Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, November 18, 2017

የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት የዩኒቨርስቲዎችን ድልድል አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ አልቀበለውም አሉ


የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ምደባ አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር እየተጠቀመበት ያለውን አሰራር እንደማይቀበሉት አስታወቁ።
የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው መመሪያ የአንድ ሀገር ህዝቦችን የሚነጣጥልና የፌደራሊዝም ስርአቱን የሚያበላሽ ነው ሲሉም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በተነሳ ግጭት በርካቶች ሕይወታቸውን አጥተዋል።በሺዎች የሚቆጠሩ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል።
አሁን ላይ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትና ከቀያቸው የተፈናቀሉትን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ጥረት እየተደረገ ባለበት በአሁኑ ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው አዲስ መመሪያ ሌላ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኗል።
መመሪያው የኦሮሞ ክልል ተወላጆች በሶማሌ ክልል፣የሶማሌ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች ደግሞ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች እንዳይመደቡ የሚያዝ ነው።
ይህንን መመሪያ ደግሞ የሶማሌ ክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በፍጹም እንደማይቀበሉትና መመሪያውንም እንደማያምኑበት ነው ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ የተናገሩት።
እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ የኦሮሞ ተማሪ ጅግጅጋ የራሱ ነው።የሶማሌው ተማሪም ኦሮሚያ ውስጥ ያለው መሬት የራሱ ነው።ይህንን ነው ልንነግራቸው የሚገባው።
የኦሮሚያ ክልል መንግስትም ቢሆን እንዲህ አይነቱን መለያየት የሚያምንበት አይመስለኝም ብለዋል።
የኦሮሚያ ተማሪዎች ከጅግጅጋ የሶማሌ ክልል ተማሪዎች ከኦሮሚያ ውጭ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ የሚያዘውን መመሪያም አላምንበትም ሲሉ አስምረውበታል።
የሁለቱ ክልል ህዝቦችን በጠላትነት እንዲፈራረጁ ማድረግ የለብንም።–ስለ አንድነት ነው ልንነግራቸው የሚገባው።የአንድ ሀገር ህዝቦች መሆናችንን መዘንጋት የለብንም እንደ አቶ አብዲ አባባል።
መመሪያው የፌደራሊዝም ስርአቱንም ቢሆን የሚያበላሽ ነው ብለዋል።
አሁን በክልሉ መሻሻሎች አሉ ያሉት አቶ አብዲ ቀድሞውንም ቢሆን እንደዚህ አይነቱ ችግር መፈጠር አልነበረበትም ሲሉ ያክላሉ።
ሁሉም ነገር ወደ ነበረበት መመለስ አለበት የሚሉት አቶ አብዲ ይህን ለማድረግ ደግሞ የተጀመሩ ጥረቶች አሉ።
የሶማሌ ክልልም የሚያስፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነው።
በኢትዮጵያ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ በታች መሆናቸው እየተነገረ ባለበት በአሁኑ ወቅት እንዲህ አይነቱን መመሪያ ማውጣትና የተማሪዎች ክፍፍልን መፍጠር ሌላ ጥያቄን ያጫረ ጉዳይ ሆኗል።
በሰው ሃይል፣በትምህርት አሰጣጥ፣በመሰረተ ልማት፣በተማሪዎቹ ብቃት በአጠቃላይ በሀገሪቱ በተደረገ ጥናት 30 ሺ 605 ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ በታች ሆነዋል መባሉን ኢሳት በትላንት የዜና እወጃ ሰአቱ ማቅረቡ ይታወሳል።

