Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Showing posts with label ‪#‎Ethiopia‬. Show all posts
Showing posts with label ‪#‎Ethiopia‬. Show all posts

Thursday, September 14, 2017

Ethiopians irate over cancellation of pop star’s album release party



Ethiopians took to the social media to express their anger over the cancellation Sunday of Teddy Afro’s album release party by authorities who have also banned his new year concert.
Lyrics by Ethiopia’s king of reggae preaching unity and peaceful coexistence do not bode well for the ominous agenda of the ethnocentric regime that divide and rule the people with iron fist.
It was not the first time that the pop star’s concerts were cancelled. Several of Teddy’s concerts were banned, some in the last minutes, resulting in thousands of dollars loss to the singer.
Security forces on Sunday prevented the unloading of sound systems and band instruments from a truck parked at the Addis Ababa Hilton Hotel and told organizers of the party that the event had been banned by authorities.
Hundreds of invited guests were on their way to the dinner party that would have seen the video release of one of his songs from the most recent album that charted number one on Billboard’s World Albums.
His fans found the ban not only unfair to the artist but also ironical in that it came at a time when the regime has organized a ten day celebration of “Ethiopianism” in connection with the Ethiopian new year on September 11.
“Ethiopians want to celebrate #EthioNewYear Not with Chris Brown or Bruno Mars BUT #Teddy_Afro,” wrote Jordan Wmariam on his Facebook.
“Most of all I wish the new year to be a year that Ethiopians are equal under the law and for justice to prevail in the new year,” Teddy wrote
in a message posted on his Facebook after the cancellation of his party.

Thursday, May 5, 2016

በሼህ መሃመድ አላሙዲን የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው AESA One በኢሳት ጋዜጠኛ ተወልደ በየነ ላይ የከፈተው ክስ ውድቅ ሆነ

ኢሳት (ሚያዚያ 27 ፥ 2016) 

በሼህ መሃመድ አላሙዲን የገንዘብ ድጋፍ በሰሜን አሜሪካ የሚንቀሳቀሰው AESA One (ኤሳ ዋን) የተባለው ተቋም በኢሳት ጋዜጠኛ ላይ የከፈተው ክስ ውድቅ ሆነ። በኢሳት የመዝናኛ ክፍል ጋዜጠኛ በሆነው በጋዜጠኛ ተወልደ በየነ ላይ በአሜሪካ ቨርጂኒያ ግዛት የተመሰረተው ክስ ውድቅ የተደረገው፣ ራሱ ከሳሽ አካል ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉና ክሱን በማቋረጡ መሆኑንም መረዳት ተችሏል። ይህ አመታዊ የስፖርት ውድድሮችን ለማካሄድ ባለፉት 4 አመታት በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች ሲንቀሳቀስ የቆየው ይህ ቡድን፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶችንም ለማካሄድ በየአመቱ ከሃገር ቤት የሙዚቃ ባለሙያዎችን ሲጋብዝ ቆይቷል። በዚህ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እንዳይገኙ በማስፈራራት በተቋሙ ላይ ኪሳራ አድርሷል በሚል በጋዜጠኛ ተወልደ በየነ ላይ የተመሰረተው ክስ ውድቅ መሆኑ የታወቀው በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት መሆኑን መረዳት ተችሏል። ይህ በቢሊዮነሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሼህ መሃመድ አላሙዲን የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው ተቋም፣ ከ30 ዓመታት በላይ በሰሜን አሜሪካ የሚንቀሳቀሰውን የስፖርት ፌዴሬሽን ለመሰንጠቅ ሞክሮ፣ በፍ/ቤት ስሙን እንዳይጠቀም ዕገዳ ከተጣለበት በኋላ ኤሳ ዋን በሚል አዲስ ስያሜ አራት አመታት አስቆጥሯል። ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ የስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ለሁለት ለመክፈል የተደረገው ሙኬራ መክሸፉን ተከትሎ ተቋሙ በኤሳ ዋን የጀመረው አመታዊ ውድድር የኢትዮጵያውያንን ትኩረት ባለመሳቡ፣ ይልቁንም ዋናውን የስፖርት ፌዴሬሽን ለማዳከም የተደረገ እንቅስቃሴ ነው በሚል ስነ-ስርዓቱ በተመልካች ድርቅ ሲመታ መቆየቱን መረዳት ተችሏል፥ ተቃውሞዎችም ሲቀርብበት ቆይቷል። የኬነጥበብ ባለሙያዎቹ በዝግጅቱ እንዳይሳተፉ የሚያግባባውም እንዲሁም የሚያስፈራራው ጋዜጠኛ ተወልደ በየነ ነው በሚል ክሱ መመስረቱንም መረዳት ተችሏል። ሆኖም ረቡዕ ዕለት ይኸው ክስ ውድቅ መደረጉም ተረጋግጧል። የቀድሞ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስተኢር አቶ ሬድዋን ሁሴን በአሜሪካ የገጠማቸው ተቃውሞ በማስመልከት በአክቲቪስት መኮንን ጌታቸው ላይ የመሰረቱት ክስ በተመሳሳይ ውድቅ መደረጉ ይታወሳል። በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በዋናነት ያቀፈውና ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የመጡ ኢትዮጵያውያን የሚታደሙበት ዓመታዊ የኢትዮጵያ የስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ዝግጅት በመጪው ሰኔ ወር መጨረሻ በካናዳ ቶሮንቶ እንደሚካሄድም ለማወቅ ተችሏል። ኢትዮጵያውያን በቋንቋና በፖለቲካ አመለካከት ሳይለያዩ የሚታደሙበት ይህ ዝግጅት መከበር ከጀመረ ከ30 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል። እኤአ ከፊታችን ጁላይ 3 እስከ 9 በካናዳ ቶሮንቶ ለ33ኛ ጊዜ ይከበራል።

