Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, June 20, 2014

የሕወሓት የደህንነት ባለስልጣናት በከፍተኛ የዘረፋ እና የማገት ስራ ላይ መሰማራታቸው ተጋለጠ‬

የሕወሓት የደህንነት ባለስልጣናት በከፍተኛ የዘረፋ እና የማገት ስራ ላይ መሰማራታቸው ተጋለጠ
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በቅርቡ የታጠቁ ግለሰቦች ከዶላር ጋር በተያያዘ በመሃል አዲስ አበባ በጠራራ ጸሃይ ሁለት ሚሊዮን ብር በመዝረፍ መሰወራቸውን ተከትሎ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዘረፋውን የፈጸሙት ግለሰቦች በአቶ ጌታቸው እና በአቶ ኢሳያስ የሚመራው የደህንነት የማፊያ ቡድን አባላት መሆናቸው ታውቋል። እስካሁን በምርመራ ላይ ተብሎ ሌሎችን በመያዝ ካለወንጀላቸው ያሰረው ፖሊስ ከሳሾች የተባሉትን በመክሰስ እንዲሁም ከሳሾች ዘራፊ ግለሰቦቹ እነዚህ አይደሉም ቢሎም ፖሊስ ለመስማት ፈቃደኛ አልሆነም።
በመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት መኮንኖች ስር የሰደደው የሙስና እና የዘረፋ አድራጎት በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥም ከሹሙ ከአቶ ጌታቸው እና ከባለስልጣኖቻቸው ጀምሮ እስከ ገራፊዎች ድረስ መንሰራፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደውስጥ አዋቂ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ የደህንነት ባለስልጣኖቹ የተዘፈቁበት የሙስና ተግባር በተጨማሪ ዘረፋን እና ሴት መድፈርን እንዲሁም የቡድን ወንጀሎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል::በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በማሰር እንዲሁም የሙስና ወንጀል ተገኝቶብሃል ይህን ያህል ገንዘብ አምጣ ካላመጣህ እንገድልሃለን እስከማለት በከመድረሳቸውም በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ለፖሊስ የጠቆመ ባለሃብት በማፈን ንብረቱ ባማገድ እና በተለያዩ ስልቶች የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲሰጥ በማስገደድ ላይ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል::
ከዚህ ቀደም በሙስና የተከሰሱ የስርኣቱ ባለስልጣናትን ተገን በማደርግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ባለሃብቶችን በመከታተል እና ደህንነት ቢሮ ድረስ በመውሰድ በሙስና ከታሰረው ስም እየተጠቀሰ … ከሚባል ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አለህ ማስረጃ ተገኝቶብሃል በማለት በፈጠራ ወንጀል ባለሃብቱን በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የነበረ እና እንዲሁም የአዲስ አበባን ቆነጃጅት ቢሯቸው ድረስ በግብረአበሮቻቸው አፋኝነት እና አስገዳጅነት በመውሰድ ካለፍላጎታቸው አስገድደው በመድፈር ላይ ናቸው ያሉት ምንጮቹ ተራ የደህንነት አባላት ለዚሁ ተልእኮ ተሰማርተው የሚሰሩት ምንም አይነት ወንጀል በቡድን ሲፈጽሙ የሚጠይቃቸው አለመኖሩን የሕዝቡን በደል የከፋ አድርጎታል::
ኢትዮጵያውያን በሕወሓቱ የደህንነት መዋቅር የሚመራ የሽብር ተግባራትን አጥብቆ ስለሚፈራ እና በየጊዜው በሕወሓት ደህንነቶች መሪነት የሚወሰዱ እርምጃዎች በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትን በመፍጠራቸው በየእስር ቤቱ የሚካሄዱ ሕገወጥ ጸረ ፍትህ ተግባራት እና የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የኢትዮጵያውያን የቀን ተቀን አጀንዳ ሆነው መምጣታቸው ገዢው ፓርቲ ሕዝቡን ምን ያህል እንዳሸበረ ይጠቁማል ሲሉ ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials