ ህገ መንግስታዊ ሂደቱን ተከትሎ እንዲፈጸም ባለፈው ጥቅምት ወር ባካሄደው ጉባኤ መወሰኑ ይታወሳል።
ይሕም ሆኖ ግን ወሳኔውን ተከትሎ ሕዝበ ውሳኔ መደረግ ቢኖርበትም ሂደቱ ለምን ዘገየ በሚል የሲዳማ ዞን ክልል የመሆን ጥያቄ በህገ መንግስቱ መሰረት ተግባራዊ ይሁን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ ከተማ ተካሄዷል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቃሬ ጫውቻ፣ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ስኳሬ ሹዳ እና የወጣቶች ተወካይ ንግግር አድርገዋል።
የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቃሬ ጫውቻ፥ የሲዳማ ህዝብ በክልል ተዋቅሮ ራስን የማስተዳደር ጥያቄ ማቅረብ ከጀመረ ረጅም ዓመታትን ማስቆጠሩን ገልጸዋል።
በመሆኑም የሲዳማ ህዝብ የክልልነት ጥያቄ በህገመንግስቱ መሰረት ምላሽ መሰጠት እንዳለበትም አቶ ቃሬ ጫውቻ ገልፀዋል።
የሲዳማ ህዝብ ክልል ለመሆን እያቀረበ ያለው ጥያቄው በህገ መንገስቱ መሰረት በአፋጣኝ መልስ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነውም ብለዋል።
የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች “ህገ መንግስታዊ መብታችን ይከበር! የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ መልስ ይሰጠው! የሪፈረንደም ቀን ይወሰን !” የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ይዘው ወጥተዋል።
ጥዋት ላይ መነሻውን ከሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገው ሰላማዊ ሰልፉ መዳረሻውን ሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲዮም ላይ በማድረግ ተካሂዷል።
በህገ መንግስት መሰረት ክልል የመሆን ጥያቄ የሚያቀርበው ብሄር፣ ብሄረሰብ ወይም ህዝብ በወከለው ምክር ቤት በሁለት ሶስተኛ ድምፅ ተቀባይነት ማግኘት ይኖርበታል።በዚሁም መሰረት የሲዳማ ዞን ምክር ቤት ይህንን ክልል የመሆን ጥያቄን ባለፈው ዓመት ተቀብሎ ማፅደቁ የሚታወስ ነው።
ጥያቄው ለክልሉ ምክር ቤት ባለፈው ጥቅምት ወር ቀርቦ ወሳኔ ያገኘ ቢሆንም  ህዝበ ውሳኔ በጠየቂው ዞን የሚካሄድበትን ጊዜ እና ሁኔታን ገና አለማሳወቁ ተዘግቧል።በደቡብ ክልል ወላይታ፥ ከምባታና ጠምባሮ፥ጉራጌ እንዲሁም ከፍቾ ተመሳሳይ ክልል የመሆን ጥያቀ ማቅረባቸው ይታወሳል ።

Saturday, February 16, 2019

አምስት ነጥቦች ስለቀጣዩ የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ

የሰው ስብስብ


ኢትዮጵያ አራተኛውን አጠቃላይ የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ ከመጋቢት 29 ቀን 2011 ዓ.ም አንስቶ ልታካሂድ ሽር ጉድ ላይ ናት። የሕገ መንግሥቱ 103ኛ አንቀፅ ቆጠራው በየአስር ዓመቱ መከናወን እንዳለበት ይደነግጋል። ይሁንና በ1999 ዓ.ም እንደተካሄደው ሦስተኛው ቆጠራ ሁሉ ይሄኛውም አስቀድሞ ከተተለመለት ጊዜ ከአንድ ዓመት በላይ ተራዝሟል።
1. ሕዝብ እና ቤት ቆጠራው ለድብልቅ ማንነቶች እውቅና ይሰጣል?
ሦስተኛው የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ ውጤት ይፋ በሆነበት ወቅት ከተለያዩ አካላት ነቀፌታዎችን ማስተናገዱ ይታወሳል። በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ እና የአማራ ክልል ሕዝቦች ቁጥሮች ጋር በተያያዘ የቆጥራውን ውጤት የመጠምዘዝ ሥራ ተከውኗል ሲሉ የሚያጣጥሉት አሉ።
አራተኛው ቆጠራ የሚከናወነው ከፍ ባለ ጉጉት ከሚጠበቀው ከቀጣዩ ምርጫ አንድ ዓመት በፊት እንዲሁም በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ራስን የማስተዳደር ጥያቄዎች በተበራከቱበት ወቅት ነው። ቆጣሪዎች የሚመለመሉት ደግሞ በየአካባቢው ባለስልጣናት ነው።

የሕዝብ ቆጠራ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ እና የብሔራዊ ስታትስቲክስ ኤጄንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ቢራቱ ይገዙ ቆጠራው ፖለቲካዊ ግብ ባይኖረውም፤ ለፖለቲካ ውሳኔዎች እና ፍላጎቶች ግብዓት መሆኑ ስለማይቀር የሚሰበሰበውን መረጃ ለራስ ፍላጎት እንደሚመች አድርጎ የመነካካት ዝንባሌ አንዱ ስጋታቸው መሆኑን ለቢቢሲ ገልፀዋል።
ይህን ለመቆጣጠር በዚህ ቆጠራ ላይ ተግባራዊ የሚደረጉ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሠራሮች አንድ መላ እንደሚሆኑ ይናገራሉ። ለቆጣሪዎቻቸው ይህን የሚመለከት ስልጠና እንደሚሰጡ፤ ተጠያቂነት እንደሚኖርባቸውም አስረግጠው እንደሚያሳውቋቸውም አቶ ቢራቱ አክለው ያስረዳሉ።
ከሚጠበቀው በተለየ የተጋነነ ለውጥ ካለ "በወረዳና በቀበሌ ያሉ የመስክ ታዛቢዎችን ለምን እንዲህ ያለ ልዩነት እንደመጣ ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ እንጠይቃለን፤ በጣም የተለየ ከሆነ ደግሞ ገለልተኛ ታዛቢ እንዲላክ ይደረጋል" ብለዋል።
በምርጫ መጠይቅ ከሚሞሉ መረጃዎች አንደኛው የተቆጣሪዎቹ ብሔር ሲሆን፤ ድብልቅ የብሔር ማንነቶች ያሏቸው ተቆጣሪዎች አንደኛውን የመምረጥ ግዴታ እንደሌለባቸው የሚያስረዱት አቶ ቢራቱ "ብሔርን፣ ኃይማኖትን በተመለከተ መልስ ሰጭው የሰጠው ብቻ ነው የሚሞላው" ይላሉ። መረጃውን የሚሞላው ሰው በዚህ ጉዳይ ላይ የራሱን ብያኔ የመስጠት ስልጣን የለውም።
ድብልቅ የብሔር ማንነት ያላቸውም ሆነ፤ የብሔር ማንነታቸውን መግለፅ የማይፈልጉ ሰዎች ይህንኑ ለቆጣሪያቸው ቢናገሩ፤ ቆጣሪያቸው የሚሞላው ወይንም የምትሞላው ኮድ አለ ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።
2. ለሕዝብ እና ቤት ቆጥራው ምን ያህል ዝግጅት ተደርጓል?
ኢትዮጵያ የሕዝብ እና ቤት ቆጠራውን ለመጀመሪያ ጊዜ በዲጂታል መሣሪያዎች የምታከናውን ሲሆን ለዚሁ ተግባር ያገለግላሉ የተባሉ 180 ሺህ ታብሌቶች ከአንድ ዓመት በፊት ተገዝተዋል።
ታብሌቶቹ ከኃይል መቆራረጥ ጋር በተያያዘ ችግር እንዳይገጥማቸው ታስቦም በመጠባበቂያነት የሚያገለግሉ 126 ሺህ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከማቻዎች (ፓወር ባንኮች) እንዲሁም 30 ሺህ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የባትሪ አቅም መሙያዎች (ቻርጀሮች) ግዥ ተፈፅሟል።
አቶ ቢራቱ ይገዙ ቆጠራውን በዲጂታል መሣርያዎች ማድረጉ "ለጥራት ቁጥጥርም፣ ለክትትልም፣ በጊዜ ለማድረስም፣ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍም" የተሻለ አማራጭ እንደሚሆን ታምኖበት የተወሰነ ነው ይላሉ።

ሌላኛው የተከናወነው ሥራ የቆጠራ ክልል ማዘጋጀት ሲሆን እርሱም ሁለት ዓመታትን ወስዷል እንደ አቶ ቢራቱ ገለፃ። በዚህም መሠረት በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ሁሉም ቀበሌዎች በቆጠራ ክልልነት ተሸንሽነዋል።
በገጠር ቤቶች ዘርዘር ብለው እንደመገኘታቸው ከአንድ መቶ እስከ አንድ መቶ ሃምሳ ቤተሰቦች በአንድ የቆጠራ ክልል የተጠቀለሉ ሲሆን በከተማ ደግሞ የቤቶቹ ቁጥር ከአንድ መቶ ሃምሳ እስከ ሁለት መቶ ከፍ ይላል። የቆጠራ ክልሎቹ መገኛ በዓለም አቀፍ የአቀማመጥ ሥርዓት (ጂፒኤስ) ነጥባቸው ተወስዷል።
እያንዳንዱ ቆጣሪ ከተሰጠው የቆጠራ ክልል ውጭ ቢንቀሳቀስ ዲጂታል መሣርያው አይሰራለትም ሲሉ አቶ ቢራቱ ገልፀዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ አንደኛው ስጋት የሳይበር ጥቃት ሊፈፀም ይችላል የሚል እንደሆነ የተናገሩት አቶ ቢራቱ ይህን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራን ነው ብለዋል።
3. ውጤቱ መቼ ይፋ ይሆናል?
በአገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች አልፎ አልፎ የሚስተዋለው ያለመረጋጋት የቆጥራውን ሒደት ሊያወከው ይችል እንደሆነ በቢቢሲ የተጠየቁት አቶ ቢራቱ፤ ስጋቱ ቢኖርም ሥራችንን ሊያውከው ይችላል ብለን አንጠብቅም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
በአስረጂነት የሚያነሱትም የቆጠራ ክልል ሲዘጋጅ በነበረበት በ2009 ዓ.ም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች ተቃውሞ እና ያለመረጋጋት የነበረ ቢሆንም፤ ሥራቸው ላይ እንቅፋት የተፈጠረባቸው አጋጣሚዎች ያለመኖራቸውን ነው።

አቶ ቢራቱ ቆጠራውን ለማካሄድ ከሰባት እስከ አስር ቀናት እንደሚወስድ ይገልፃሉ።
ቆጠራው ከተከናወነ በኋላ የተሰበሰበውን መረጃ የመተንተን ሥራ የሚቀጥል ሲሆን፤ ውጤቱን ሕጉ የሚያስገድዳቸውን ሒደቶች አልፎ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀ በኋላ ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ ስድስት ወር ገደማ ያስፈልጋል ሲሉም አክለዋል።
4. ማን ምን ይጠየቃል?
ለመጀመሪያ ጊዜ የሕዝብ እና ቤት ቆጠራው መጠይቆች በአምስት ቋንቋዎች ተዘጋጅተዋል። ከአማርኛ በተጨማሪም ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ ትግርኛ እና አፋርኛ መጠይቁ የተሰናዳባቸው ቋንቋዎች ናቸው።
መሠረታዊ መረጃን ከሚያመላክቱ ዕድሜ፣ ፆታ፣ ኃይማኖት፣ ብሔር፣ የሥራ ስምሪትና የመሳሰሉ ጥያቄዎች በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ የአካል ጉዳት መረጃ እና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ደረጃ ማለትም የተንቀሳቃሽ ስልክ እና ኢንተርኔት ተጠቃሚነት መረጃዎችም ይጠየቃሉ።
በኢትዮጵያ የሥነ ምድር ክልል ውስጥ የሚገኙ ዜጎችም ሆኑ ስደተኞች የሚቆጠሩ ሲሆን የሕግ ታራሚዎችን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችን እና የጎዳና ተዳዳሪዎችን የሚመለከቱ ልዩ የመጠይቅ ዓይነቶችም አሉ ሲሉ የቆጠራ ኮሚሽኑ ዋና ጸሐፊ ይናገራሉ።

ኢትዮጵያ ከዓለም ቀዳሚ ያደረጓትን ቁጥራቸው በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃዮችን አስመልክተውም፤ መንግሥት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በተቻለ መጠን ወደቀያቸው "ለቆጠራውም፣ ለሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ሲባል" እንዲመለሱ ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል። ይህ ሁሉ ተደርጎም ግን ፍልሰትን የተመለከተ "የአቆጣጠር ዘዴ አለ" ይላሉ።
ተፈናቃዮቹ የቆጠራው ውጤት ይፋ ከመሆኑ በፊት ወደቀያቸው ለመመለሳቸው ማረጋገጫው ሲገኝም "መረጃውን ተከታትለን የምናስተካለው ነው የሚሆነው" ብለዋል ዳይሬክተሩ።
ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቅቆ ወደውጭ አገር የሄደ የቤተሰብ አባል አለ ወይ? የሚለው ሌላኛው በአራተኛው የሕዝብ ቆጠራ ውስጥ የተካተተ አዲስ ጥያቄ ነው።
5. ቆጥራውን የሚያካሂዱት እነማን ናቸው?
ቆጠራውን በበላይነት የመምራቱ እና የማስተባበሩ ስልጣን የሕዝብ ቆጥራ ኮሚሽን ነው። በሕገ መንግሥቱ መሠረት ኮሚሽኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ እጩ አቅራቢነት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚፀድቁ አባላት ይኖሩታል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኮሚሽኑ የበላይ ሲሆኑ፤ ይመለከታቸዋል የሚባሉ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች እንዲሁም የክልል እና የከተማ መስተዳደር ኃላፊዎችን በአባልነት ያካትታል።
አጠቃላይ ዕቅዶችን መገምገም፣ አቅጣጫዎችን መስጠት፣ በከፍተኛ ደረጃ መፍትሄ የሚፈልጉ ችግሮች በሚያጋጥሙበት ወቅት መፍትሄ መስጠት ከኮሚሽኑ ኃላፊነቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ሆኖም የቆጠራውን ቴክኒካዊ ሥራዎች የሚያከናውነው ቆጠራ በሚኖርበት ወቅት ተጠሪነቱ ለኮሚሽኑ የሚሆነው ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጄንሲ ነው።

ኤጄንሲው የቆጠራ ካርታ የማዘጋጀት ኃላፊነት አለበት። የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ያቀርባል። ለተመለመሉ ቆጣሪዎች ስልጠና ይሰጣል። የቆጠራ መረጃውን ይሰበስባል። መረጃውን ይተነትናል። ከዚያም ለኮሚሽኑ ያቀርባል። ኮሚሽኑ መረጃውን ካፀደቀው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቦ ያስፀድቃል።
ኤጄንሲው በተጨማሪም የኮሚሽኑ ሴክሬታሪያት ፅህፈት ቤት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
ለቆጠራ የሚሰማሩ ሰራተኞችን መልምለው የሚያቀርቡት የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። ተመልማይ ቆጣሪዎቹ የመንግሥት ሰራተኞች ሲሆኑ በአብዛኛው መምህራን፣ የግብርና ልማት ሰራተኞችና የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ይሆናሉ።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር እንዲሆኑ አቶ ዳንኤል በቀለ መንግሥት ያቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀበሉ


በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ  አቶ ዳንኤል በቀለ  የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር እንዲሆኑ መንግሥት ያቀረበላቸውን ጥያቄ መቀበላቸው ተሰማ።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች  እንዳረጋገጡት አሜሪካን የሚገኙት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ዳንኤል፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት እንዲመሩ መንግሥት ላቀረበላቸው ጥያቄ ፈቃደኛ ሆነዋል።

ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ለሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ኮሚሽነሮች የሚሾሙት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚያቋቁመው ኮሚቴ ዕጮዎችን ተቀብሎና መዝኖ ከመረጠ በኋላ ለምክር ቤቱ በማቅረብ ሲፀድቅ ነው።
በዚህም መሠረት ዕጩዎችን የሚያቀርበው ኮሚቴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ  አቶ ዳንኤል በቀለን  በዕጩ ኮሚሽነርነት እንደመዘገባቸው ገልጸዋል።
አቶ ዳንኤል በቀለ በ1997 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ ማግሥት መንግሥት ባቀረበባቸው ክስ ከዓመት በላይ ታስረው እንደነበር ይታወሳል።
በወቅቱ አክሽን ኤድ ተብሎ የሚታወቀው ዓለም አቀፍ የሲቪክ ማኅበር ባልደረባ ነበሩ።
ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ከአገር በመውጣትና መቀመጫቸውንም በኬንያ በማድረግ፣ አምነስቲ ለተባለው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የምሥራቅ አፍሪካ ተወካይ በመሆን የኢትዮጵያንም የሰብዓዊ መብት አያያዝ ይከታተሉ ነበር።
በመቀጠልም ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ላደረገው ታዋቂው ‹‹ሂውማን ራይትስ ዋች›› የተባለ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር በመሆን፣ ለረዥም ዓመታት ኒውዮርክ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤቱ ሲያገለግሉ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአንድ ወር እረፍት ከመበተኑ አስቀድሞ ጥር 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፣ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዕጩ ኮሚሽነር አቅራቢ ኮሚቴ አቋቁሟል።
ምክር ቤቱ 11 አባላት የያዘ ኮሚቴ ማቋቋሙ ነው የተነገረው።
ኮሚቴውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ በሰብሳቢነት ይመሩታል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካይ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ጉባዔ ተወካይ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ተወካይ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ተወካይ ለኮሚቴው በአባልነት ከተመረጡት መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።
የተቀሩት ደግሞ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መካከል የተመረጡ መሆናቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

በለገጣፎ የተጀመረው ቤትን የማፍረስ ዘመቻ ህግን መሰረት ያደረገ ነው ተባለ

በለገጣፎ የተጀመረው ቤትን የማፍረስ ዘመቻ  ህግን መሰረት ያደረገ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሚልኬሳ ሚደግሳ ተናገሩ።
በጉዳዩ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የቢሮ ሃላፊው በለገጣፎ እየተወሰደ ያለው እርምጃ የሊዝ አዋጅ 721ን መሰረት ያደረገ መሆኑን ቢሮ ሃላፊው ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሚልኬሳ ሚደግሳ እንደገለጹት እርምጃው ከተሞች ስርዓት ባለውና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲያድጉ ለማድረግ ያለመ ነው።
በለገጣፎ  በወንዞች ዳርቻና አረንጓዴ ስፍራዎች ጉዳዩ ሕገ ወጥ መሆኑ እየታወቀ ግንባታዎች ተከናውነዋል ብለዋል።
ከዚህ ባለፈም ግንባታዎቹ ለመኖሪያ ምቹ ባልሆኑ ስፍራዎች የሚካሄዱ በመሆናቸው መንግስት ተጠያቂ የሚሆንበትን እድል ይፈጥራል ሲሉም ነው የገለጹት።
ዶክተር ሚሊኪያስ በመግለጫቸው 2004 ዓመተ ምህረት ላይ የወጣውን የሊዝ ህግ ለማስፈፀም 2005 ዓም  ላይ መመሪያ መውጣቱን አስታውሰዋል።
መመሪያውም ከ2005 ዓመተ ምህረት በፊት የተገነቡ ቤቶች ከሳይት ፕላኑ ጋር የሚጣጣሙ ከሆነ ህጋዊ እንዲሆኑ፤ ከፕላኑ ጋር የማይጣጣሙ ከሆነ ደግሞ እንደሚፈርሱ ያስቀምጣል ነው ያሉት።
እናም አሁን እየተወሰደ ያለው እርምጃም ከዚህ አንጻር መሆኑን ነው ያስረዱት።
በጥናቱም በአንዳንድ አካባቢዎች መንግስት ለአርሶ አደሩ ካሳ ከፍሎ ለልማት ባዘጋጃቸው ቦታዎች ላይ ህገ ወጥ ግንባታ መካሄዱንም ጠቅሰዋል።
በቀበሌ ቤቶች ሳይቀር ግለሰቦች የፈለጉትን ዓይነት ግንባታ አከናውነው መገኘታቸውም በጥናቱ ተደርሷል።
ግንባታው ህገ ወጥ መሆኑ እየታወቀ ግንባታ መካሄዱም ትልቁ ችግር መሆኑን ጠቅሰው፥ መንግስትም ህግ የማስከበር ስራ እያከናወነ ነው ብለዋል።
በቅርቡ በአዳማ፣ በሻሸመኔ እና መቱ ከተሞች በሺዎች የሚቆጠሩ ህገወጥ ግንባታዎች መፍረሳቸውን በማንሳትም፥ እርምጃው በፍንፊኔ ዙሪያ ብቻ እየተወሰደ አለመሆኑን ገልፀዋል።
ዶክተር ሚልኬሳ እርምጃ በተወሰደባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎቹ ቤታቸውን እንዲያፈርሱ ከአንድ አመት ጀምሮ ማስጠንቀቂያ ሲሰጣቸው እንደቆየም አስታውሰዋል።

ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በፋይናንስ ዘርፍ እንዲሳተፉየሚፈቅድ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ


 በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ እንዳይሳተፉ በሕግ ተከልክለው የቆዩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን በዘርፉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚፈቅድ ረቂቅ ሕግ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ አስታወቁ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶር ይናገር ደሴ በሰጡት መግለጫ፣ በፋይናንስ ዘርፉ ውስጥ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዳይሳተፉ የሚያግደውን ሕግ በማሻሻል ተሳታፊ የሚሆኑበት መንገድ መመቻቸቱን አስታወቀዋል፡፡

ይሕ በእንዲህ እንዳለም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተለይ ለግብርና የሰጠው ከ6 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ሊመለስ የማይችልበት ደረጃ መድረሱን  የባንኩ ገዥ ይፋ አድርገዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት የፋይናንስ ዘርፉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ላላቸው ብቻ የተፈቀደ ነው።
በዚሁህግ መሰረትም  የውጭ ዜግነት ያላቸው ዳያስፖራዎች በዘርፉ ተሳታፊ እንዳይሆኑ ተገድበው ቆይተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶር ይናገር ደሴ በሰጡት መግለጫ በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ እንዳይሳተፉ በሕግ ተከልክለው የቆዩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን በዘርፉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚፈቅድ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጅቷል።
አዲሱ ረቂቅ ዝርዝር ጉዳዩ ባይገለጽም፣ ማሻሻያው ዳያስፖራው በዘርፉ እንዲሰማራ ያስችላል ነው የተባለው፡፡
‹‹በእኛ በኩል በተለይ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በፋይናንስ ዘርፉ መሳተፍ የሚቻልበትን ዕድል እንዲኖር ጥናቶችን አጥንተናል፤›› ሲሉ ዶር ይናገር አስታወቀዋል።
እናም ከሚመለከታቸው ጋር ውይይት ተደርጎበት ከፀደቀ አንድ ትልቅ የለውጥ አካል ይሆናል ብለዋል።
ረቂቅ ሕጉ ከጸደቀ ዲያስፖራዎች ባብንክና ኢንሹራንስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ያስችላቸዋል።
ይሕ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተለይ ለግብርና የሰጠው ከ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ሊመለስ የማይችልበት ደረጃ መድረሱን  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶር ይናገር ደሴ አስታውቀዋል፡፡
ባንኩ ለግብርና ከሰጠው ብድር ውስጥ 6.3 ቢሊዮን ብር የሚሆነው ሊመለስ የማይችል መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ ይህም የሆነው በተደራጀና በተቀነባበረ መንገድ ብድሩ በመሰጠቱ ነው ብለዋል፡፡
ይሕ በመሆኑም  የባንኩን የተበላሸ የብድር መጠን ከፍ ያደርገዋል የሚል ሥጋት አሳድሯል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባለፈው ዓመት የተበላሸ የብድር መጠኑ 40 በመቶ መድረሱ ይታወሳል፡፡ ‹
‹የልማት ባንክ ከፍተኛ ችግር አለበት፡፡ ያልተመለሰ ብድር ምጣኔው በከፍተኛ መጠን ጨምሯል፡፡ በተለይ ደግሞ ለእርሻ ያበደረው ብድርን መመለስ አልተቻለም፤›› ብለዋል፡፡
ሪፖርተር ጋዜጣ ዶር ይናገር ደሴን ጠቅሶ እንደዘገበው   በግብርና ስራ ስም ክርልማት ባንክ የተበደሩ ሰዎች ወደ ሕግ የሚቀርቡበት ሁኔታ እንዲጀመር ብሔራዊ ባንክ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

Thursday, February 14, 2019

የኢሳት ባልደረቦች ወደ ኢትዮጵያ ተሸኙ


 የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሊቪዥንና ሬዲዮ ኢሳት ባልደረቦች ከአምስተርዳም፣ለንደንና ዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኢትዮጵያ ዛሬ አሸኛኘት ተደረገላቸው።

ከዋሽንግተን ዲሲ የተነሱት የኢሳት ባልደረቦች ከዳላስ አይሮፕላን ማረፊያ ሲነሱ በኢትዮጵያውያን አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል።
አሸኛኘቱን በስፍራው ተገኝቶ ሲዘግብ የነበረውም ምናላቸው ስማቸው ስለ አሸኛኘቱ መረጃውን ሊያደርሰን እዚህ ስቱዲዮ ይገኛል።

