Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, November 8, 2018

"ቤተ ክርስትያን በአማርኛ መስበክና መዘመር ተከልክሏል" ዲ/ን ላሊበላ ሙላው



"ቤተ ክርስትያን በአማርኛ መስበክና መዘመር ተከልክሏል"
ዲ/ን ላሊበላ ሙላው ( ለግዮን መፅሔት)
"ወልቃይት በአሁኑ ሰዓት በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለችው። አማርኛ መፅሐፍ ማንበብ፣ በአማርኛ መዝፈን፣ መፈከር፣ መሸለል፣ በአማርኛ ማውራትና በስልክ መነጋገር ተከልክሏል። የአማርኛ ፅሑፍ ያለባቸው ቲሸርቶችን መልበስ ተከልክሏል። የጠ/ሚኒስትር ዓብይ፣ ለማ መገርሳ፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የፋሲል ግንብ፣ የዐፄ ቴዎድሮስ ምስል ያለባቸውን አልባሳት የለበሰ ሰው እስራትና ግርፋት ነው የሚጠብቀው። ወልቃይት ላይ ቤተ ክርስትያን ውስጥ በአማርኛ እንዳይሰበክ ተከልክሏል። ታግዷል። ስብከት በትግርኛ እንዲሆን ተደርጓል። አማርኛ ተወግዟል ማለት ይቻላል።"

No comments:

Post a Comment

wanted officials