Wednesday, May 4, 2016

‘I Was Forced to Drink My Own Urine’: Ethiopian prisoner


Photo-based graphic of Zelalem Workagegnehu by Melody Sundberg. Image used with permission.
Photo-based graphic of Zelalem Workagegnehu by Melody Sundberg. Image used with permission.
On April 15, 2016, the Ethiopian Federal High Court acquitted two men, Yoantan Wolde and Bahiru Degu, who spent more than 600 days incarcerated on terrorism charges that critics allege were politically motivated. Zelalem Workagenehu, a third man, was not so lucky. He was convicted and will be sentenced on May 10. (On April 26, the public prosecutor submitted a sentence aggravation statement to the court, and Zelalem was asked to file a sentence mitigation letter on his part.) Zelalem is a human rights advocate and a scholar who regularly contributed to the diaspora-run website DeBirhan.
All three were accused under Ethiopia's Anti-Terror Proclamation, which was adopted in July 2009. State officials defend the law, saying it is modeled on existing legislation in countries such as the United Kingdom.
Yonatan Wolde and Bahiru Degu were released after spending 647 days—almost two years—in prison, demonstrating a disturbing trend in Ethiopia where prisoners of conscience are locked away for long periods without a trial.
In what seemed to be a show of brute force, plainclothes security officers re-arrested Yonatan and Bahiru shortly after they left prison on April 18. The two men were held overnight at Maekelawi (Central) Prison, before being released again and warned that they're still under observation.They were also told by the securities “They would be killed if they made any moves,” their relatives say.
Zelalem was initially charged in October 2014, along with a group of nine other defendants that included Internet users, opposition politicians, and activists. So far, seven people in this group have been acquitted after spending more than a year in jail, after which they signed what they now say were false confessions, in order to escape further torture.
The charges against Zelalem include leading a terrorist organization (which is how the government came to define Ginbot 7, a pro-democracy political party founded byBerhanu Nega), conspiring to overthrow the government, and disseminating false information through reports on websites run by the diaspora. For instance, one of Zelalem's coauthors on the De Birhan Blog was also implicated in the case.
The case was later reduced to two charges: recruiting members to start an Arab-Spring-like revolution in Ethiopia and co-facilitating what the government says was a “training operation to terrorize the country.” (Zelalem says it was actually a training camp to build digital communication, social media, and leadership.)
Yonatan and Bahiru were charged with applying to the participate in Workagenehu's training camp, and suspected of joining Ginbot 7. (They denied these accusations.)
In his ruling, the judge reportedly said that applying to or participating in such training exercises was not illegal and so Yonatan and Bahiru should be acquitted. Despite their two years behind bars, Yonatan and Bahiru aren't entitled to any form of compensation. It's not yet clear if they intend to press the matter in court.
Bahiru Degu, who attended his former co-defendant's trial last week, struggles the most among the three men. He told the court he experienced extensive torture during the first three months of his detention:
I was forced to get naked and was regularly beaten. Due to the severity of the beating, I was unable to control my bowels [sic]. I was forced to drink my own urine.
Like Bahiru Degu, Zelalem Workagenehu and Yonatan Wolde also told the court about the severity of the torture committed against them in prison, saying guards were trying to force them to sign false confessions. A recent report published by Human Rights Watch revealed that Ethiopian investigators and police do abuse journalists and opposition activists, in order to extract confessions:
Police investigators at Maekelawi use coercive methods on detainees amounting to torture or other ill-treatment to extract confessions, statements, and other information from detainees. Detainees are often denied access to lawyers and family members. Depending on their compliance with the demands of investigators, detainees are punished or rewarded with denial or access to water, food, light, and other basic needs.
https://globalvoices.org/2016/05/02/i-was-forced-to-drink-my-own-urine-freedom-after-647-days-locked-up-but-not-for-all/

Thursday, April 14, 2016

በኦሮሚያ ክልል በመንግስት ሃይሎች የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አለም-አቀፍ ትኩረት አለማግኘቱን ሂውማን ራይትስ ዎች ገለጸ


ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008)
ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በኢትዮጵያ ጸጥታ ሃይሎች ቢገደሉም፣ አለም አቀፍ ማህበረሰቡ ዝምታን መምረጡ እንዳሳዘነው የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (Human Rights Watch) ትናንት ባወጣው መግለጫ ገለጸ።
በኦሮሚያ ክልል የታየው ተቃውሞ ከምርጫ 97 በኋላ ከተቀሰቀሱት የፖለቲካ ቀውሶች ትልቁ እንደሆነ የገለጸው የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (Human Rights Watch)፣ ይህ ተቃውሞ ግን በአለም አቀፍ መድረክ ያገኘው ተሰሚነት እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ገልጿል።
የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (Human Rights Watch) የመረጃ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው በአሁኑ ሰዓት ከኦሮሚያ ክልል የሚወጣ መረጃ ባለመኖሩ ምን እየተደረገ እንደሆነ ለማወቅ እጅግ ከባድ ነው።
መንግስት የመረጃ ዝውውርን ለማገድ የሚዲያ አፈና አጧጡፎ ባለበት በአሁኑ ሰዓት፣ አብዛኞቹ የማህበራዊ ሚዲያ ድረገጾች ጭምር በአገር ውስጥ እንዳይታዩ እንደተደረገና፣  ባለፈው ወር ሁለት የውጭ ጋዜጠኞችም ጭምር የታሰሩበት ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበር የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ትናንት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።
የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ 100 ኢትዮጵያውያን ላይ ያደረገው ጥናት እንደሚያመለክተው፣ የመንግስት ጸጥታ ሃይሎች ሰላማዊ ሰልፈኞች ናቸው ብለው በጠረጠሯቸው ሰዎች ላይ ሲተኩሱ፣ የዘጠኝ አመት ህጻናት ጭምር እንዳሰሩና፣ ካሰሯቸውም በኋላ ስቃይ ይፈጽሙባቸው እንደነበር መመስከራቸውን በሪፖርቱ አካቷል።
በኢትዮጵያ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚሰሩት ጥቂት የመገናኛ ብዙሃንና ዘጋቢዎችም አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመዘገብ ያልፈደሩበት ምክንያት በእስር ከመሰቃየት፣ አገር ለቅቀው ከመሰደድና ራሳቸውን ሳንሱር ከማድረግ አንዱን መምረጥ ስለነበረባቸው እንደነበር ሪፖርቱ ያብራራል።
ለቃለመጠይቅ የሚደፍሩ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ከፍርሃት የተነሳ ለውጭም ሆነ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በመንግስት ፖሊሲ ላይ ትችት እንደማያቀርቡና፣ ትችት ያቀረቡት ግን እንደታሰሩና እንደተንገላቱ የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች) በሪፖርት አስፍሯል።
ከውጭ የሚተላለፉ የሳቴላይት ቴለቪዥንና ሬዲዮ ጣቢያዎች ስርጭት እንዳይሰማ የኢትዮጵያ መንግስት የጸጥታ ሃይላት በማሰማራት በግለሰቦች ቤት የተተከሉትን የሳተላይት መቀበያ ሳህኖችን እንደሰባበረና፣ በሁዋላም የሳተላይት አቅራቢ ድርጅቶች ውላቸውን እንዲያቋርጡ እንዳስገደዳቸው ትናንት የወጣው አጭር ሪፖርት አትቷል።
በኦሮሚያ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ የመረጃን ክፍተትን በመጠኑም ቢሆን የሞላው የማህበራዊ ሚዲያ መሆኑን በሪፖርቱ ላይ ያሰፈረው የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች)፣ በአመጹ ሰዓት የቆስሉ ሰዎችን የቀረጹና ቪዲዮዎችን በፌስቡክ ያሰራጩ ስዎችን የመንግስት ጸጥታ ሃይሎች እየተከታተሉ እንዳሳደዷቸው ሪፖርቱ ያስረዳል።
ይህንን ለመግታት ሲባል የኢትዮጵያ መንግስት የድምጽና ምስል ስርጭት ግልጋሎት የሚሰጡ ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንደዘጋ ሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት ገልጿል። በመሆኑም ህጻናትን ጨምሮ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸሙት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ሳይደርሱ ቀርተዋል ብሏል።
የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት በዚህ አይነት ሸፍጥ በተሞላበት ሁኔታ ለረጅም ጊዜ ሊቀጥል እንደማይልች በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።
የኢትዮጵያ መንግስት በኦሮሚያ ለተፈጸመው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ከአጋር ድርጅቶችና አገሮች ጋር በመሆን፣ ነጻና ገለልተኛ አጣሪ ቡድን እንዲያቋቁም መክሯል። የህዝቡን መብት ለማፈን የወጡትንና የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን የሚጋፉ ህጎች የኢትዮጵያ መንግስት እንዲሽራቸውም ጠይቋል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በኦሮሚያ እየሆነ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከቀጠለ፣ በኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላምና ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሪፖርት አብራርቷል።

wanted officials