Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Showing posts with label #zEthiopians. Show all posts
Showing posts with label #zEthiopians. Show all posts

Sunday, September 17, 2017

Killings, displacement continue in Eastern Ethiopia as violence intensifies


Photo from social media showing displaced Oromos in Chinaksen
ESAT News (September 14, 2017)
Officials of the Oromo and Somali regional administrations traded accusations and counter accusations amid the death of scores of people on both sides in a new wave of violence.
The Somali administration said in a statement that in Aweday town alone, a commercial hub in Eastern Ethiopia, over 50 Somalis were killed in the last few days, while an official with the Oromo administration told ESAT that about 12,000 Oromos have been evicted from Jijiga. Clashes also flared up while the Oromos were on their way to Harar and they were attacked by the Somali Liyou Forces, according to the official. Twelve people were killed from the Somali side in a counter attack by the Oromos.
What began as a turf dispute between the two communities has now grown into deadly violence.
Analysts fear the worst in the East African country where ethnic politics has been the guiding principle of a regime known for its abysmal human rights record. Indifference by the regime in the face of deadly violence, the analysts say, tantamount to complicity.
Demonstrations were held in the labyrinth city of Harar, where according to information received by ESAT, the Agazi forces of the regime killed one person.
The violence has also spread to Somaliland where reports reaching ESAT show the Oromos were under attack and unknown number of people are feared to have been killed.

የኦሮምያና የሶማሌ ችግር ሶማሊላንድ ላይ ጥቃት አስፈፀመ – ሰሎሞን አባተ(ቪኦኤ)



በኦሮምያና በሶማሌ ክልሎች ወሰኖች ባሉ ወረዳዎች ውስጥ እየተካሄደ ካለው የጥቃት እርምጃዎችና ግጭቶች ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ከተፈጠረው የፀጥታ ቀውስ ጋር ተያይዞ ከሰማሌ ክልል የተፈናቀሉ ከአርባ ሺህ እስከ ሃምሣ ሺህ የሚሆኑ የኦሮሞ ተፈናቃዮች ምሥራቅ ሃረርጌ መግባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ ማምሻውን ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ዋሺንግተን ዲሲ — በኦሮምያና በሶማሌ ክልሎች ወሰኖች ባሉ ወረዳዎች ውስጥ እየተካሄደ ካለው የጥቃት እርምጃዎችና ግጭቶች ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ከተፈጠረው የፀጥታ ቀውስ ጋር ተያይዞ ከሰማሌ ክልል የተፈናቀሉ ከአርባ ሺህ እስከ ሃምሣ ሺህ የሚሆኑ የኦሮሞ ተፈናቃዮች ምሥራቅ ሃረርጌ መግባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ ማምሻውን ለቪኦኤ ገልፀዋል።በሌላ በኩል ደግሞ ጭናቅሰን ውስጥ ዛሬ በተፈጠረ ግጭት የሦስት ሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰምቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዚሁ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ቀውስ ጋር ተያይዞ ጎረቤት ሶማሌላንድ ውስጥ በስደት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ህይወት ያጠፋ ጥቃት እየተፈፀመባቸው መሆኑና ከፍተኛ ሥጋት ላይ እንደሚገኙ እየገለፁ ናቸው።

ሃርጌሣ ላይ ሁለት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተገድለው አንደኛው ላይ ጉዳት እንደደረሰት የሶማሊላንድ የፀጥታ ሚኒስትር ዴኤታ አስታውቀዋል።

ሶማሊያዊያኑ በኢትዮጵያዊያን ላይ ጥቃት እንዳያደርሱ ጥሪ ያስተላለፉት ሚኒስትር ዴኤታው ሞሐመድ ሙሣ ዴሬ ለኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ጥበቃ እንዲያደርጉ ኃይሎቻቸውን ማዘዛቸውን አመልክተዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
  00:14             12:48  


እኛ በመላው አለም የምንገኝ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ተወላጆች ዛሬም እንደትላንቱ በአንድነት ከሕዝባችን ጎን በጽናት በመቆም የትግል አጋርነታችንንና አንድነታችንን እንገልጻለን

የአማራና የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንቶች ጠገዴ ላይ ያሳለፉትን ውሳኔ ልሳነ ግፉአንና የጠለምት አማራ ማንነት ኮሚቴ በጋራ እንደሚቃወሙት አስታወቁ


