Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, February 25, 2018

እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ የቂሊንጦ እስር ቤት ኃላፊን በዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሚጠይቋቸው ገለፁ





በጌታቸው ሺፈራው

በእነ ማስረሻ ሰጤ ክስ መዝገብ ስር የተከሰሱ እስረኞች የቂሊንጦ እስር ቤት ኃላፊን በዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሚጠይቋቸው ገልፀዋል። ዛሬ ታህሳስ 24/2010 ዓም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በተከሳሾቹ ላይ የዐቃቤ ሕግ 83ኛ ምስክር ሆነው የቀረቡት የቂሊንጦ እስር ቤት ደህንነትና ጥበቃ ኃላፊ ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ ኣብርሃ ሊመሰክሩ በቀረቡበት ወቅት ከእስረኞቹ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።


ተከሳሾቹ ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም በቂሊንጦ ቃጠሎ ወቅት እስረኞችን በመግደልና በማስገደል እንዲሁም አስከሬናቸውን በእሳት በማቃጠል ተጠያቂ ናቸው ብለዋል። 1ኛ ተከሳሽ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ ምስክር ሆነው የቀረቡትን ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ በዘር ማጥፋት ወንጀል የሚጠይቋቸው በመሆኑ መመስከር እንደሌለባቸው ገልፆአል። 5ኛ ተከሳሽ አግባው ሰጠኝ ምስክሩ በቂሊንጦ ቃጠሎ ወቅት ሰው ገድለው እሳት ውስጥ በመጨመር ወንጀል እንደፈፀሙ ለችሎቱ ገልፆአል። በተመሳሳይ 4ኛ ተከሳሽ አበበ ኡርጌሳ ምስክሩ ለችሎቱ ጠቁመው ባሳዩት ወቅት “ያውቀኛል። ሲገድልና ሲያስገድል የነበረ ሰው ነው። በዘር ማጥፋት ሊጠየቅ የሚገባው ሰው ነው” ብሏል። 33ኛ ተከሳሽ ሸምሱ ሰኢድ “ገድሎ ማዕረግ የተሰጠው፣ ዞን 5 የተባለ የድሃ ልጅ የሚሰቃይበት እስር ቤት ያሰራ ሰው ነው።” ሲል ዋና ኦፊሰሩ እንዳይመሰክሩ ተቃውሟል። በተጨማሪም 31ኛ ተከሳሽ ጌታቸር እሸቴ “ምስክሩ ህሊናቸውን የሸጡ ናቸው። እንደሳቸው ህሊናቸውን የሸጡ አሉ። መንግስት ጨፍጭፌያለሁ ብሎ ይቅርታ ከጠየቀ በኋላ እንኳን ከስህተታቸው አልተማሩም” ብሏል።

ተከሳሾቹ ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ እንዳይመሰክሩባቸው ተቃውሞ ካሰሙ በኋላ፣ 18ኛ ተከሳሽ አንጋው ተገኘ “እኛ ፍትህ እናገኛለን ብለን ሳይሆን ለታሪክ እንዲመዘገብ ስለምንፈልግ ይመስክር” ብሏል። ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ እንዲመሰክሩ ተከሳሾቹን ካግባቡ በኋላ ተከሳሾች ምስክርነቱ እንዲቀጥል ተስማምተዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials