Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Showing posts with label #zeabraham. Show all posts
Showing posts with label #zeabraham. Show all posts

Wednesday, May 16, 2018

ጠቅ/ሚኒስትሩ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሀገር ቤቱ የውጩ ቅዱስ ሲኖዶስ ዕርቀ ሰላሙ ሥምረት ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ

በግላቸውም ኾነ በመንግሥት ደረጃ፣ለዕርቀ ሰላሙ ሥምረት ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ

አንዲትና ታላቅነቷ የተጠበቀ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የማየት ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ
“ለአንድነት ታሪካዊ ሚና ያላት ተቋም፣ራሷ መከፋፈሏ ለብሔራዊ ተግባቦቱ ተግዳሮት ነው፤”
“ልዩነቱ ምንም ቢኾን የማይፈታ አይደለም፤ችግር ፈቺዎቹ ከተቸገሩ ትልቁ ችግር እርሱ ነው፤”
“በጥረታችሁ ግፉበት፤ ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ ነን፤ልዩነቱን ሥበሩና ለኛም አርኣያ ኹኑን፤”
“የልኡካን አባቶችን ስጋት የሚያስወግድና የሰላም ኮሚቴውን የሚያበረታታ ነው፤”/ታዛቢዎች/

†††
በውጭ ሀገር በስደት በሚኖሩት አባቶች ከተቋቋመው ሲኖዶስ ጋራ ለተጀመረው የዕርቀ ሰላም ጥረት መሳካት፣ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ኹሉ እንደሚሰጥ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ትላንት ቅዳሜ፣ ግንቦት 4 ቀን 2010 ዓ.ም. ረፋድ፣ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባደረጉላቸው ጥሪ መሠረት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሯቸው ሲኾን፤ ቅዱስነታቸውና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ አንድነት ለማስጠበቅ በጀመሩት የዕርቀ ሰላም ጥረት እንዲገፉበት አሳስበዋል፤ለሥምረቱም መንግሥታቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡
ለሀገራችን ኢትዮጵያ አንድነት መጠበቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላት ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ በሲኖዶሳዊ አስተዳደሯ መከፋፈሏ በግላቸውም ቢኾን እንደሚያሳዝናቸው ያልሸሸጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ አንዲትና ታላቅነቷ የተጠበቀ የተጠናከረች ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ማየት ፍላጎታቸው እንደኾነ ለቅዱስነታቸው ገልጸውላቸዋል፡፡
በሀገራችን ለግጭት መንሥኤ የኾኑ ልዩነቶችን በጋራ ለመፍታት እየተደረገ ባለው ጥረት፣ ለሀገራዊ አንድነት መጠበቅ ታሪካዊ ሚና ያላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ራሷ በማዕከላዊ አስተዳደሯ ለሁለት መከፈሏ፣ ለብሔራዊ ተግባቦቱ ትልቅ ተግዳሮት በመኾኑ በተጀመረው የአባቶች ዕርቀ ሰላም ጥረት መፍትሔ ሊሰጠው እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
“ልዩነቶቹ በተለያየ ምክንያት ተከሥተው ሊኾን ይችላል፤ ነገር ግን ለመፍታት የማይቻሉ አይመስለኝም፤ ይቻላል፤ ሃይማኖታዊ ሰው ደግሞ አይደለም የውስጡንና የራሱን፣ የሌሎችንም ችግር መፍታት አይሳነውም ተብሎ ነው የሚታመነው፤” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አያይዘውም፣“የሌሎችን ችግር ይፈታሉ የተባሉት ችግር ፈቺዎቹ ራሳቸው ከተቸገሩና ሌላ ችግር ፈቺ ካስፈለጋቸው ትልቁ ችግር የሚኾነው እርሱ ነው፤” በማለት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ልዩነቷን ለማስወገድ በያዘችው ጥረት እንድትቀጥልበት አበረታታዋል – “እንደ ግልም እንደ መንግሥትም ከእኛ የሚፈለገውን ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ ነን፤ እናንተ ግን ግፉበት፤ ይህን ልዩነት በመሥበር ለእኛም አርኣያ ኹኑን፤”ብለዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በበኩላቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ስለ ማበረታቻ ሐሳባቸውና አቋማቸው በማድነቅና በማመስገን፣ በውጭ ከሚኖሩት አባቶች ጋራ የተጀመረው ዕርቀ ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዜው ስላደረጋቸው ጥረቶች አብራርተውላቸዋል፤ በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ባጠናቀቀው የግንቦቱ ርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤውም፣በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቋቋመው የሰላምና አንድነት ኮሚቴ፣ ከቀድሞው በተሻለ አያያዝ ሒደቱን ለማስቀጠል ላቀረበው ጥያቄ ይኹንታውን በመስጠት የሚነጋገሩ ልኡካን አባቶች መሠየሙንም ነግረዋቸዋል፡፡
ትላንት ማምሻውን፣ ከአማራ ክልል የመጡና የባሕር ዳር ልዩ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃምን ጨምሮ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት፣ በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ባደረጉት የራት ግብዣ ላይም፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልእክት፤ ለሀገር አንድነት ለመሥራት የሃይማኖት ተቋማት ውስጣዊ አንድነት ወሳኝ መኾኑን በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡ መድኃኒቱ ራሱ ሲበከል መጥፎ በመኾኑ፣ ውስጣዊ ችግራቸውን በራሳቸው በመፍታት ለሀገራዊ ተግባቦት መጠናከር የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ለማበርከት በጋራ እንዲሰለፉ አሳስበዋል፡፡
ስለጉዳዩ የተጠየቁ አስተያየት ሰጭዎች፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከቤተ ክርስቲያን ታሪካዊ አስተዋፅኦ በመነሣት ለሲኖዶሳዊ አንድነቷ መጠበቅ ያሳዩት መቆርቆር እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል፤ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን ወደ ጽ/ቤታቸው በመጥራት ማበረታታቸውም፣ ቢያንስ ሦስት ፋይዳዎች እንዳሉት አመልክተዋል፡፡ በመንግሥት እያመካኙ ወይም መንግሥት እንዲህ ሊያስብ ይችላል፤ እያሉ ወደ ኋላ የሚሉትንና በዕርቀ ሰላሙ ሒደት ላይ ሻጥር የሚፈጥሩትን የሀገር ቤት አካላት ያስታግሣል፤ የሚለው የመጀመሪያው ነው፤ በውጭ ባሉትም ዘንድ፣ “ዕርቀ ሰላሙን መንግሥት አይፈልገውም፤” የሚለውን ስጋታቸውን ያስወግዳል፤ ከዚህም ጋራ ተያይዞ፣ የዕርቀ ሰላም ሒደቱን በተሻለ አያያዝ ለማስቀጠልና ከዳር ለማድረስ ተነሣሽነቱን ለወሰዱ ሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የሰላምና አንድነት ኮሚቴ አባላት ጉልበት ይኾናቸዋል፡፡
የሀገር ቤቱ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሚያዝያ 26 ቀን 2010 ዓ.ም. ባካሔደው የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤ ስብሰባው፥ ለዕርቀ ሰላሙ እንዲነጋገሩ፣ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሚመሩ ሦስት አባቶችን የሠየመ ሲኾን፤ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የሚመራው የውጩ ሲኖዶስም፣ ከጥቅምት 22 እስከ 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በኮለምበስ ኦሃዮ ባደረገው ጉባኤ፣ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ ሊቀ ጳጳስ የሚመራ ሦስት አባላት ያሉት ተደራዳሪ ልኡክ ሠይሟል፤ “እግዚአብሔር ይጨመርበት፤ አምላከ አበው ሥራችሁን የተቃና ያድርግላችሁ፤” ሲልም ለሰላምና አንድነት ኮሚቴውቡራኬውን ሰጥቷል፡፡ በተለያዩ ሀገራት ቅርንጫፎችን በማቋቋም የሚንቀሳቀሰው፣ሁለተኛው ዙር የሰላምና አንድነት ዓለም አቀፍ ኮሚቴ፣ ልኡካን አባቶች የሚገናኙበትንና ድርድሩ የሚካሔድበትን ቦታና ጊዜ በቅርቡ ለኹለቱም ወገኖች እንደሚያሳውቅ መግለጹን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
Source: ሐራ ዘተዋሕዶ

Friday, October 20, 2017

የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ በተፈጠረበት የቴክኒክ ችግር ምክንያት መራዘሙ ታወቀ


 የዛሬ ሁለት ሳምንት የተጀመረው የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ በተፈጠረበት የቴክኒክ ችግር ምክንያት መራዘሙ ታወቀ።
ባለፉት 13 ቀናት ያመለከቱ አመልካቾች የቀደመው ውድቅ በመሆኑ እንደገና ማመልከት እንዳለባቸውም በየሀገሩ ባሉ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከጥቅምት 3/2017 እስከ ህዳር 7/2017 መርሃ ግብር የተያዘለት የ2019 የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ በኮምፒዩተር ስርአቱ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ላለፉት 13 ቀናት የገቡት ማመልከቻዎች ውድቅ ሆነዋል።
አንድ ሰው ከአንድ ግዜ በላይ ማመልከቻ ካቀረበ ወዲያውኑ ከውድድሩ ውጭ እንደሚሆን የታወቀ ቢሆንም ባለፉት 13 ቀናት ማመልከቻ ያቀረቡት ግን በድጋሚ ማመልከት እንደሚችሉ ተመልክቷል።
በአዲሱ መመሪያ መሰረት የዲቪ ማመልከቻው ከፊታችን ረቡዕ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከጥቅምት 18/2017 ተጀምሮ እስከ ህዳር 22/2017 እንደሚቀጥልም ታውቋል።
የቀድሞው ቀነ ገደብ ህዳር 7 እንደነበር ይታወሳል።
(ኢሳት ዜና–ጥቅምት 6/2010)

Saturday, September 23, 2017

በመንገድ ግንባታና ስርጭት ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ግንባር ቀደም ሆና የተገኘችው ትግራይ ናት ተባለ


 በኢትዮጵያ ባለፉት 10 አመታት በመንገድ ግንባታና ስርጭት ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ግንባር ቀደም ሆና የተገኘችው ትግራይ መሆኗን የአለም ባንክ ጥናት አመለከተ።
አማራ ክልል ደግሞ የመጨረሻ ሆኖ ተመዝግቧል።
ለመንገድና ለልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች በስልጣን ላይ ላለው የኢትዮጵያ መንግስት በብድርና በስጦታ ገንዘብ በማቅረብ የሚታወቀው የአለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 10 አመታት የተካሄዱ የመንገድ ግንባታዎችን የገመገመበትን ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
አዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከፍተኛ የመንገድ ስርጭት የታየባቸው ሲሆኑ ክክልሎች ደግሞ የትግራይ ክልል ከፍተኛ የመንገድ ስርጭት ተመዝግቦበታል።
እንደ አውሮፓውያኑ ከ2006 እስከ 2016 ከክልሎች የመንገድ ስርጭት የመጨረሻ ሆኖ የተመዘገበው የአማራ ክልል እንደሆነም ታውቋል።
በአጠቃላይ በሀገሪቱ ገጠሮች የመንገድ ስርጭት ደካማ እንደሆነም ተመልክቷል።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገቱ መቀጠሉን የሚናገረው የአለም ባንክ እድገቱ በዋናነት በግብርናና በአገልግሎት መስክ መሆኑን ያብራራል።
ሆኖም የድሃና ሃብታሙ ርቀት እንደሰፋ መቀጠሉን በድህነት ደረጃ ላይ ያሉ ዜጎች ቁጥር ይበልጥ እያሻቀበ መሄዱንም በሪፖርቱ አስፍሯል።
ከእድገቱ ጋር ተያይዞ መታየት የነበረበት የከተሞች መስፋፋትና እድገት ብዙም ልዩነት እንዳልታየበት በምሽት በሳተላይት የተነሱ ፎቶግራፎችን በአስረጅነት ያስቀምጣል።
በዚህም ከኢትዮጵያ ከተሞች መቀሌ በብርሃን ድምቀትም ሆነ የብርሃን ስፋቱ በመጨመር ቀዳሚ ሆና ስትመዘገብ ጎንደር የመጨረሻ ሆና ተመዝግባለች።
በቀድሞ መንግስት ከአዲስ አበባና አስመራ ቀጥላ በሶስተኛ ከተማነት ትጠቀስ የነበረችው ድሬደዋ ከመቀሌ በእጅጉ ዝቅ ብላ ተገኝታለች።

Wednesday, September 20, 2017

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ያለስምምነት ተበተነ

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ያለስምምነት ተበተነ

(ኢሳት ምንጮች–መስከረም 12/2010)
የብሔረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ብአዴን/ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ያለስምምነት መበተኑን ምንጮች ገለጹ።
በስልጣን ላይ ለ2 አመታት የቆየው የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አዲስ ምርጫ ማካሄድ ይጠበቅበት ነበር::የሚባረሩ እንዳሉም ይነገራል።
የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በግጨው የስምምነት ጉዳይና በቅማንት ሕዝበ ውሳኔ ውጤት መነታረካቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል።
የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በስምምነት የተጠናቀቀ ለማስመሰል የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ደመቀ መኮንን የውይይቱን መጠናቀቅ ተከትሎ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
አቶ ደመቀ ግን በአባላቱ የነበሩትን ልዩነቶችና ስምምነት ያልተደረሰባቸውን ጉዳዮች ይፋ አላደረጉም።
ጥልቅ ተሀድሶው የታሰበለትን አላማ በተሟላ መንገድ እንዳላሳካ ግን ለመናገር ተገደዋል።
በተለይም የህዝብ ጥያቄዎችን የመመለስ ተግባር ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በከፊል መካሄዱን ነው የገለጹት።
በተለይም የግጭት መንስኤ የሆኑ የወልቃይትና የግጨው እንዲሁም የቅማንት ጉዳዮች ግን ለማእከላዊ ኮሚቴው መጨቃጨቅና ስምምነት ላይ አለመድረስ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የወልቃይት ጉዳይ ሳይፈታ የግጨው ጉዳይ ለምን ቅድሚያ ተሰጠው፣የቅማንት ማንነት ጥያቄ ከብአዴን ይልቅ ከበስተኋላው የሚገፋው አካል አለ የሚሉት ጉዳዮች እንዳላግባቧቸው ታውቋል።
በማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱ ከባድ መካረርና ውዝግብ የፈጠረው ግን ከብአዴን ካድሬዎች እንዲታሰሩና ከግጭቶች ጋር በተያያዘ በሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተጠያቂ ይደርጋሉ በተባሉ ሰዎች ዙሪያ ልዩነት መፍጠራቸው ነው።
እንደ ምንጮች ገለጻ ግዛት አብየ፣ ደሴ አሰሜና አገኘሁ ተሻገር ከሰሜን ጎንደር ችግር ጋር በተያያዘ በተጠያቂነት እንዲታሰሩ በሕወሃት በኩል ፍላጎት አለ።
በአማራ ህዝባዊ አመጽ ጊዜ የልዩ ሃይል አዛዥ የነበሩ ግለሰብና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ ወርቁን ከስልጣን ለማንሳት በተደረገው ግምገማም ስምምነት አልተደረሰም ተብሏል።
እናም የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ለክልሉ ምክር ቤት በሚቀርቡ አጀንዳዎች ላይ የተሟላ መግባባት እንደሌላቸው ነው የተገለጸው።
የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ለክልሉ በሚቀርቡ አጀንዳዎች ላይ የተሟላ መግባባት እንደሌላቸው ነው የተገለጸው።
የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የ2 አመት የስልጣን ጊዜው የተጠናቀቀ ቢሆንም ምርጫ አላካሄደም።
በመጪዎቹ ስብሰባዎች ግን ከስልጣን የሚወርዱና የሚወጡ የብአዴን ካድሬዎች እንደሚኖሩ ይጠበቃል።
የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በግጨው ጉዳይ ላይ ሕወሃት በፈለገው መንገድ ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ በሕዝብ ዘንድ በመጠላታቸው አሁን ቢወርዱ ችግር የለውም በሚል በሕወሃት ባለስልጣናት ዘንድ ምክክር እየተደረገ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ይገልጻሉ።
 

