Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, October 14, 2016

ደራሲ ኃይሉ ፀጋዬ በEBC ቀጥታ ፕሮግራም ላይ በአርሂቡ ላይ ቀርቦ ስለ ወቅታዊ ፓለቲካ ተጠይቆ በድፍረት መንግስትን ተች ቶዋል

ደራሲ ኃይሉ ፀጋዬ በEBC ቀጥታ ፕሮግራም ላይ በአርሂቡ ላይ ቀርቦ ስለ ወቅታዊ ፓለቲካ ተጠይቆ በድፍረት መንግስትን ተች ቶዋል !!!
<<አሁን ለተፈጠሩት ችግሮ ሁሉ ትልቁን ኃላፊነት መውሰድ ያለበት መንግስት ነው :: እኔ በናዝሬት (አዳማ) ነው ተወልጄ ያደኩት የኦሮሞ ሕዝብ ምን ስጠይቅ እንደነበር በደንብ ተከታትያለው ፣ ህገመንግስታዊ ጥያቄ ነው የጠየቀው :: በአማራው ክልል የወልቃይት የህዝብ የጠየቀውም ህገመንግስታዊ ጥያቄ ነው :: መንግስት በሕዝብ ተመረትኩ እያለ ለሚንሱት ጥያቄዎች ሕሉ ጥይትን መፍትሄ ካደረገ እንዴት ይሆናል :: ሕዝቡን ማዳመጥ አለበት :: በጉልበት በመተኮስ የትም አይደረስም :: ዓለም ላይ ትላልቅ ቀውሶች ችግሮችን በግዜ መፍታት ካለመቻል የመጡ ናቸው ::
እውነት እንነጋገር ከተባል እዚች ሀገር በጣም ብዙ ልያሳምፁ የሚችሉ ችግሮች አሉ ፣ ሕዝብ በጣም ለብዙ ዓመት ታግሶ ታግሶ የሚሰማው ስላጣ ነው ወደዚህ አይነት አደገኛ ሁኔታ የገባው :: ሙስናው ፣ መልካም አስተዳደሩ በጣም በጣም የከፋ ደረጃ ደርሶዋል :: የህዝብ ምሬት እውነትነት አለው :: ሕዝብ ለትንሽ ነገር አያምፅም ከአቅሙ በላይ ሲሆን እንጅ ::
ሌላው ሁሉ ቢቀር በየሚድያው የሚወራው አንድ አይነት ድምፅ ነው ሕዝብ ሬታዉን ችግሩን የሚተነፍስበት ሚድያ ያስፈልገዋል :: ሀገር በደዚህ አይነት ሁኔታ አትቀትልም :: አሁንም ችግሩን በትዘላቂነት ለመፍታት ትናንች ለውጦችን ማድረግ ሳይሆን የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ ተገንዝቦ በአግባቡ መመለስ ያስፈልጋል :: ይህን የማድረግ ትልቁ ኃላፊነት ደግሞ የመንግስት ነው :: ትልቅ ኃላፊነት አለበት ::>>

አርቲስት ማለት እንደዚህ ነው ... የፖለቲካ ወገንተኚነት የሌለበት የህዝብ ልጅ ነኝ አንድም ሰው አይሙት የሚል መንግስትን በድፍረት ለህዝብ ትክክለኛ መልስ መስጠት አለበት ግን በጠበንጃ አይደለም የሚል ....
ሰላምሽ ይብዛ እናት ሀገሬ እማማ ኢትዮጵያ💚💛!


No comments:

Post a Comment

wanted officials