Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, October 31, 2016

በአማራው ተጋድሎ የተነሳ ዳሸን ቢራ ኪሳራ ውስጥ እየወደቀ ነው | “ዳሸን ቢራ የጠጣ የወገኑን ደም የጠጣ ነው”



dashen
(ዘ-ሐበሻ) የአማራው ሕዝብ ከትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ጋር እያደረገ ባለው የነጻነት ትግል አንደኛው አካል ዳሸን ቢራን ማዳከም እንደሆነ በተደጋጋሚ ከአማራው ተጋድሎ አስተባባሪዎች ሲገልጹ ነበር:: የአማራው ተጋድሎ በተፋፋመባቸው ጎንደር እና ጎጃም የዳሽን ቢራን የጫኑ መኪኖች ጥቃት ሲደርሰባቸው ቆይቷል:: በተለይም ዳሸን ቢራ በአማራ የልማት ድርጅት ስም የተቋቋመ የትግራይ ነጻ አውጪው መንግስት ንብረት በመሆኑ ይኸው ጨካኝ መንግስት አማሮችን ሲገድል የዳሸን ቢራ ንብረቶችን ሁሉ ተጠቅሟል::
በአሁኑ ወቅት በመላው አማራ ክልል ዳሸን ቢራን የጠጣ የወገኑን ደም የጠጣ ነው በሚል በተደረገ ቅስቀሳ ሕዝብ ቢራውን መጠጣት አቁሟል:: ሰዎች ሲጠጡ ከተገኙም “የወንድምህን ደም ጠጣ” እየተባሉ እንደሚረገሙ የሚደርሰን መረጃ ያመለክታል::
ከአማራ ክልል አሞራው ምንአለ ባሻ በለቀቁት መረጃም ይህንኑ አረጋግጠዋል:: መረጃቸው እንደወረደ ይኸው:-
የልጆቻችን ደም አንጠጣም ያለው የአማራ ህዝብ ከዳሸን ጋር እጅግ ተለያይቷል።በተለይም የባህርዳሩ ብቸኛ አከፋፋይ #ኮበል ኢንዱስትሪ ጥበቃዎች ባህር ዳር ላይ ወጣቶችን ከአጋዚ ጋር በመተባበር በጥይት ካረገፏቸው በኋላ ዳሸን በሁሉም የአማራ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ከህዝብ ተለይቷል።
ጎንደር እንፍራንዝ አካባቢ የተወሰደው እርምጃ ለዚህ ማሳያ ነው።ይህ ያስጨነቀው የጥረት ኮርፖሬት በግዳጅ እንዲሸጡ እና እንዲገዙ በሚል #የባህርዳር ግሮሰሪ ባለቦቶችን #በአቫንቲሊሰበስብ መሆኑን መረጃው ደርሶናል።የዳሽን ቢራ ስራአስኪያጅ በጠራውና ታደሰ ጥንቅሹ ይመራዋል በተባለው ስብሰባ ውይይቱ ምን ላይ ይደረሳል የሚለው መልስ እጅግ በጣም ቀላል ነው። #የልጆቻችን ደም አንጠጣም የሚለው የአማራ ህዝብ በሁሉም አካባቢ ቀጥሏል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials