Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, February 13, 2020

ህንድ፡ አልኮል በቧንቸው የመጣላቸው ነዋሪዎች በድንጋጤ ላይ ናቸው Alchohol via water pipeline

በመጠጥ የተሞላው ቧንቧ

Image copyrightJOSHY MALIYEKKAL
በህንዷ ግዛት ኬራላ ሰሞኑን አንድ አስደናቂ ጉዳይ ተከስቷል።
በአንድ የጋራ መኖሪያ ህንፃ የሚኖሩ ነዋሪዎች የቤታቸውን ቧንቧ በሚከፍቱበት ወቅት ቢራ፣ ብራንዲና ሌሎች መጠጦች ጋር የተቀላቀለ የአልኮል መጠጥ መፍሰስ ጀመረ።
የሚሰነፍጥ ሽታ ያለው ቅልቅሉ ቡናማ ቀለም ያለው ሲሆን በህንፃው ማዕድ ቤቶች ባለው ቧንቧ በኩልም ነው የመጣው ተብሏል።
በዚህ ሁኔታ የተደናገጡት ነዋሪዎች የአካባቢውን ባለስልጣናት ስለ ሁኔታው ያሳወቁ ሲሆን፤ ውሃቸውም በድንገት ከአልኮል ጋር መቀላቀሉን ተረድተዋል።
እንዴት ሊቀላቀል ቻለ? ነገሩ እንዲህ ነው
ስድስት ሺ ሊትር የሚሆን ህገ ወጥ የአልኮል መጠጥ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ በጋራ መኖሪያ ቤቱ አካባቢ በሚገኝ ጉድጓድ ተቀምጦ ነበር።
በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋለው መጠጥ በመሬትም ስር ፈሶ ለትሪሱር ግዛት የመጠጥ ውሃ የሚያቀርበው የውሃ ጉድጓድ ላይ መቀላቀሉ ታውቋል።
በዚህም የውሃ መጠጥ ጉድጓድም አስራ ስምንት የጋራ መኖሪያ ቤቶችም ይጠቀሙበታል ተብሏል።
"በጣም ነው የደነገጥነው" በማለት ጆሺ ማልይካል የተባለ ነዋሪ ለቢቢሲ ሂንዲ ተናግሯል።

እንደ እድል ሆኖ በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰነፍጠው የአልኮል መጠጥ ከመጠጣት ቢያግዳቸውም፤ ለመጠጥም ሆነ ለመታጠቢያ የሚሆን ውሃ ተቸግረዋል።
"በውሃ ችግር ምክንያት ልጆች ትምህርት ቤት መሄድ አልቻሉም፤ ከስራም ቀርተናል" ብሏል ጆሺ ማልይካል
በውሃ ፋንታ በአልኮል መጠጦች የተሞላው ቧንቧImage copyrightJOSHY MALIYEKKAL
ነዋሪዎቹ ሁኔታውን ካስረዱ በኋላ ባለስልጣናቱ ስህተታቸውን ለማስተካከል ሞክረዋል።
ነገር ግን የውሃ ጉድጓዱን በደንብ ለማፅዳት አንድ ወር እንደሚወስድ ነዋሪዎቹም ገልፀዋል፤ ይህም ሁኔታ ነዋሪውን ባለስልጣናቱ እየቀዱ በሚያመጡት ውሃ እንዲወሰኑ አስገድዷቸዋል።
"በየቀኑ አምስት ሺ ሊትር የሚሆን ውሃ እየቀዱ ቢያመጡም በህንፃዎቹ ለሚኖሩ ቤተሰቦች በሙሉ በቂ ሆኖ አላገኘነውም" ብለዋል ጆሺ ማልይካል
የአካባቢው ባለስልጣናት ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምንም አይነት ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
የኬራላ ግዛት በአገሪቱ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ አልኮልን በሚወስዱ ነዋሪዎቿ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

No comments:

Post a Comment

wanted officials