Monday, September 18, 2017

አንድ የእስራኤል ኩባንያ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ክስ መሰረተ


 አንድ በኢትዮጵያ በማእድን አሰሳ ላይ የነበረ አንድ የእስራኤል ኩባንያ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ክስ መሰረተ።Bildergebnis für አንድ በኢትዮጵያ በማእድን አሰሳ ላይ የነበረ አንድ የእስራኤል ኩባንያ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ክስ መሰረተ
ዘሔግ ኔዘርላንድ በተመሰረተው በዚህ ክስ አይ ሲ ኤል የተባለው የእስራኤል ኩባንያ ከኢትዮጵያ መንግስት የ198 ሚሊየን ዶላር ካሳ መጠየቁም ተመልክቷል።
የእስራኤሉ ኩባንያ አይ ሲ ኤል በኢትዮጵያ መንግስት ላይ በኔዘርላንድ ዘሔግ ክሱን የመሰረተው ስምምነቱ የተካሄደው በኔዘርላንድ በመሆኑ እንደሆነም አስታውቋል።
በኢትዮጵያና በኔዘርላንድ መካከል የተፈረመውን የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ከለላ ስምምነት የጣሰ ድርጊት እንደሆነም አክሏል።
አላና ፖታሽ የሚባል የካናዳ ኩባንያ በኢትዮጵያ የአፋር ክልል የጀመረው የፖታሽ ማእድን አሰሳ በመሳካቱ ለ5 አመታት የ3 ነጥብ 2 ቢሊየን ቶን የፖታሽ ማዕድን ክምችት መኖሩን አረጋግጦ የማዕድን ልማቱን ለማከናወን እንደ አውሮፓውያኑ በ2013 ስምምነት መፈራረሙን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።
ሆኖም ይህ ኩባንያ ማዕድን ለማልማት የሚያስችለውን የ700 ሚሊየን ዶላር ገንዘብ ማቅረብ ባለመቻሉ አይ ሲ ኤል የተባለው የእስራኤል ኩባንያ ስራውን መረከቡን ከዘገባው መረዳት ተችሏል።
ይህንን የ3 ነጥብ 2 ቢሊየን ቶን ፖታሺየም ማእድን ስራ ላይ ለማዋል በኔዘርላንድ ዘሔግ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት የፈረመውና በ150 ሚሊየን ዶላር ግዢውን የፈጸመው የእስራኤሉ ኩባንያ አይ ሲ ኤል በኢትዮጵያ መንግስት ደረሰብኝ ባለው ጫና በጥቅምት ወር 2009 ስራውን አቋርጦ ከኢትዮጵያ መውጣቱ ተመልክቷል።
የፖታሽ ማዕድን ማውጫና የማዳበሪያ ፋብሪካዎችን በ3 ቢሊየን ዶላር በመገንባት ስራውን በስፋት ለማካሄድ በመንቀሳቀስ ላይ ሳለ መንግስት ሕገ ወጥ ግብር እንድከፍል ጠይቆኛል በቂ መሰረተ ልማትም ለመዘርጋት አልቻለም በሚል ውሉን አቋርጧል።
በዚህም ለደረሰበት ኪሳራ የ198 ሚሊየን ዶላር ካሳ እንዲከፈለው ዘሄግ ኔዘርላንድ ላይ ክስ መመስረቱ ታውቋል።

Sunday, September 17, 2017

Israeli chemical company files a 198M suit at The Hague against Ethiopian gov’t


ESAT News
Israel Chemicals (ICL) files a 198M dollars compensation suit against the Ethiopian government for losses it incurred due to the latter’s “failure to provide the necessary infrastructures and regulatory framework.”
ICL ended its potash project in Ethiopia in October 2016 after the Ethiopian government assessed what ICL called “unjustified and illegal tax assessment.”
A local newspaper in Addis Ababa reported quoting its sources that the Israeli company has taken the case to the International Court of Arbitration at The Hague, Netherlands.
A five year exploration in Afar region of Ethiopia by the chemical company found 3.2 billion tons of potash and an agreement was signed with the Ethiopian government in 2013.
ICL took over the potash development project in Afar from Allana Potash in 2015, and used Allana’s name for a while till Revenue Authorities levied a 50 million dollar tax. ICL refused to pay the taxes saying it was “unjustified and illegal tax assessment.” The company claims it lost millions of dollars.
Tax authorities say they have tried to settle the matter with ICL outside the court but the company has refused their plea.

Friday, September 15, 2017

Ethiopia: TPLF annex areas in Amhara region to Tigray


ESAT News 
A former land administrator in the Amhara region says the recent pact signed between the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) and the Amhara National Democratic Movement (ANDM) has illegally transferred several villages to the Tigray region.
The land administration expert who wish to remain anonymous told ESAT that two areas – Gichew and Gobe – that were historically Amhara were given to Tigray against the will of the people. He said the TPLF regime had illegally annexed the Wolkait and Tegede and other agriculturally fertile regions to Tigray and the recent pact gave more areas to the Tigray region against the will of the Amhara people.
The expert recalled a referendum ten years ago in Gichew that was monitored by the House of the Federation in which the people voted to remain in the Amhara region. The expert said the result of that referendum has never seen the light of day.
The former land administrator told ESAT that the TPLF had settled thousands of people from Tigray into the Amhara territory in the last two decades to deliberately change the demographics of the region.
The Wolkait and Tegede regions that were forcefully annexed to Tigray was the cause of the protest last summer in Gondar and Bahir Dar where TPLF forces killed at least two hundred in the two northern cities.

አሪክ የተባለው የናይጄሪያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከሰሰ

Bildergebnis für አሪክ የተባለው የናይጄሪያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከሰሰ

 አሪክ የተባለው የናይጄሪያ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተሳሳተ መግለጫ ደርሰብኝ ላለው ጉዳት 56 ሚሊየን ዶላር ይከፈለኝ ሲል በፍርድ ቤት ክስ አቀረበ።
አየር መንገዱ ለናይጄሪያ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ባቀረበው የጉዳት ካሳ ክስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣የናይጄሪያ ትራንስፖርት ሚኒስቴርና የናይጄሪያ አቃቢ ህግ ተጠያቂ እንደሆኑ አመልክቷል።
20 አንቀጾች ባለው የክስ አቤቱታ የኢትዮጵያ አየር መንገድና የፌዴራሉ የናይጄሪያ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የአሪክ አየር መንገድ አስተዳደርን ለመውሰድ ጀመርን ያሉትን ድርድር ፍርድ ቤቱ እንዲያስቆምም ተጠይቋል።
በአሪክ አየር መንገድ የቀረበው ክስ እንዳመለከተው አምኮን የተባለ ድርጅት ቀደም ሲል የተቋሙን አስተዳደር እንዲወስድ በመደረጉ ይህንኑ በመቃወም ሁለት የፍርድ ቤት አቤቱታዎች ቀርበው በሂደት ላይ ይገኛሉ።
እነዚህ ክሶች መቋጫ ሳያገኙ የናይጄሪያ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የአሪክ አየር መንገድ አስተዳደርን ለመረከብ ተደራድሬያለሁ ማለቱ ሕገወጥና ለኪሳራ የሚዳርግ ነው ብሏል። _ የአሪክ አየር መንገድ።
እናም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሌላ ተወዳዳሪ ተቋም ጉዳይ ጣልቃ በመግባትና ባደረሰው ጉዳት የናይጄሪያ አቃቤ ህግ ምርመራ እንዲጀምር ፍርድ ቤቱ እንዲያደርግ አሪክ አየር መንገድ አቤቱታ አቅርቧል።
የአሪክ አየር መንገድ ለናይጄሪያ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ ቢያቀርብም ለየትኛው ዳኛ እንደተመራና በመቼ ጊዜ ቀጠሮ እንደተሰጠ ገና የታወቀ ነገር አለመኖሩን የአፍሪካ ፕሬስ ኤጀንሲ ዘግቧል።

Thursday, September 7, 2017

ONLF says member handed over to Ethiopia not terrorist


Abdikarin Sheikh Muse
ESAT News (September 7, 2017)
The Ogaden National Liberation Front (ONLF) said an executive member of the Front, Abdikarin Sheikh Muse, who was handed over to Ethiopia last week was not a terrorist as described by the cabinet of the Somali government.
Hassan Abdulahi, a senior member and spokesperson of the ONLF, was responding to statementents by the Somali government spokesperson that Sheikh Muse was a terrorist and his extradition to the Ethiopian regime was “a legal step taken to remove a security threat.”
Abdulahi told ESAT that there is no extradition agreement between the two countries and the statement coming out of the Somali Information Minister Abdirahman Omar Osman was a text prepared by an operative of the Ethiopian regime in Somalia known by the name General Gabre.
Abdulahi further said that the parliament not the cabinet had the power to decide on such matters. He said he had information that Parliament will convene Saturday to deliberate on the issue.
Somalis both at home and abroad denounce the government of Mohamed Abdullahi Farmajo for handing over Sheikh Muse to the Ethiopian regime. Farmajo won the election running on the platform of restoring the sovereignty of Somalia and stop meddling by the TPLF in the affairs of the country. Somalis believe the President had broken his promise by handing over Sheikh Muse to the TPLF.
Somalis in Mogadishu and Kenya took to the street to denounce the extradition of Abdikarin Sheikh Muse, also known as Qalbi-Dhagax. Asked why Somalis care if Sheik Muse is an ONLF that is fighting the Ethiopian regime, Abdulahi responded “Somalis are one people regardless of where they live.”
The Ethiopian regime says Abdikarin Sheikh Muse surrendered at his will.

Wednesday, August 16, 2017

Ethiopia: Court denies bail to Bekele Gerba


ESAT News (August 10, 2017)
The 4th criminal bench of the federal high court in Addis Ababa on Thursday denied bail to a prominent Ethiopian opposition leader while the 2nd bench gave additional time to police investigating the cases of individuals accused of corruption.
Bekele Gerba, first secretary general of the Oromo Federalist Congress was initially accused of terrorism but the charges were later reduced to criminal offences. As soon as the charges were reduced, Gerba’s lawyers requested bail for their client. The court in today’s session rejected the request saying Gerba “could incite violence” if released. Gerba, among other charges, was accused of igniting the unrest in the Oromo region last year.
Gerba responded to the court saying he expected no justice from the court and that he was not surprised at all. Gerba said that was not the first time an Ethiopian court made such a decision.
Bekele Gerba a linguist who taught at the Addis Ababa University for nearly three decades is also a vocal opposition figure in Ethiopia. Gerba had previously served 4 years on trumped up charges of terrorism. No sooner had he been released upon serving his four years sentence than he was arrested again in December 2016.
Meanwhile the 2nd bench of the court gave police additional 14 days in the case 16 individuals recently detained on suspicion of high level corruption. The individuals, including the former bosses of the Addis Ababa Roads Authority, were arrested a week ago as part of the crackdown against corruption by the regime. Critics say the campaign has left untouched high level officials who are accused of squandering billions of dollars.

wanted officials