Tuesday, February 12, 2019

"አሁንም የታገቱ ሰዎች አሉ" ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ፅጌ

ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ፅጌ


በተደጋጋሚ ግጭቶች ከተከሰቱና በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ከደረሰ በኋላ የክልሉና የፌደራል መንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው እንዲሰማሩ ተደርገዋል።
በተጨማሪም በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ውስጥ ባሉ አካባቢዎች ከተፈቀደላቸው አካላት ውጪ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ክልከላ ተጥሏል።
በእነዚህ አካባቢዎች ስላለው የፀጥታ ሁኔታና ተያያዥ ጉዳዮች የአማራ ክልል የሠላምና የህዝብ ደህንነት ግንባታ ቢሮ ሃላፊ ከሆኑት ከብ/ጀኔራል አሳምነዉ ፅጌ ጋር ቆይታ አድርገናል።
ጎንደር፡ የአስቸኳይ ጊዜ ወይስ የመሣሪያ እገዳ?
ቢቢሲ በአሁኑ ሰዓት አጠቃላይ በክልሉ ያለዉ የጥታ ሁኔታ ምን ይመስላል?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ቀደም ሲል ከነበረዉ አሁን አንጻራዊ ሰላማዊ ነው። ይህም በቀጠናዉ ሰፊ የሆነ የሠራዊትና የፀጥታ አካላት ስምሪት ስለነበረ ነው። ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ነገሮች ተስተካክለዋል ማለት አይደለም።
ቢቢሲ፦ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት ያልተቻለበት ምክንያት ምንድን ነው?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ የተነሱ ጥያቄዎች የአገራችን ሕገ መንግሥት በሚፈቅደዉ መሰረት በየደረጃዉ ያሉ አካላት የህዝቡን ስሜትና ፍላጎት መነሻ አድርጎ ተወሰኗል። በህግ በኩል ይሄ ነው የሚቀረው ተብሎ የሚታሰብ ነገር አይደለም።
ከዚህ ዉጭ ግን ይህ ሁኔታ በዚህ መንገድ እንዳይቀጥል የተለየ ፍላጎት ያላቸዉ ወገኖች አሉ። ስለዚህ በዚያ አካባቢ ባለዉ እንቅስቃሴ ላይ የተለያዩ ኃይሎች ፍላጎት ማሳደራቸዉና ግጭት እንዲቀጥል ፍላጎት ብቻ ሳይሆን አጥብቀው እየሰሩበት በመሆኑ እንቅስቃሴው በፈለግነው መንገድና ህዝቡ ይጠቅመኛል ብሎ ባሰበዉ መንገድ ሊቋጭ አልቻለም። አሁን ግን በዚያ መንገድ ለማቀራረብና ችግሩን ለማስተካከል ጥረት እየተደረገ ነዉ።
ቢቢሲችግሩን ከመቆጣጠር አኳያ አሁን ታዲያ ምን ሰራችሁ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ የቆየ ችግር እንደሆነ ይታወቃል። ህዝባዊ ባይሆንም የሆነ መነሻ አለዉ። ስለዚህ ይህን መነሻ አድርገን እየሰራን ነው። አንደኛ በሁለቱ ህዝቦች መካከል እርቀ ሰላም እንዲወርድ፤ ችግሩ የሁለቱ ህዝቦች እንዳልሆነ በሚያሳይ መንገድ ብቻ ሳይሆን መነሻዉን በግልጽ ለህብረተሰቡ በማሳየት ህብረተሰቡ እንዲሳተፍበት እየተደረገ ነው።
ሁለተኛ ከቀውሱ ማናችንም ተጠቃሚ አይደለንም። እነዚህ ህዝቦች አሁን ብቻ ሳይሆን ወደፊት አብረው የሚቀጥሉ ናቸዉ። በብዙ መንገድ አንድ መሆናቸዉን የሚያሳዩ ቁርኝቶች አሉ።
"የቅማንትን ሕዝብ እንወክላለን የሚሉ ፅንፈኞች ከሌሎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ ነው" ጄኔራል አሳምነው
ስለዚህ አካባቢው ላይ የተጠነሰሰ ችግር ሳይሆን የተላከ ፕሮጀክት ስለሆነ ይህን ፕሮጀክት ለማምከን ደግሞ ህዝቡ እንዲገነዘብ እየተደረገ ነው። ይህ ራሱ አንዱ መነሻ ነው። ምክንያቱም ያው ችግሩን ካወቅኸዉ ለመፍትሔውም ተቃረብክ ማለት ነዉ።
ከዚህ ውጪ ለችግሩ መነሻ ናቸዉ በተባሉ ኃይሎችና ለጸጥታ መሰናክል ናቸው በተባሉ ግለሰቦች ላይ ርምጃ ለመውሰድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። ተጠናክሮም ይቀጥላል። ስለዚህ ህብረተሰቡ ይህንንም ሽምግልናውንም ከራሱ ልምድና ተሞክሮ ያገኘዉን ነገር አጠናክሮና አደራጅቶ ሰላማዊ ሁኔታውን ያመጣዋል ብለን ተስፋ እናደረጋለን። በዚያ መንገድ ደግሞ እየሄድን ነዉ።
ቢቢሲ፦ በምዕራብ ጎንደር ያለው ችግር ወደ ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች ሊዛመት ይችላል የሚል ስጋት አለዎት?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ጎንደር ለአስተዳደራዊ ሁኔታ ተብሎ የተከፈለ ስለሆነ አንድ ቦታ ላይ ያለዉ ስሜት ሌላ ቦታ ይነበባል። አንድ ቦታ ያለው መልካም ነገር ሌላ ቦታ መልካም ነገር ይዞ ይመጣል። ስለዚህ የአንዱ ተጽዕኖ ሌላው ጋ ሊኖር አይችልም ልንል አንችልም። በጋራ አንድ መስመር የሚጠቀሙ ናቸው።
ስለዚህ አንዱ ቦታ በተነሳዉ ግጭት ምክንያት ተንቀሳቅሰው መስራት ካልቻሉ ችግሩ ሌላም ቦታ ተጽዕኖ አሳድሯል ማለት ነው። አሁን ባለው ሁኔታ ግን ተጽዕኖው አይደለምና በሌላው አካባቢ፤ ችግሩ በተከሰተበት ስፍራም እየቀነሰ ስለሆነ ተጽዕኖው የለም ማለት ይቻላል። ህብረተሰቡም ከውድቀቱ እየተማረ ስለመጣ በራሱ ሰላሙን ለማስጠበቅ እየሰራ ነው። ነገር ግን አካባቢውን ማበጣበጥ የሚፈልጉ ኃይሎች አርፈዉ ይቀመጣሉ ብለን አናስብም።
ቢቢሲ፦ እነዚህ ይሎች ግን እነማን ናቸዉ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ እሱን ሌላ ጊዜ እንነጋገረዋለን። ግን ዞሮ ዞሮ ይሄ አካባቢ ድንበር ነው፤ ታውቀዋለህ አይደል? በአብዛኛው ሱዳን ጋር እንዋሰናለን ሌላም ጋር እንዋሰናለን። አንዳንድ አካባቢዎች የይገባኛል ጥያቄ ከታሪክም ከሌላም በለው እዚህ አካባቢ ችግር እንዲከሰት ያደርጋል።አንዳንድ አካባቢ ደግሞ ይሄ ህዝብ በርካታ ጥያቄዎች ኑረውት በተገቢው መንገድ እንዳያቀርብ ደግሞ አንቅፋት ለመፍጠር የሚፈልጉ ኃይሎች አሉ። ይህን በተደጋጋሚ ተነጋግረንበታል ህዝቡ በራሱ መንገድ ይፈታዋል።
ቢቢሲ፦ ሰሞኑን በተለይ ከጎንደር መተማና ከጎንደር ሁመራ በሚወስዱት መንገዶች ላይ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል። ከክልከላዉ በላም ግን እገታዎች እንደተፈጸሙ እየተነገረ ነዉ። እዴት ይህን መከላከል አልተቻለም?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ እነዚህ መንገዶች ዓለም አቀፍ መንገዶች ናቸዉ። እነኝህን መንገዶች በራሳችን ፍላጎት መከላከያ በበላይነት ብቻ ሳይሆን በወሳኝነት እንዲቆጣጠራቸው አድርገናል። ሌላውን ሥራ ደግሞ እኛ እንድንሰራ ተደረጓል። ይህም የተልዕኮ ግልጽነት እንዲኖርና በተልዕኮ ላይ አሻሚነትና አወዛጋቢነት እንዳይከሰት ነው።
ከጄኔራሎቹ ሹመት ጀርባ?
ክልከላዉ የተካሄደውም አጠቃላይ እንቅስቃሴውን ሰላማዊ ለማድረግና የሚፈጠሩ እገታዎችን ለመከላከል ታስቦ ነዉ። ይሁን እንጂ ይህ ችግር አልተቀረፈም። ሰሞኑን ሚኒባስ የያዙ ሹፌሮችና ረዳቶች ታግተዋል። ጭልጋ አካባቢም የተወሰነ ችግር ገጥሞናል። ይሄ የቆየና የሚጠበቅ ነዉ አዲስ ነገር አይደለም። መልሰን ለማስተካከል እየሰራን ነው። እነዚህ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም የምንጠብቃቸው ችግሮች አሉ።
ቢቢሲ፦ የታገቱት ሰዎችስ የት እንደደረሱ ይታቃል?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ይገኙበታን የተባሉበትን ቦታ መለየት ተችሏል። አንዳንዶቹን የመከላከያ ሠራዊት ደረሶ እርምጃ በመውሰድ ወደ ቤተሰቦቻቸዉ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል። አንዳንዶቹን ደግሞ ፍለጋና ክትትል ላይ ናቸው።
ቢቢሲ፦ ካሁን በፊት ወታደራዊ ስልጠና የሚሰጥባቸዉ ቦታዎች መገኘታቸዉን ገልጸዉ ነበር። እነዚህ ቦታዎች አሁንም በእናንተ ቁጥጥር ስር ናቸው?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ይህ የአደባባይ ሚስጢር ነው። አሁን ግን መንግሥት እየተቆጣጠረው ነው። የአካባቢው መልክዐ ምድር አስቸጋሪ ነው። አንዱን ስተቆጣጠረው ሌላ ቦታ ሊከሰት ይችላል። ስለዚህ ይሔ እስካሁን የቀጠለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይህ ደግሞ በእንዲህ አይነት መልክዐ ምድር የሚያጋጥም ነው። ካሁን በፊት የነበሩትን ተቆጣጥረናል። ነገር ግን ሌሎች አካባቢዎች እስካሁን አሉ። በአብዛኛው ከሱዳን ድንበር ጋር ተያይዞ የቆየ ባህልም ስላለ እሱን ተጠቅሞ የመንቀሳቀስ ነገር አለ እንጅ፤ በአብዛኛው የጎንደር አካባቢ ጠንካራ ይዞታ የላቸውም።
ቢቢሲ በክልሉ በተለይ አሁን ችግሩ በሚነሳባቸዉ አካባቢዎች በተለያየ ጊዜ የግልም ሆነ የቡድን መሳሪያ በተደጋጋሚ በግለሰቦች እጅ ይያዛል፤ ወደ ሌላ አካባቢ ሲንቀሳቀስም በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ይነገራል። ለመሆኑ የእነዚህ መሳሪያዎች ምንጭ ከየት እንደሆነ ይታወቃል?
መከላከያ የኢህአዴግ የመጨረሻ ምሽግ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ፦ አናቅም ይህንን ነገር።
ቢቢሲ፦ ስለዚህ ክልሉ ስጥ ከገቡ በኋላ ነ ማለት ነ መረጃ የሚደርሳችሁ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ እውነት ነዉ።
ቢቢሲሕገወጥ የመሳሪያ ዝውወውሩን ከምንጩ ለማድረቅና ምንጩን ከመፈለግ አንጻርስ ምን ሰርታችኋል?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ በእሱ ላይም እየሰራን ነው።
ቢቢሲ፦ በክልሉ በተከሰተ ግጭት ምክያት የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እየተሰራ ያለ ራ አለ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ ከሰላም ማስከበሩ በተጓዳኝነት እየተሰራ ያለዉ ሥራ አንዱ እሱ ነው። ህብረተሰቡ የማሳ ዝግጅቱ ጊዜ ሳያልፍበት ወደ አካባቢዉ እንዲመለስ ይፈለጋል። አሁን የሰፈሩትም በቅርብ ርቀት ነው። ግን ደግሞ የጸጥታ ዋስትና እንዲኖራቸዉ ይፈልጋሉ፤ ይህንን እየሰራን ነዉ። በቅርቡ አብዛኛዉ ይመለሳል።
ቢቢሲበመጨረሻ የሚሉት ነገር ካለ?
ብ/ጀኔራል አሳምነዉ የአንድ አካባቢ ችግርና ቀውስ የሃገርም ችግር የሃገርም ቀውስ ተደርጎ መወሰድ አለበት። የትኛዉም አካባቢ የሚደርስ የዜጎች መፈናቀል ሁላችንንም አንገት ሊያሰደፋን ካልሆነ በስተቀር አንዱ የሚጠቀምበት ሌላዉ የሚጎዳበት ተደርጎ መወሰድ የለበትም።
በተለይ በሰለጠነዉ በዚህ በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን በጎሳና በዘር ላይ የተመሰረተ ፖለቲካና እጅግ ኋላ ቀር በሆነ አካሄድ ብዙዎቻችን እየተጎዳን እንገኛለን፣ አገሪቱም እየተጎዳች ትገኛለች፣ አካባቢያችንም በዚህ ዙሪያ እየታመሰ ይገኛል።
ስለዚህ በዚህ አይነት ምስቅልቅልና የፖለቲካ ኪሳራ መጨረሻ ላይ ሁላችንም ተጎጂዎች እንጅ ተጠቃሚዎች አንሆንም። የተለያዩ የሃገራችን ምሁራን የተሳተፉበት ተቋማት፣ የሀገራችን ታላላቅ ሰዎች፣ የቢዝነስ ሰዎች፣ ሁላችንም ያገባናል የምንል ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ አጽንኦት ሰጥተን እንድንመክርበት በዚህ አጋጣሚ ማሳሰብ እንፈልጋለን።
ይሄ ሁኔታ መቀየሩ አይቀርም፤ ግን ደግሞ ታሪካችንን ሳያበላሽ መቀየሩ ሁላችንንም ይጠቅማል። በዚህ መልኩ ለሚሳተፉም ፈጣሪ ልቦና እንዲሰጣቸዉ፣ ሌሎች ደግሞ በመልካም ሁኔታ ላይ እንዲንቀሳቀሱ፣ ሁላችንም እንድንረዳዳ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን ለማስተላለፍ እወዳለሁ።

Monday, February 11, 2019

የኩላሊት መድከም የገጠማቸው ሰዎች ተስፋ-ንቅለ ተከላ

የኩላሊት መድከም የገጠማቸው ሰዎች ተቸግረው፣ ሕመማቸው በርትቶ፣ ጎዳና ወጥተው ተመልክተናል፤ በየመገናኛ ብዙሃኑ የድረሱልኝ ጥሪያቸውን ሰምተናል። በአደባባዩች ፎቷቸውን ሰቅለው ለህክምና ምፅዋት ሲጠይቁ አድምጠናል።
ሰርተው ይበሉ የነበሩ እጆች ተይዘው፣ ያስተዳድሩት የነበረው ቤተሰብ ተበትኖ የነገን ፀሐይ ለመሞቅ ማሰብ ቅንጦት ሲሆንባቸው ማጣታቸውን ቆርሰው ያካፈሉ፣ በሙያቸው የቻሉትን አስተዋፅኦ ያበረከቱትንም ተመልክተናል።
Warning Signs of Kidney Disease - ኩላሊት ሲጎዳ የሚታዩ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች
ድምጻውያን "እኔ ነኝ ደራሽ" ሲሉም አቀንቅነው ልባችንን ነክተው ኪሳችንን እንድንዳብስ አድርገዋል። ይህ ትናንት የሚመስለው የኩላሊት መድከም ወሬ ዛሬ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል።
"እኛ ብቻ አይደለንም ዘመዶቻችንም ታመዋል"
መሪማ መሐመድ ጦይብ የተሻለ ኑሮን ለመምራት በማሰብ ነበር ወደ አረብ ሀገር ያቀናችው፤ ነገር ግን ብቸኛ ሀብቴ ያለችው ጤናዋ ከዳት። ዘወትር ከብርታት ይልቅ ድካም በጎበኛት ቁጥር ሕክምና ወደ ምታገኝበት ስፍራ ሄደች።
የሰማችው ነገር ግን ጆሮን በድንጋጤ ጭው የሚያደርግ ዜና ነበር። "ሁለቱም ኩላሊቶችሽ ከጥቅም ውጪ ሆነዋል" ተባልኩኝ ትላለች። ስለዚህ ቢያንስ ሞቴን በዘመዶቼ መካከል፣ በሀገሬ አፈር ብላ ብላ ጓዟን ጠቅልላ ወደ ሀገሯተመለሰች።

አቶ አለነ ወልደማሪያም ደግሞ የስኳር ሕመምተኛ ናቸው። የስኳር ሕመምተኛ ሲኮን ካሉ የጎንዮሽ ጉዳቶች መካከል የኩላሊት መድከም አንዱ እንደሆነ ያውቁ ስለነበር ሁሌም ስጋት ሽው ይላቸው ነበር።
አንዳንድ የህመም ምልክቶቻቸው ደግሞ ስጋታቸው እውን እንደሆነ እንዲሰማቸው ያደርጉ ጀመር። ወደህክምና ተቋም ሄደው ሲመረመሩ ስጋታቸው ልክ እንደሆነ አረጋገጡ፤ ኩላሊታቸው ደክሟል።

የስኳር በሽታው እና የኩላሊት ህመሙ ተደራርቦ አልጋ ላይ ጣላቸው። ሌሎች የጎንዮሽ ህመሞች መደራረብ ደግሞ አልጋ ላይ የሚቆዩበትን ጊዜ አረዘመው።
መሪማ ሀገሯ ስትመለስ ዘመድ ወዳጆች ተረባርበው ወደ ግል ሆስፒታል ወሰዷት። የሄደችበት የግል ሆስፒታል ለአንድ ቀን ለመታጠብ፣ ለመድሃኒት፣ ለታክሲና ለአንዳንድ ነገሮች እስከ ሦስት ሺህ ብር ያስወጣን ነበር ትላለች።

"ይህንን ወጪ በየቀኑ ማሰብ ከሕመሙ በላይ የሚሰማ ሕመም ነው። ይህ የሌላቸው የዘመድ እጅ ወደ ማየት ንብረት ወደመሸጥ ይሄዳሉ" ትላለች መሪማ።
አቶ አለነም ቢሆኑ ለእጥበቱ የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ወደ ጎዳና ላለመውጣት ቤተሰቦቻቸው አግዘዋቸዋል። ለተከታታይ ስምንት ወራት የኩላሊት እጥበት ሲያደርጉ ቤተሰቦቻቸው ያላቸውን ንብረት ለመሸጥ ሃሳብ አቅርበውላቸው እንደነበር ይናገራሉ።
ጥሪት አሟጠው፣ ቤተሰቦቻቸውን ያለ መጠለያ አስቀርተው፣ ጤናቸውን መመለስ ግን አልፈለጉም። "ሞት እንኳ ቢመጣ አንድ ነፍሴን ይዤ እሄዳለሁ" በማለት አሻፈረኝ አሉ።
መሪማ ሰዎች የኩላሊት እጥበት ለማድረግ የሚያስፈልገውን ወጪ መሸፈን አቅቷቸው ሲሞቱ ስታይ ነገም የእኔ እጣ ይህ ነው በማለት የፍርሃት ቀዝቃዛ ዳና ይሰማት ጀመር።

መሪማ ሞትና ሕይወት እጣ እየተጣጣሉባት እንደሆነ ታስብ እንደነበር ትናገራለች።
ሐኪሞች በኩላሊት እጥበት መዳን እንደማይቻል፣ ኩላሊት የሚሰጥ ዘመድ ካገኙ ንቅለ ተከላ ማካሄድ ብቸኛ መፍትሄ እንደሆነ ለሁለቱም እንደነገሯቸው ያስታውሳሉ።
መሪማ እህቶቿ ወደ ህንድ ሄዳ ንቅለ ተከላ እንድታካሄድ ሃሳብ አቀረቡ። ነገርግን እህቶቿን አስቸግራ፣ አንገት ማስገቢያ ቤታቸውን ሸጠው፣ ወደ ውጪ ሄዶ የመታከም ሀሳብ በጭራሽ አልነበራትም። ስድስት ሰባት ሰው የሚጠለልበትን ቤት ለሽያጭ ማቅረብ ቤተሰቡን እንደመበተን ተሰማት።

ከዘመዶቿ ውጪም የማንንም እጅ ላለማየት ለራሷ ቃል ገብታለች። ያላት ተስፋ እጥበቱን እያካሄደች ከነገ ማህፀን የሚወለድ ተስፋን መጠበቅ ብቻ ሆነ።
ተስፋ ጠፍቶ ሐዘን ባጠላበት አንድ ቀን ጆሮዎቿ መልካም ወሬ ሰሙ።

ሕይወት በክር ጫፍ

መሪማ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንደሚያካሂድ ስትሰማ ጆሮዎቿን ማመን አልቻለችም። ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት ህክምና ለማግኘት ተመዘገበች።
ወዳጅ ዘመድ ሁሉ ይህንን ዜና ሲሰማ ኩላሊቱን ለመስጠት ተሽቀዳደመ። አብድሩሃማን መሐመድ የመሪማ መሐመድ ልጅ ነው። ኩላሊታቸውን ለመለገስ ከተስማሙ ቤተሰቦች መካከል ቀዳሚው ነበር። ነገር ግን በተደረገለት ምርመራ እንደማይችል ተነገረው።
በዚህ ቀን እንኳ ለእናቱ ያለውን ማካፈል ባለመቻሉ አዘነ። አካሏን ከደፍላ ያኖረችው እናቱን አካሉን ከፍሎ ማኖር ባለመቻሉ ከፋው። የአክስት ልጅ የአጎት ልጅ እኛ አለን ሲሉ ተረባረቡ። የሚመረመሩት ሁሉ በአንድም በሌላም ምክንያት መስጠት እንደማይችሉ እየተነገራቸው ተመለሱ። ለመሪማ መሐመድ ኩላሊት የሚለግስ ሳይጠፋ ኩላሊቱ ግን ጠፋ።
በዚህ መሀል የአክስቷ ልጅ ሙና መሀመድ ስትመረመር መስጠት እንደምትችል ታወቀ። "ለአክስቴ መዳን ምክንያት በመሆኔ ደስተኛ ነኝ" ትላለች ሙና። መሪማ ግን "ለአቧቷ አንድ ሴት ልጅ፣ ያልወለደች፣ ያልከበደች እንዴት ኩላሊቷን ወስጄ በአንድ አስቀራታለሁ" ስትል አሻፈረኝ አለች።
አቶ አለነ ወልደማሪያም ከሐኪማቸው ንቅለ ተከላ በሐገር ውስጥ ማግኘት እንደሚችሉ ሲነገራቸው 'እራሴን ለማኖር የሌላ ሰው ኩላሊት እንዴት እወስዳለሁ' የሚል ሀሳብ ፈትሮ ያዛቸው። በሕይወት መንገድ ላይ ራሳቸውን አስቀድመው ያዩ ስለመሰላቸው አንገራገሩ።
ሐኪሙ ግን በአንድ ኩላሊት መኖር እንደሚቻል በመንገር ለማሳመን ሞከሩ። እህት ወንድሞቻቸውም እኛ እያለን ወንድማችን አልጋ ይዞ አይቀርም በሚል ተረባረቡ።
የመኖር ዋጋው፣ የነገን ፀሐይ ማየት፣ በወዳጅ ዘመድ መካከል በፈገግታ ታጅቦ የመገኘት ዋጋ ውድ ነው የሚሉት አለነና መሪማ የዘመዶቻቸውን ስጦታ ተቀብለው ንቅለ ተከላው ተካሄደላቸው።
ህክምናው ደግሞ በአብዛኛው በነፃ የሚሰጥ መሆኑ የበለጠ ደስታቸውን አድልቦታል። ሁለቱም መድሃኒቱን ለመግዛት ብቻ ገንዘብ እንደሚያወጡ ተናግረዋል።
"በአንድ ኩሊት የሚኖር ሰው ስጋት ሊኖረው አይገባም"
ዶ/ር ብርሃኑ ወርቁ የኩላሊት ስፔሻሊስት ሲሆኑ በጳውሎስ ሆስፒታል የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማዕከል ይሰራሉ። በሆስፒታሉ ማንም ሰው የኩላሊት መድከም ካጋጠመው መጥቶ በነፃ መታከም ይችላል የሚሉት ዶ/ር ብርሃኑ ነገር ግን ታማሚው ኩላሊት የሚለግሰው፣ ዘመድ የሆነ አንድ ሰው ሊኖረው ይገባል ሲሉ ያስረዳሉ። ዝምድና ካላቸው ሰዎች ብቻ የኩላሊት ልገሳውን የሚቀበሉት በዋናነት ህገወጥ የአካል ሽያጭን ለመከላከል እንደሆነ ያስረዳሉ።
የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዲካሄድላቸው የሚፈልጉ ሕሙማን ማሟላት ካለባቸው ነገሮች መካከል አንዱ ኩላሊቱን ለመስጠት ፈቃደኛ የሆነ፣ እድሜው በራሱ ለመወሰን የሚያስችለው ደረጃ ላይ የሚገኝ ሰው ማምጣት እንደሆነ ዶ/ር ብርሃኑ ይናገራሉ።
ሌላው የኩላሊትም ሆነ ሌሎች ተጓዳኝ በሽታዎች የሌሉበት፣ በተለይ በረዥም ጊዜ በራሳቸው የኩላሊት መድከም ሊያመጡ የሚችሉ ህመሞች የሌሉበት ግለሰብ መሆን አለበት ይላሉ። አክለውም ኩላሊት የሚሰጡ ሰዎች ከመስጠታቸው በፊት አስፈላጊው ምርመራ ሁሉ እንደሚደረግላቸውም ያስረዳሉ።

በአንድ ኩላሊት የሚኖሩ ሰዎች የተለየ ስጋትና ፍራቻ ሊኖራቸው አይገባም የሚሉት ዶ/ር ብርሃኑ ለጋሾችምሆኑ ተቀባዮች ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ መምራት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ይመክራሉ።
ኩላሊታቸውን የሚለግሱም ሆኑ የሚቀበሉ በአግባቡ የህክምና ክትትላቸውን ማድረግና የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር መከተል ያስፈልጋቸዋል የሚሉት ዶ/ር ብርሃኑ፤ ንቅለ ተከላውን ያደረጉ ሰዎች ደግሞ አዲሱ ኩላሊታቸው ከእነርሱ ጋር አብሮ የሚቆየው መድሃኒታቸውን በአግባቡ መውሰድ እስከቻሉ ድረስ ብቻ ስለሆነ የሐኪሞችን ምክር መከተል የግድ ነው ይላሉ።
"የኩላሊት መድከም ገጥሟቸው ንቅለ ተከላ የሚካሄድላቸው ሕሙማን የወሰዱት የሌላ ሰው ኩላሊት ስለሆነ ሁሌም አዲሱ ኩላሊት ሰውነታቸው ውስጥ እንግዳ ሆኖ ነው የሚኖረው" የሚሉት ዶክተሩ መድሃኒታቸውን ካልወሰዱ አካላቸው ኩላሊቱን እንደባዕድ ስለሚቆጥረው ይታመማሉ ይላሉ።
ኢትዮጵያ ውስጥ የኩላሊት ንቅለ ተከላ በብቸኝነት የሚሰጠው የመንግሥት የጤና ተቋም ቅዱስ ጳውሎስ ሲሆን አገልግሎቱን መስጠት ከጀመረ ሦስት ዓመት እንደሆነው ዶ/ር ብርሃኑ ይናገራሉ። እስከ አሁን ድረስ በማዕከሉ አንድ መቶ ያህል ሰዎች የኩላሊት ንቅለ ተከላውን አካሂደዋልም ይላሉ።

Saturday, February 9, 2019

እነ አቶ በረከት በማረሚያ ቤቱ ኢንተርኔት የለም ሲሉ ለፍርድ ቤት ተናገሩ


በጥረት ኮርፖሬት የሃብት ብክነት የተጠረጠሩት አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሣ ዛሬ በባህር ዳርና አካባቢዋ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ባለፈው በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ማስረጃዎችን ማየቱንና የምስክሮችን ቃል መቀበሉን አሳውቋል።
ሆኖም ጉዳዩ ከባድ፣ ውስብስብና ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑም በላይ ምስክሮች እና ሰነዶች በሃገር ውስጥ እና ከሃገር ውጪ መገኘታቸውን አስታውሶ ምርመራውን አለማጠናቀቁን አስታውቋል።
በረከት ስምኦን
ከዚህ ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የሕግ ሥልጣን በሌለው አካል መከሰሰሳቸውን የጠቀሱት አቶ በረከት ሰምኦን ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮው ውድቅ አንዲሆን ጠይቀው ነበር።
የዳሽን ቢራ ሁሉም ሰነዶች ተሟልተው እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ ታደሰ ካሣ በበኩላቸው መነግሥት አስረን አናጣራም፤ አጣርተን ነው የምናስረው ማለቱን ጠቅሰው የተጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ አነሱን በእስር ለማቆየት ብቻ መሆኑን በመጠቆም ውድቅ አንዲሆን ጠይቀዋል።
የግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን ውስብስብነትና መረጃዎች በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ መገኘታቸውን ከግምት በማስገባት የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮውን ፈቅዷል።

አቶ በረከት ስንገባም ስንወጣም አየተሰደብንና ስማችን እየጎደፈ ነው ብለዋል።
ጠበቃ ማግኘት ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ እንዲያቆምላቸውና ከቤተሰባቸው ጋር የመገናኘት ዕድል እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ለመፃፍ የሚያስችላቸው ኮምፒዩተር እንዲገባላቸው ጠይቀዋል። አቶ በረከት በማረሚያ ቤት ውስጥ ኢንተርኔት የለም ሲሉም ተደምጠዋል።
የሚደርስባቸውን ዘለፋ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የሚደርስባቸውን ዘለፋ ለማስቆም እንደሚሰራ አስታውቋል።

በጎንደር የተለያዩ ዞኖች በተከሰተ ግጭት 39ሺህ ሰዎች ተፈናቀሉ

የአማራ ክልል ኮሙኑኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰማኸኝ አስረስ
ሰሞኑን በጎንደር እና ዙሪያው በተከሰቱ ግጭቶች በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን እና በሺዎች የሚቆጠሩ መፈናቀላቸውን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ አሰማኸኝ አስረስ ዛሬ ከሰዓት ጋዜጠኞችን ሰብስበው ''ሰሞኑን በማዕከላዊ ጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ፣ ላይ አርማጨሆ እንዲሁም በጭልጋ አካባቢ ግጭቶች ተከስተው በሰዎች ሕይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። ጎንደር አካባቢ በተፈጠረው ግጭት የተፈናቃዮች ቁጥር ወደ 39ሺህ ደርሷል'' ብለዋል።
አቶ አሰማኸኝ በባህር ዳር ከተማ በሰጡት መግለጫ፤ የዛሬ ሳምንት በዕለተ ዓርብ ጥር 24 በማዕከላዊ ጎንደር ሰፍሮ የነበረው የመከላከያ 24ኛ ክፍለ ጦር ቦታውን ለቅቆ 33ኛው ክፍለ ጦር እስኪረከብ ድረስ በተፈጠረው ክፍተት፤ ፅንፈኛ ያሏቸው ቡድኖች የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ላይ ተኩስ ከፍተው በሁለቱም ወገኖች መካከል የሰው ሕይወት መጥፋቱን ተናግረዋል። ከዚያ በኋላ ባሉት ቀናት የተለያዩ ቀበሌዎች የሰው ሕይወት መጥፋቱን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች በእሳት እንዲጋዩ መደረጋቸውን አብራርተዋል።
Image may contain: one or more people, shoes and outdoor
ጥር 27፣ 28 እና 29 በነባሩ ጭልጋ ወረዳ መቋሚያ ማርያም፣ ችሃ ማንጊያ፣ አማኑኤል ቀን ወጣ፣ ናራ እና አንከር አደዛ በተሰኙ ቀበሌዎች፤ ቤቶች መቃጠላቸውን እንዲሁም ጥር 29 እና 30 ደምቢያ ወረዳ ሰቀልተ ሰሃ መንጌ እና ድርማራ ቀበሌዎች ቤቶች መቃጠላቸውን እና በድርማራ ቀበሌ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን ጨምረው ተናግረዋል።
እንደ አቶ አሰማኸን ገለፃ ትናንት ማታ በጎንደር በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ወጣቶች የከብት ማደለቢያ ላይ ቃጠሎ ደርሶ 40 የቀንድ ከብቶች ተቃጥለዋል። ቃጠሎው ከአለመረጋጋቱ ጋር መያያዝ አለመያያዙን ገና መጣራት እንዳለበትም ጨምረው አብራርተዋል። አቶ አሰማኸኝ በመቀጠል ያብራሩት፤ በምዕራብ ጎንደርም ግጭት እንደነበረና በዚህም ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ነው።
ከዚህ በፊት የተፈጠረው ችግር መረጋጋት ቢያሳይም በቅርቡ ግን መተማ አካባቢ ችግር ተከስቶ የሰው ሕይወት ማለፉን አስረድተዋል።
''በምዕራብ ጎንደር ተከስቶ የነበረው ግጭት ወደ ሰላም እየመጣ ነው። ነገር ግን ጥር 30 በምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ ግጭት ተከስቶ የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል'' ብለዋል።
Image may contain: 1 person, outdoorለመሆኑ በግጭቱ የተፈናቀሉ ሰዎች ምን እየተደረገላቸው ነው ተብለው ተጠይቀው፤ መንግሥት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሆነ ገልፀው ማህበረሰቡ ዛሬም እርስ በእርሱ እየተደጋገፈ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በዛሬው ዕለት ከጎንደር አርማጨሆ የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም 2 ሰዎች በመታገታቸው ምክንያት ሌሎች ላይ የማሳደድ ተግባር በመፈፀሙ መቋረጡን ተናግረዋል።
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የፖሊስ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር እንየው ዘውዴ ደግሞ ለቢቢሲ ሲናገሩ ''አማራ እና ቅማንት ለረዥም ዓመታት አብረው የኖሩ እና ወደፊትም አብረው የሚኖሩ ሕዝቦች ናቸው። ነገር ግን በመካከላቸው ሌላ ኃይል ገብቶ ደም እያቃባ ይገኛል። እሱን ለመከላከል የክልሉ ኃይል እና ሃገር መከላከያ በመቀናጀት ሥራ እየተሠራ ነው''ብለዋል።
ኮማንደር እንየው ''ሌላ ኃይል'' ያሉት ቡድን የትኛው እንደሆነ እንዲነግሩን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ''ይሄ ግልጽ ነው። ሁሉም ያውቀዋል። የአደባባይ ምስጢር ነው'' ከማለት ውጪ እሳቸው ''ኃይል'' አቶ አሰማኸኝ ደግሞ ''ጸንፈኛው ቡድን'' ያሉትን አካል በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል።

በአዲስ_አበባ ነዋሪ ላልሆኑ የቀበሌ መታወቂያ እየተሰጠ እንደሆነ ለሚዲያዎች መረጃ ሰጥታችኋል በማለት ፣ ታከለ_ኡማ የከተማ አስተዳድር ሰራተኞችን ከስራ ማገዱን

በአዲስ_አበባ ነዋሪ ላልሆኑ የቀበሌ መታወቂያ እየተሰጠ እንደሆነ ለሚዲያዎች መረጃ ሰጥታችኋል በማለት ፣ #ታከለ_ኡማ የከተማ አስተዳድር ሰራተኞችን ከስራ ማገዱን ሸገር ዘግቧል !!


Image may contain: 1 person

wanted officials