የአማራና የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንቶች ጠገዴ ወረዳ ላይ ያሳለፉትን ውሳኔ ልሳነ ግፉአንና የጠለምት አማራ ማንነት ኮሚቴ በጋራ እንደሚቃወሙት አስታወቁ።

ሕወሃትና ተላላኪው ብአዴን በአዲሱ አመት ዋዜማ ለመላው የጎንደር ህዝብ የሰጡት ስጦታ ቢኖር ሰላምና አንድነቱን ሳይሆን አካሉ የሆነውን የጠገዴ ማህበረሰብን ለሁለት እንደ ቅርጫ መቀራመትን ነው በማለት እርምጃውን በጽኑ አውግዘዋል።
ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ የወልቃይትን መሬት ከረገጠበት ጊዜ ጀምሮ ሕዝቡ እስራት፣ድብደባና ግድያ እንዲሁም ዝርፊያ ሲፈጸምበት መቆየቱን ልሳነ ግፉአን ከጠለምት አማራ ማንነት ጥምረት ጋር ባወጣው የጋራ መግለጫ በዝርዝር አስቀምጧል።
የወልቃይትን ሕዝብ ሙሉ ውክልና ይዘውና የሕዝብ ጥያቄን አንግበው በሰላማዊ መንገድ ፍትህ የጠየቁ የወልቃይት አማራ ማንነት ኮሚቴ አባላት በሽብርተኝነት ተወንጅለው በሕወሃት ማሰቃያ ካምፕ መከራ በመቀበል ላይ መሆናቸውንም አስታውቋል።
በሰላማዊ መንገድ ለቀረበው ጥያቄ በተሰጠው የሃይል አጸፋ የተቆጡ የጎንደር ልጆችም መብታቸውን ለማስከበር በመዋደቅ ላይ መሆናቸውን በመግለጫው ያስታወቀው ጥምር ኮሚቴው ጳጉሜ 1/2009 ሕወሃትና ብአዴን የተፈራረሙትንም ውሳኔ እንደማይቀበለው አስታውቋል።
እኛ በመላው አለም የምንገኝ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ተወላጆች ዛሬም እንደትላንቱ በአንድነት ከሕዝባችን ጎን በጽናት በመቆም የትግል አጋርነታችንንና አንድነታችንን እንገልጻለን ብለዋል።
ከጳጉሜ 1/2009 ጀምሮ በሕወሃትና በብአዴን መሪዎች አማካኝነት የታወጀው ጠገዴን ለሁለት መክፈል አንቀበልም በማለት በመግለጫው ላይ አስፍሯል።
የጎንደር አማራ ለምና ታሪካዊ የሆኑትን የግጨውና የጎቤ መንደሮችን ወደ ትግራይ መከለል ፍጹም ሰብአዊነት የጎደለውና አንድን ብሔረሰብ ለሁለት የሚከፍልና የሚለያይ ጭራቃዊ ተግባር በመሆኑ የምንጸየፈውና የምናወግዘው ነው ብሏል መግለጫው።
ልሳነ ግፉአንና የጠለምት የአማራ ማንነት ጥምረት በጋራ ባወጡት በዚህ መግለጫ በኦሮሚያ ክልልና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል እየተካሄደ ያለውን ደም አፋሳሽ ድርጊት በማውገዝ ሕወሃት ኦህዴድና ሶህዴፓን በመጠቀም ወንድማማቾችን እያፋጀ ነው ብሏል።

የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት ኤጀንሲ የኢትዮጵያው አገዛዝ ዜጎቹን እንዲሰልል የቴክኖሎጂ እገዛና ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተጋለጠ


(ኢሳት ዜና–መስከረም 4/2010)
የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት ኤጀንሲ የኢትዮጵያው አገዛዝ ዜጎቹን እንዲሰልል የቴክኖሎጂ እገዛና ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ኢንተርሴፕት የተባለ ተቋም አጋለጠ።
ብሔራዊ የደህንነት ኤጀንሲው በኢትዮጵያ የስለላ መረብ እንዲዘረጋ ትልቅ እገዛ ማድረጉን መረጃዎቹን ያሰባሰበው ይሄው ተቋም ገልጿል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየአመቱ የሀገራትን ሰብአዊ መብት አያያዝ በማስመልከት በሚያወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ዜጎቿን መሰለሏንና ማፈኗን ቢያወግዝም የዚሁ ድርጊት ተባባሪ መሆኑ ግን ትክክል አለመሆኑን ተቋሙ ተችቷል።
አሜሪካ የኢትዮጵያ ዜጎች እንዲሰለሉና እንዲታፈኑ በሚያስችለው የደህንነት ቴክኖሎጂ መረብ ዝርጋታ እጇ አለበት መባሉ ጉዳዩን ውስጡን ለቄስ አስብሎታል።
በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ረገጣ ትፈጽማለች በማለት የምታወግዘው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ በሌላ በኩል የጉዳዩ ተባባሪ ሆና መገኘቷ ብዙዎችን አስገርሟል።
ኢንተርሴፕት የተባለው ተቋም ሚስጥራዊ ሰንዶችን በመመርመር ይፋ እንዳደርገው የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት መስሪያ ቤት ኢትዮጵያ የዜጎቿን የስልክ ግንኙነትና ንግግሮችን የሚጠልፍ የቴክኖሎጂ መረብ እንድትዘረጋ ከፍተኛ የቴክኖሎጂና የስልጠና ድጋፍ አድርጓል።
በአንድ በኩል በልማትና በጤና እንዲሁም በሰብአዊ ጉዳይ ላይ ብቻ እርዳታ እሰጣለሁ እያለች የምትፎክረው አሜሪካ በሌላ ሁኔታ የኢትዮጵያውያን መብት እንዲጣስና እንዲታፈን በሚያደርግ ወንጀል ተባባሪ መሆኗ ትልቅ ችግር መሆኑን ኢንተርሴፕት ዘርዝሯል።
እንደ ተቋሙ ገለጻ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የስለላ መረብ መረጃ የቴክኖሎጂና የስልጠና አገልግሎት ስትሰጥ የቆየችው ሽብርተኝነትን ለመከላከል በሚል ሰበብ ነው።
ይህም ሆኖ ግን የኢትዮጵያ አገዛዝ ይህን ቴክኖሎጂ ለሰብአዊ መብት ረገጣና ለአፈና እየተጠቀመበት መሆኑን አሜሪካ እያወቀች ይህን ማድረጓ አግባብነት የለውም ብሏል።
ኢትዮጵያ የተቃዋሚ መሪዎችንና ጋዜጠኞችን በማሳደድና በማሰር እንዲሁም ዜጎችን በመግደል ወንጀል እየፈጸመችበት መሆኑንም ኢንተርሰፕት የተባለው ተቋም ገልጿል።
አሜሪካ ለኢትዮጵያ መንግስት የስለላ መረብ የሰጠችው የቴክኖሎጂ መረብ የአንበሳው ኩራት ወይም ላየንስ ፕራይድ የተሰኘ ነው።
ይህም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2002 በትንሽ የሰው ሃይል ጀምሮ በ2005 ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደገ ነው ተብሏል።
በዚህ ፕሮጀክት 8 አሜሪካውያንና 103 ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል ተብሏል።
ፕሮጀክቶቹም በአዲስ አበባ፣በድሬደዋና በጎንደር ከተሞች የተዘረጉ መሆናቸው ነው የተገለጸው።
በእነዚህ ፕሮጀክቶችም 7 ሺ 700 ሰንዶችና 900 ሪፖርቶች ከስለላ ስራው በኋላ የተዘጋጁ መሆናቸውን ኢንተርሴፕት አጋልጧል።

Friday, September 15, 2017

በመታወቂያቸው በሰፈረ የብሄር ማንነት እየተለዩ የሚገደሉ፣ የሚታሰሩ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር እየጨመረ መቷል።

በኦሮሞና ሶማሌ ወሰኖች ላይ የተጀመረው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ተገለጸ

 በኦሮሞና ሶማሌ ወሰኖች ላይ የተጀመረው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ተገለጸ።
በሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች ከሶማሌ ክልል የተለያዩ ከተሞች ተፈናቅለው ወደ ሀረር መግባታቸው ታውቋል። ሁለቱ ክልሎች እየተወዛገቡ ነው።
ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ሰዎች ተገድለዋል። ግጭቱ ወደ አጠቃልይ ቀውስ ሊያመራ እንደሚችል እየተነገረ ነው።
የሃይማኖት አባቶች ጥሪ አስተላልፈዋል። ይህ ግጭት በአገዛዙና በህዝብ መካከል ብቻ መሆኑን በሶማሌ እና ኦሮሚያ አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኢሳት በኩል መልዕክት እንዲደርስላቸው ጠይቀዋል።
የሁለቱ ክልሎች መንግስታት እየተወነጃጀሉ ነው። ሁለቱም ወገኖች በየፊናቸው የሚያሰራጯቸው መልዕክቶች ግጭቱን ከማብረድ ይልቅ እንዲባባስ ምክንያት መሆኑም እየተነገረ ነው።
ይሄን ያህል ዜጎች ሲገደሉና ከሚኖሩበት ተባረው ሲወጡ በዝምታ እየተመለከተ ያለው የህወሃት መንግስት ለ26 አመታት የተከተለው የዘር ፖለቲካ ውጤት ነው የሚለው ድምዳሜ በብዙ ወገኖች ዘንድ እየተሰጠ ነው።
ለኢሳት የሚደረሱ መረጃዎች አሰቃቂ በመሆናቸው ለህዝብ ደህንነት ሲባል እንዳይተላለፉ መደረጋቸው ተገልጿል።
ባለፉት ሶስት ቀናት ከሶማሌ ክልል የተለያዩ ከተሞች በተለይም ከጂጂጋና ውጫሌ በመታወቂያቸው በሰፈረ የብሄር ማንነት እየተለዩ የሚገደሉ፣ የሚታሰሩ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር እየጨመረ መቷል።
ይህን በመስጋት ቤት ንብረታቸውን ትተው የተሰደዱ የኦሮሞ ተወላጆች ወደ አቅራቢያ የኦሮሚያ መንደሮች እየገቡ ሲሆን በሀረር ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ መድረሳቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ለኢሳት ዛሬ በደረሰው መረጃ በሺ ዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች ከጅጅጋ በመውጣት ላይ ናቸው።
እስከ 12 ሺ የሚሆኑት ከሶማሌ ክልል እንደሚፈናቀሉ አንድ ባለስልጣን ለዘጋቢያችን ገልጸዋል።
ተፈናቃዮቹ በሽሽት ላይ እያሉ በመንገድ ላይ ግጭት ተከስቷል ተብሏል። ስለደረሰው ጉዳት ግን ዝርዝር መረጃ እየጠበቅን ነው።
ጥቃቱን እየፈጸሙ ያሉት የሶማሌ ልዩ ሃይል አባላት መሆናቸውን ተፈናቃዮች ይናገራሉ።
በሶማሌ ተወላጆች በኩልም ግድያና መፈናቀል እንደደረሰባቸው የሚገለጹ መረጃዎች በመውጣት ላይ ናቸው።
የኦሮሚያ ክልል የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ባወጣው መግለጫ በሶማሌ ልዩ ሃይል የጭካኔ እርምጃ የተቆጡ የኦሮሞ ተወላጆች ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ግጭት ተፈጥሮ 18 ሰዎች መገደላቸውን አስታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ 12ቱ የሶማሌ ተወላጆች መሆናቸው ተገልጿል።
ዛሬ በሃረር ተቃውሞ መካሄዱ ተሰምቷል። ሸዋ በር እና ፈረስ መጋላ አካባቢ የአጋዚ ወታደሮች አንድ ሰው መግደላቸው የተገለጸ ሲሆን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ውጥረት መንገሱን ነው መረጃዎች የሚያመለክቱት።
በድሬደዋም እንዲሁ ግጭት እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን ስለደረሰው ጉዳት ግን የታወቀ ነገር የለም።
ሶማሌላንድ በተባለችው ሀገር የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ጥቃት በመፈጸም ላይ መሆኑን ዘግይቶ የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ የኦሮሞ ተወላጆች በሶማሌላንድ መገደላቸውንም ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
በሌላ በኩል ለኢሳት በስልክ፣ በኢሜይና በፌስቡክ ከሀገር ቤት በተለይም በሶማሌና ኦሮሚያ ክልል ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን በርካታ መልዕክቶች እየደረሱ ሲሆን ህዝቡ ከማንኛውም የእርስ በእርስ ግጭት ራሱን እንዲጠብቅና እንዲከላከል የሚጠይቁ ናቸው።
ይህ የህወሀት መንግስት ከህዝብ ጋር የገባበት ግጭት እንጂ በኢትዮጵያውያን መሀል የተፈጠረ አይደለም የሚለው መልዕክት በሁለቱም ክልሎች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተላለፉ ናቸው።

Thursday, September 14, 2017

Ethiopians irate over cancellation of pop star’s album release party



Ethiopians took to the social media to express their anger over the cancellation Sunday of Teddy Afro’s album release party by authorities who have also banned his new year concert.
Lyrics by Ethiopia’s king of reggae preaching unity and peaceful coexistence do not bode well for the ominous agenda of the ethnocentric regime that divide and rule the people with iron fist.
It was not the first time that the pop star’s concerts were cancelled. Several of Teddy’s concerts were banned, some in the last minutes, resulting in thousands of dollars loss to the singer.
Security forces on Sunday prevented the unloading of sound systems and band instruments from a truck parked at the Addis Ababa Hilton Hotel and told organizers of the party that the event had been banned by authorities.
Hundreds of invited guests were on their way to the dinner party that would have seen the video release of one of his songs from the most recent album that charted number one on Billboard’s World Albums.
His fans found the ban not only unfair to the artist but also ironical in that it came at a time when the regime has organized a ten day celebration of “Ethiopianism” in connection with the Ethiopian new year on September 11.
“Ethiopians want to celebrate #EthioNewYear Not with Chris Brown or Bruno Mars BUT #Teddy_Afro,” wrote Jordan Wmariam on his Facebook.
“Most of all I wish the new year to be a year that Ethiopians are equal under the law and for justice to prevail in the new year,” Teddy wrote
in a message posted on his Facebook after the cancellation of his party.

Tuesday, September 12, 2017

በፍሎሪዳ ኢርማ አውሎ ንፋስ 25 በመቶ የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶችን ከጥቅም ውጪ ማድረጉ ተሰማ

በአሜሪካ የፍሎሪዳ ግዛትን የመታው ኢርማ አውሎ ንፋስ 25 በመቶ የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶችን ከጥቅም ውጪ ማድረጉ ተሰማ።

የሀገሪቱ የፌደራል የአስቸኳይ ጊዜ መስሪያ ቤት 65 በመቶ የሚሆኑት መኖሪያ ቤቶችም ከባድ በሚባል ሁኔታ መጎዳታቸውን አስታውቋል።
60 በመቶ የሚሆኑ ነዋሪዎች እስካሁን ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጪ ሆነው በጨለማ እንደተዋጡ ናቸው ይላል ቢቢሲ በዘገባው።
በፍሎሪዳ ከአውሎ ንፋሱ ጋር በተያያዘ 6 ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውም ታውቋል።
አሁን ላይ ፍጥነቱን በሰአት ወደ 95 ማይልስ በመቀነስ ጉዞውን ወደ ደቡብ ደቡብ ምእራብ አትላንታ ጆርጂያ ያደረገው ኢርማ አውሎ ንፋስ ወደ አልባማ ብሎም ወደ ምዕራብ ቴንሴ ሊያቀና እንደሚችል ሲ ኤን ኤን በዘገባው አስፍሯል።

Wednesday, August 16, 2017

Ethiopia: Court denies bail to Bekele Gerba


ESAT News (August 10, 2017)
The 4th criminal bench of the federal high court in Addis Ababa on Thursday denied bail to a prominent Ethiopian opposition leader while the 2nd bench gave additional time to police investigating the cases of individuals accused of corruption.
Bekele Gerba, first secretary general of the Oromo Federalist Congress was initially accused of terrorism but the charges were later reduced to criminal offences. As soon as the charges were reduced, Gerba’s lawyers requested bail for their client. The court in today’s session rejected the request saying Gerba “could incite violence” if released. Gerba, among other charges, was accused of igniting the unrest in the Oromo region last year.
Gerba responded to the court saying he expected no justice from the court and that he was not surprised at all. Gerba said that was not the first time an Ethiopian court made such a decision.
Bekele Gerba a linguist who taught at the Addis Ababa University for nearly three decades is also a vocal opposition figure in Ethiopia. Gerba had previously served 4 years on trumped up charges of terrorism. No sooner had he been released upon serving his four years sentence than he was arrested again in December 2016.
Meanwhile the 2nd bench of the court gave police additional 14 days in the case 16 individuals recently detained on suspicion of high level corruption. The individuals, including the former bosses of the Addis Ababa Roads Authority, were arrested a week ago as part of the crackdown against corruption by the regime. Critics say the campaign has left untouched high level officials who are accused of squandering billions of dollars.

Saturday, October 8, 2016

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የእሬቻውን ጭፍጨፋ አስታከው የሽግግር መንግስቱ እቅድ ይፋ አደረጉ


ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የእሬቻውን ጭፍጨፋ አስታከው የሽግግር መንግስቱ እቅድ ይፋ አደረጉ | ሙሉ ንግግራቸውን ይዘነዋል

የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትውልድ ቦታቸው ቢሾፍቱ የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት የፈጸመውን ግድያ አውግዘው በሽግግር መንግስቱ እቅድ ዙሪያ ተናገሩ:: ሙሉ መል ዕክታቸው ከአስመራ ደርሶናል ያድምጡት::

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የ እሬቻውን ጭፍጨፋ አስታከው የሽግግር መንግስቱ እቅድ ይፋ አደረጉ | ሙሉ ንግግራቸውን ይዘነዋል





Friday, August 5, 2016

ሰበር ዜና ጎንደር ተቃውሞ ተነስቷል። ከፍተኛው ፍርድ ቤት በህዝብ ተጥለቅልቋል



ጎንደር የጦርነት ቀጠና ሆናለች ። ‪#‎Amharaprotests‬ ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Gonder‬

አንዳንድ ታጣቂ ገበሬዎች እና የታጠቀው የከተማ ኗሪ ከሕወሓት ጦር ጋር እዬተፋለሙ ነው። አጠቃላይ የጎንደር ዞን ታጣቂ ገበሬዎች በአጭር ጊዜ ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል። ህዝቡ ፒያሳ አካባቢ የወያኔን ባንዲራ በማውረድ የአባቶቹን ሰንደቅ አላማ እየሰቀለ ይገኛል ።


ጎንደር ከተማ ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ውጭ ሆናለች
• የትግራይ ልዩ ኃይል አርማጭሆ ወደ አርማጭሆ ሒዶ ዐማሮችን ሊበቀል እንደሚችል ተጠቁሟል
• ሁለት የትግራይ ሠላዮች አርማጭሆ አካባቢ ባልታወቀ ምክንያት ተገድለው ተገኝተዋል

ዛሬ ማለዳውን የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን የፍርድ ሒደት ለመከታተል በመጡ ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወያኔ ሠራዊት ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ የዐማራ ገበሬዎች የአጸፋ መልስ ሰጥተዋል፡፡ በአጋዚ ጦር እስካሁን የሁለት ዐማሮች ሕይወት ማለፉን ለማወቅ የታቻለ ሲሆን አንድ የትግሬ መከላከያ ተገድሏል፤ በርካታ የፌደራል ፖሊሶችም ቆስለዋል፡፡

የትግሬው መንግሥት የወልቃይት ጠገዴ የዐማራ ማንነትን ለማፈን በመፈለጉ መላውን የዐማራ ሕዝብ በቁጣ አነሳስቷል፡፡ ዛሬ ሐምሌ 29 ቀን 2008 ዓ.ም. መለው የጎንደር ከተማ ከወያኔ ቁጥጥር ውጭ ሆኗል፡፡ ከአዘዞ እስከ ሸንበቂት ድረስ ያሉ ሁሉም የጎንደር ከተማ መንገዶች ሞት በማይፈሩ ወጣቶችና የታጠቁ ገበሬዎች ተሞልቷል፡፡ የትግሬ መከላከያ ከጭልጋና እና ከባሕር ዳር እንዳይመጣ መንገዶች ሁሉ ተዘግተዋል፡፡

ከኹመራ፣ ዳንሻሻ ሶሮቃ፣ አብደራፊ፣ ሳንጃ፣ ትክል ድንጋይ፣ አሽሬ፣ ዳባትና ደባርቅ፣ ከበለሳ፣ አዲስ ዘመን፣ ጋይንት፣ ፋርጣና ፎገራ፣ ከደንቢያ፣ ከጯሒት፣ አቸፈር፣ ዳንጋላና ዱር ቤቴ፣ … በቅርብ የሚገኘው የዐማራ ታጣቂ ገበሬ ሁሉ ወደ ጎንደር በመሔድ ከወንድሞቹ ጋር እንዲዋደቅ ተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበ ነው፡፡ የትግሬ መንግሥት ይህን ተከትሎ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሊያቋርጥ ይችላል እየተባለ ነው፡፡
አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና የትግራይ ልዩ ኃይል ፖሊስ በዳንሻ ከተማ ዐማሮችን ማስፈራራት የቀጠለ ሲሆን አርማጭሆ በመሔድ ዐማሮች ላይ የበቀል እርምጃ እወስዳለሁ ማለቱ ከዳንሻ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሁለት የትግራይ ሠላዮች ጎንደር ከተማ ሰንብተው ሲመለሱ አርማጭሆ ሲደርሱ ባልታወቀ ምክንያት ተገድለው መገኘታቸው ወያኔን አናዷል፡፡

wanted officials