Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, February 5, 2018

ጎንደር ከተማ ሆቴል እና የንግድ ሱቅ ተከፍቶላቸው የወልቃይትን ጉዳይ በዋነኛነት የሚከታተሉ የህወሓት የደህንነት አባላት

የህወሓት የደህንነት አባላት የሚጠቀሙት ሽፋን ተጋለጡ ፡፡
ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማሰቃየት እና የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ከሚጠቀምባቸው ተቋማት አንድና ዋናው የሆነው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መ/ቤት ሲሆን ይህ ተቋም በቋሚነት ቀጥሮ ከሚያሰራቸው ኦፊሰሮች በተጨማሪ የተለያዩ ሽፋኖችን በመስጠት በወኪልነት ያሰራቸዋል ፡፡
በተለይም በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ሆቴል እና የንግድ ሱቅ ተከፍቶላቸው የወልቃይትን ጉዳይ በዋነኛነት የሚከታተሉ እንደነበሩ እና በተለያየ ጊዜ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ሲገለፅ የቆየ ሲሆን ፡ በቅርቡ ደግሞ በሰሜን ወሎ በወልዲያ ከተማ ልዩ ሽፋን ተዘጋጅቶላቸው ነጋዴ ወይም "ልማታዊ ባላሀብት" የሚል ሽፋን ተሰጥቷቸው ወደ ትግራይ የተካለሉትን የራያን መስመር አላማጣና ኮረምን የሚከታተሉ የህወሓት ሰዎች ያሉ ሲሆን ከነዚህ የደህንነት ወኪል በመሆን ከሚያገለግሉ ሰዎች አንድ እና ዋናው አስተባባሪ የሆነው አቶ ኪዳነማሪያም ካህሳይ መዝገቡ የተባለው "የአርሲማ ሆቴል ባለቤት ‘’ እንደሆነ የሚታወቀው ሰው በወልዲያ ከተማ በርካቶችን ሲያስገድል ፡ አድራሻቸውን ሲያስጠፋ ሲያሳስር የነበረ እና አርሲማ ሆቴልን የህወሓት አልሞ ተኳሾች እንዲያርፋበት እና የቡድን መሳሪያዎች ጠምደው ዜጎችን በግፍ እንዲጨፈጭፋ ያደረገ ሰው ነው ።
የዚህ ሰው እና የሊሎች ወኪሎች መረጃዎች እና ሰነዶች ለአግ7 መረጃ ክፍል የደረሱት ሲሆን ፡ ለዛሬው ይህ ከላይ የተጠቀሰው ግለሰብ ወልዲያ እንደሚኖር ውጫዊ ሽፋን ሲሆን ነገር ግን በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መ/ቤት አማካኝነት በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ወገራ ወረዳ ቀበሌ 02 እንደተወለደ እና የመኖሪያ አድራሻው ከዚያ እንደሆነ የሚገልፅ የነዋሪነት መታወቂያ ወጥቶለት ፡ ከዚያም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገለግሎት መ/ቤት የውስጥ ደህንነት ዋና መመሪያ ዳሪክተር በሆነው የህወሓቱ ሰው አማኑኤል ኪሮስ አማካኝነት የኦሮሚያ ክልል ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኃላፊ ለሆነው ተስፋዬ ኡርጊ የተባለውን በማዘዝ በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ የመንጃ ፍቃድ ቁጥሩ 21- 08484 የሆነ በቀን 01/03/2007 ዓ/ም ወጥቶ ተሰጥቶታል ፡፡
እንግዲህ በዚህ መልክ ሽፋን ተሰጥቶት በሚሊዮን የሚቆጠር የሕዝብ ገንዘብ ተመድቦለት ባለ ሁለት ፎቅ ሆቴል እና የንግድ ድርጅት መሀል ወልዲያ ተከፍቶለት የንፁሃንን ደም ሲያፈስ እና ሲመጥ የነበረ ሰው ነው
በመሆኑም ህዝቡ ማን ገዳይ እና አስገዳዩን ለይቶ ያውቃል ማንነትን መሰረት ባአደረገ መልኩ ጥቃት ቢፈፀም ኑሮ የትግራይ ተወላጅ የሆኑት አቶ ገነተ ልዑል ላይ በእሳቸው እና በድርጅታቸው ላይ እርምጃ በተወሰደባቸው ነበር ፡፡
በመሆኑም ለአግ7 መረጃ ክፍል ከደረሱ የሰነድ መረጃዎች ውስጥ ለዛሬው የኪዳነማሪያም ካህሳይን መንጃ ፍቃድ ኮፒ እና መሀል ወልዲያ የተሰራለትን ሆቴል ከዚህ ዜና ጋር አውጥተንዋል ፡፡
ሊሎች መረጃዎችን በቀጣይ የምናወጣ መሆኑን እንገልፃለን ፡፡
#ድል ለሕዝብ !!!
#የአግ7 ዘመቻ ነፃ ትውልድ ፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials