Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Showing posts with label #ESAT. Show all posts
Showing posts with label #ESAT. Show all posts

Tuesday, January 9, 2018

የጎንደር የውሃ ፕሮጀክት ተቋረጠ






(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2010)

ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ሆነበት የተባለውና ሁለት ጊዜ የተመረቀው የጎንደር የውሃ ፕሮጀክት መቋረጡ ተገለጸ።

የህዝብ ቁጣ ይቀሰቀሳል በሚል ጉዳዩ በሚስጢር መያዙም ታውቋል።

በሌላ በኩል ጎንደርን ጨምሮ በአማራ ክልል በበርካታ ከተሞች የውሃና መብራት አገልግሎት መቋረጡ ታውቋል።

ከውሃና መብራት ሌላ ዘይትና ስኳር ከገበያ በመጥፋታቸው ህዝቡ በከፍተኛ ችግር ላይ እንደሚገኝ በደረሰን መረጃ ላይ ተመልክቷል።

የጎንደርን የውሃ ጥም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያረካል በሚል በአገዛዙ መገናኛ ብዙሃን ሲነገር የነበረው፣ ሁለት ጊዜም የምርቃት ስነስርዓት የተደረገለትና 525 ሚሊዮን ብር የተመደበለት የጎንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ውሃ በልቶት ቀርቷል።



ኢሳት ያገኘው መረጃ ላይ እንደተመለከተው በ2007 እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ነው።

ወቅቱ ደግሞ የህዝብ አመጽ የተቀጣጠለበት ሲሆን የአገዛዙ ዓላማ አመጹን ያበርዳል በሚል በችኮላ የታቀደ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል።

በሁለት ዓመት ውስጥ ያልቃል የተባለው ይህ ፕሮጀክት ያለበቂ የአፈርና የመልከዐምድር ጥናት መካሄዱን ምንጮች ገልጸዋል።

ከቆላድባ አካባቢ ካለው መሬት ላይ ውሃ ላማውጣት የተጀመረው ፕሮጀክት አዘዞ መድረስ አቅቶት፡ ጎንደርን በሩቅ ትቶ መቆሙ ታውቋል።

ውሃው ወደላይ ከመውጣት ይልቅ ወደታች መሬት ውስጥ ሰርጎ የሚገባ መሆኑ የታወቀው ቁፋሮ ተካሂዶ ግንባታው ከተጋመሰ በኋላ መሆኑን የጠቀሱት ምንጮች ጉዳዩ የህዝብ ቁጣ እንዳያስነሳ በሚል እንዲደበቅ መወሰኑንም ገልጸዋል።

ጎንደር ውሃ ሳታገኝ የፕሮጀክቱ ምርቃት ሁለት ጊዜ የተከናወነ ሲሆን በክልሉ ማስሚዲያና በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መተላለፉ ታውቋል።

የሃይል እጥረት በመግጠሙ የውሃ ስርጭቱ አልተጀመረም የሚል ምክንያት በመንግስት በኩል በመቅረብ ላይ ነው።

ይሁንና 525 ሚሊየን ብር የወጣበት የውሃ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ የከሸፈ መሆኑን ለኢሳት በደረሰው መረጃ ላይ ተመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በበርካታ የአማራ ክልል ከተሞች የመብራትና የውሃ እጥረት በመከሰቱ ህዝብ ከፍተኛ ችግር ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

በጎንደር፣ ወረታ፣ ባህርዳር፣ ወልዲያና ደብረማርቆስ የተከሰተው የውሃና የመብራት እጥረት የህዝቡን የመኖር ህልውና አደጋ ውስጥ መክተቱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

በተለይም በወረታ ከተማ የውሃ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ የተቋረጠ መሆኑ ታውቋል።

የወረታ ከተማ ነዋሪ ቁጣውን ለመግለጽ እየተዘጋጀ ሲሆን የአገዛዙ ታጣቂዎች የህዝቡን ተቃውሞ ለማፈን ከወዲሁ በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

በየከተማው የተከሰተውን የውሃና የመብራት እጥረት ለመቅረፍ በአገዛዙ በኩል ምንም ዓይነት ርምጃ እየተወሰደ አለመሆኑም ታውቋል።

በአሁኑ ጊዜ የህወሀት አገዛዝ መሰረታዊ የሆኑ ፍጆታዎችንና አገልግሎቶችን ማቅረብ የተሳነው መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ከዚያ ይልቅ ብሶት የሚያሰማውን ህዝብ በሃይል ለማፈን የሰራዊትና የደህንነት አቅሙን በማጠናከሩ ላይ መጠመዱን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

ከውሃና መብራት ሌላ ዘይትና ስኳር ከገበያ መጥፋታቸውም ታውቋል።

ለቀላል ህክምና የሚሆኑ መድሃኒቶች ከመደብሮች በመጥፋታቸው በህሙማን ላይ ከፍተኛ አደጋ መደቀኑንም ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚደርሱን መረጃዎች ላይ ተመልክቷል።

አገዛዙ ለመድሃኒት መግዣ የሚሆን የውጭ ምንዛሪ እያጠረው በመሆኑ በቀጣይ አደጋው የከፋ ሊሆን እንደሚችልም ይነገራል።










Thursday, December 7, 2017

የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ የህወሃትን ሰራዊት መቶ መለሰ


(ኢሳት ዜና–ሕዳር 29/2010)
የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰራዊት የአርዱፍን ይዞታ ሰብሮ ለመግባት ያደረገው ሙከራ መክሸፉንና ተመቶ መመለሱን የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ አስታወቀ።
መብታችን እስኪከበር በሕወሃትና በመልዕክተኛው የአፋር ልዩ ፖሊስ ሃይል ላይ የጀመርነው ውጊያ ይቀጥላል ሲልም አስታውቋል።
የውጭ ሀገር ዜጎችና ጎብኚዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አርዱፍ አስጠንቅቋል።
የብሔር ብሄረሰቦች በአል ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበር በሚል በአርዱፍ ላይ የተከፈተው ዘመቻ ከአርዱፍ ተዋጊዎች አልፎ በሰላማዊ ዜጎች ላይም የተነጣጠረ እንደሆነ ግንባሩ አስታውቋል።
በዚህም ሰላማዊ የአፋር ተወላጆች ሰቆቅና እስራት እየተፈጸመባቸው እንደሆነም በመግለጫው ተመልክቷል።
ከነሀሴ ወዲህ 580 ሰዎች በሕገ ወጥ መንገድ ተይዘው በተለያዩ ስፍራዎች መታሰራቸውንም አርዱፍ አስታውቋል።
የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰራዊት ከአፋር ክልል ልዩ ሃይል ፖሊስ ጋር በመሆን፣በህዳር ወር ሶስተኛ ሳምንት በሞጎሮስ ተራራማ ስፍራ ላይ የተጀመረው ውጊያ እንደ አውሮፓውያኑ እስከ ታህሳስ 3/2017 መቀጠሉን በመግለጫው ዘርዝሯል።
የሕወሃት ሰራዊት የአርዱፍን ይዞታ ሰብሮ ለመግባት ያደረገ ሙከራ ባለፈው እሁድ ሙሉ በሙሉ መክሸፉንና ተመተው መመለሳቸውን ይፋ አድርጓል።
በዚህም 17 ወታደሮች ሲገደሉ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ቆስለዋል ሲል በመግለጫው አስታውቋል።
የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ መብቱ እስኪከበር ውጊያውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ሕዳር 28/2010 ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
በአፋር ክልል የሚገኙ የውጭ ሀገር ኩባንያዎች እንዲሁም ጎብኝዎች ለደህንነታቸው ሲሉ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።
አዳዲስ ጎብኚዎችም ወደ አካባቢው እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ በአፋር ክልል ለ7 ጊዜያት ያህል ጎብኝዎችን እያገተ በድርድር ሲፈታ ቆይቷል።
በዚህም አለም አቀፍ እውቅና ያገኘ ሲሆን ባለፈው እሁድ በአፋር ክልል ከተገደሉት ጀርመናዊ ጎብኚ ጋር በተያያዘም የስርአቱ ደጋፊ መገናኛ ብዙሃን አርዱፍን ተጠያቂ ማድረጋቸው ይታወሳል።

Saturday, September 23, 2017

በቢልና ሚሊንዳ ጌት ፋውንዴሽን እንዲሁም በሌሎች ለጋሾች የሚሰጠው ድጋፍ ለአማካሪ ድርጅት በሚደረግ ክፍያ እየባከነ መሆኑ ተገለጸ

በቢልና ሚሊንዳ ጌት ፋውንዴሽን እንዲሁም በሌሎች ለጋሾች የሚሰጠው ድጋፍ ለአማካሪ ድርጅት በሚደረግ ክፍያ እየባከነ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያን የግብርና ስርአት ለማሻሻልና አርሶአደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ በቢልና ሚሊንዳ ጌት ፋውንዴሽን እንዲሁም በሌሎች ለጋሾች የሚሰጠው ድጋፍ ከተግባራዊ ስራ ይልቅ ለአማካሪ ድርጅት በሚደረግ ክፍያ እየባከነ መሆኑን ምንጮች ገለጹ።
የኢትዮጵያ ግብርና ማበልጸጊያ ማእከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ካሊድ ቦምባ የዘመዶቻቸው ንብረት ለሆነውና ፈርስት ኮልሰንታሲ ለተባለው ድርጅት በእርዳታ የሚመጣውን ገንዘብ እያሻገሩ እንደሆነም ተመልክቷል።
የጉዳዩን አሳሳቢነት በተመልከተ የሚመለከታቸው አካላት ለጸረ ሙስና ኮሚሽን እንዲሁም ለቢልና ሚሊንዳ ጌት ፋውንዴሽን አቤቱታ ማቅረባቸውንም ለኢሳት የደረሰው ዜና ያመለክታል።
የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመንና አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በቢልና ሚሊንዳ ጌት ፋውንዴሽን ድጋፍ የተቋቋመው የግብርና ማበልጸጊያ ተቋም ስራን በሃላፊነት እንዲመሩ አቶ ካሊድ ቦምባ የተባሉ አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያዊ ተወላጅ ወደ ኢትዮጵያ መሄዳቸውንና ለሶስት አመት በኮንትራት እንዲሰሩ መወሰኑን ምንጮች ገልጸዋል።
ሆኖም ግለሰቡ የኮንትራት ጊዜያቸው ካለፈ ሶስት አመት ቢቆጠርም ምንም አይነት የተጨበጠ ነገር ባለመታየቱ ጥረቱ መክሸፉን ምንጮቹ ይገልጻሉ፡፡
ይህ ሁሉ ሆኖ ግን አቶ ካሊድ ቦምባ አሁንም በሃላፊነታቸው ላይ መሆናቸውን መረጃው ያመለክታል።
በእቅዱ መሰረት ከሶስት አመት በኋላ አቶ ካሊድ ቦምባ በኢትዮጵያዊ ዜጋ እንዲተኩ የተወሰነ ቢሆንም ተግባራዊ መሆን ግን አልቻለም።
በየአመቱ የሚገኘው 60 ሚሊየን ዶላርም የርሳቸው ዘመዶች ንብረት ለሆነው ፈርስት ኮንሰልታንሲ በአማካሪነት ስም እየባከነ መሆኑ ታውቋል።
ፈርስት ኮንሰልታንሲ በቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አህመድ ቄሎና በልጃቸው ነቢል ቄሎ የሚመራ የቤተሰብ ተቋም እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
በአሜሪካው ዜጋ በአቶ ካሊድ ቦምባ የሚመራው የግብርና ማበልጸጊያ ተቋም በ2008 ባሳተመው አመታዊ መጽሄት በመስኩ በአለም አቀፍ ድጋፍ ምን ተሰራ የሚለውን ከመመለስ ይልቅ የመጽሄቱን የመጀመሪያ ገጾች የሀገሪቱን ባለስልጣናት መልዕክት በማስተናገድና ስለ ሀገሪቱ የግብርና ታሪክ በመዘርዘር እንዲሁም እቅዶችን በማብራራት ወደ 130 ገጽ በሚሆነው መጽሔት የተሰራ ስራ ማስፈር አለመቻሉን ከመጽሄቱ ጋር አያይዘው ለኢሳት የደረሱት መረጃዎች አመልክተዋል።
በአጠቃላይ በ26 አለም አቀፍና አህጉራዊ እንዲሁም ሀገራዊና ግለሰባዊ ድርጅቶች ድጋፍ የሚደረግለትና በአቶ ካሊድ ቦምባ የሚመራው የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድርጅት የታሰበለት አላማ መክሸፉን ምንጮቹ ይናገራሉ።
ሆኖም የሚመጣውን ገንዘብ የሚጠቀሙት አማካሪዎች ሀሴት እያጋበሱ መሆኑንም መረዳት ተችሏል።
የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድርጅት ሃላፊዎች ከመንግስት ባለስልጣናት በይበልጥም ከሕወሃት ሰዎች ጋር በፈጠሩት ቅርበት ከመቀሌ ዩኒቨርስቲና ከሬዲዮ ፋና ጋር በትብብር የሚሰሩዋቸው ስራዎች በመኖራቸው የመንግስትን ከለላ ለማግኘት እንደረዳቸው የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ለጸረ ሙስና ኮሚሽን በቀረበ ሪፖርት መሰረት ጸረ ሙስና ኮሚሽን የጀመረው ምርመራ የቆመው በሕወሃት መሪዎች ግፊትና በአቶ ሃይለማርያም ደብዳቤ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል።
 

Sunday, September 17, 2017

Nigerian Airline files 56M suit against Ethiopian Airlines, Nigerian gov’t



Arik Air, a Nigerian airline, has filed a 55.6 million dollars suit against the the Nigerian government and Ethiopian Airlines over recent news in the media that Ethiopian Airlines was negotiating with the Nigerian government to takeover the management of Arik Air Limited.
According to a copy of the suit obtained by the News Agency of Nigeria on Sunday in Lagos, the plaintiff asked the court to restrain the first and second defendants from further negotiations on the takeover of Arik Air.
“The plaintiff avers that the agreement of the second defendant with the first defendant will be wide ranging and intricately affect every aspect of the plaintiff herein, including but not limited to the day to day running technical as well as financial management which will affect the plaintiff as being the largest domestic and regional airline in Nigeria.”
“The plaintiff further avers that the action taken by the first and second defendants will have a negative effect on the country’s image as the plaintiff being the largest airline will be pawned over to another country for management,” it said.
The plaintiff also averred that the negotiations had caused undue hardship and irreparable damage to the Arik Air brand and ongoing investment discussions as well as unbearable distress to the airline’s shareholders and directors, according to the Premium Times of Nigeria.
The plaintiff asked the court to declare the negotiations null and void because the Ministry of Transportation had no power to transfer the management of the airline to Ethiopian Airlines while the suits over the takeover are pending.
The plaintiff also asked the court for an order directing the Attorney General of the Federation to ensure the investigation of Ethiopian Airlines by the appropriate authorities for inducing and interfering in the administration of justice in the pending suits, the Times of Nigeria reported.
ESAT News 

Killings, displacement continue in Eastern Ethiopia as violence intensifies


Photo from social media showing displaced Oromos in Chinaksen
ESAT News (September 14, 2017)
Officials of the Oromo and Somali regional administrations traded accusations and counter accusations amid the death of scores of people on both sides in a new wave of violence.
The Somali administration said in a statement that in Aweday town alone, a commercial hub in Eastern Ethiopia, over 50 Somalis were killed in the last few days, while an official with the Oromo administration told ESAT that about 12,000 Oromos have been evicted from Jijiga. Clashes also flared up while the Oromos were on their way to Harar and they were attacked by the Somali Liyou Forces, according to the official. Twelve people were killed from the Somali side in a counter attack by the Oromos.
What began as a turf dispute between the two communities has now grown into deadly violence.
Analysts fear the worst in the East African country where ethnic politics has been the guiding principle of a regime known for its abysmal human rights record. Indifference by the regime in the face of deadly violence, the analysts say, tantamount to complicity.
Demonstrations were held in the labyrinth city of Harar, where according to information received by ESAT, the Agazi forces of the regime killed one person.
The violence has also spread to Somaliland where reports reaching ESAT show the Oromos were under attack and unknown number of people are feared to have been killed.

wanted officials