ባህርዳር የገባው የአክሱም ከነማ እግር ኳስ ቡድን ያረፈበት ሆቴል ላይ የቦምብ ጥቃት ተፈጸመ


ባህርዳር ከነማ ጋር ውድድሩን ሊያካሂድ ባህርዳር የገባው የአክሱም ከነማ እግር ኳስ ቡድን ያረፈበት ሆቴል ላይ የቦምብ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ውጥረት መንገሱ ተሰማ።
ማምሻውን የልዩ ሀይል ፖሊሶች ተጫዋቾቹን ከሆቴሉ ለማስወጣት እየሞከሩ መሆናቸው ታውቋል።
በሁለቱ ቡድኖች መካከል ነገ ይካሄዳል ተብሎ ስለሚጠበቀው ጨዋታ ግን የተባለ ነገር የለም።
በሌላ በኩል በኦሮሚያ ክልል ዝዋይ /ባቱ/ ከተማ በግለሰቦች መካከል ተቀስቅሷል የተባለ ጸብ ወደ ሌሎች ተሸጋግሮ ከ10 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሞትና ለበርካቶች መቁሰል ምክንያት መሆኑ ታውቋል።
በመቱ ዩንቨርስቲ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ የመማር ማስተማር ሂደቱን ሙሉ በሙሉ መስተጓጎሉ ተሰምቷል።
የአክሱም ከነማ ቡድን ባህር ዳር ሲገባ ያወቀም ሆነ በግልጽ የተነገረ ነገር አልነበረም።
ነገር ግን ቡዳኑ ወደ ከተማዋ ከገባ በኋላ ንብረትነቱ የህወሃት የደህነነት ሰው እንደሆነ በሚታወቀውና ቀበሌ 02 በሚገኘው ዳግማዊ ዮሃንስ ጋርደን ሆቴል ማረፉ የታወቀው በሆቴሉ ላይ የቦምብ ፍንዳታ ከተከሰተ በኋላ ነው።
በተፈጸመው ጥቃትም እስካሁን ሁለት ሰዎች መጎዳታቸውናን ወደሆስፒታል መወሰዳቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
ማምሻውን የልዩ ሀይል ፖሊሶች ተጫዋቾቹን ለማስወጣት እየሞከሩ መሆኑን ከመረጃው ለማወቅ ተችሏል።
እስካሁን ጥቃቱን ማን ፈጸመው ለሚለው ግን ምላሽ አለተገኘለትም።
ከተፈጸመው የቦንብ ጥቃት ጋር ተያይዞ ነገ ይካሄዳል የተባለው ጨዋታ በመርሃ ግብሩ መሰረት ይካሄድ አይካሄድ የታወቀ ነገር የለም።
የከተማው ህዝብ ጨዋታውን ለመመልከት ወደስፈራው የመሄዱ ጉዳይም አጠራጣሪ ሆኗል።
እንደ ኢሳት ምንጮች ከሆን ከቦምብ ጥቃቱ ጋር ተያይዞ በከተማዋ ውጥረት ነግሷል።
ከባህርዳር ከነማ ጋር የአክሱም ከነማ እግር ኳስ ቡድን ጨዋታውን በባህርዳር ብሔራዊ ስታዲየም እንዲያካሂድ መርሃ ግብር ወጥቶለታል።
ነገር ግን ከዚህ በፊት በከተማዋ ይካሄዱ የነበሩ የሊግ ጨዋታዎች ሲካሄዱ የነበሩት በአጠቃላይ በባህርዳር ዩንቨርስቲ ፔዳ ሜዳ ሲሆን አሁን ይህ ጨዋታ በባህርዳር ብሄራዊ ስታዲየሙ እንዲካሄድ መወሰኑ ጥያቄ አስነስቷል።
በሌላ በኩል በኦሮሚያ ክልል ዝዋይ /ባቱ/ ከተማ በግለሰቦች መካከል ተቀስቅሷል የተባለ ጸብ ወደ ሌሎች ተሸጋግሮ ከ10 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሞትና ለበርካቶች መቁሰል ብሎም መፈናቀል ምክንያት መሆኑ ታውቋል።
በቡድን የተደራጁ ወጣቶች ወደ ከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ነዋሪዎችን ሲደበድቡና ሲያዋክቡ መዋላቸው ተነግሯዋል።
ችግሩ በተከሰተበት ሰዓት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ባለመድረሱና በቂ ሃይል ይዞ ባለመምጣቱ አስቸኳይ መፍትሄ መስጠት እንዳልተቻለ ምንጮቻችን ገልጸዋል።
በዚህም ምክንያት በግጭቱ 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን የአካባቢው ምንጮች አስታውቀዋል።
በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸውና የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በከተማዋ አስተዳደር እርዳታ እየተደረጋላቸው መሆኑ ሲጠቀስ ነዋሪዎቹ አሁንም ስጋት ወስጥ መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በሌላ በኩል የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ በመግለጫቸው እንደጠቀሱት በመቱ ዩንቨርሲቲ ተማሪ የነበሩት የአማራ ተወላጆች ዩኒቨርስቲውን ለቀው በመውጣት በከተማዋ መናሃሪያ ተሰባስበዋል።
እንደቃል አቀባዩ ገለጻ ሌላ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው አካላት ባደረጉት ቅስቀሳ ተማሪዎቹ ከማደሪያቸው ለቀው በመውጣት ለአራት ቀናት በመሰብሰቢያ አዳራሽ አድረዋል።
ችግሩን ለመፍታትና ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በሀይማኖት አባቶች፥ በአባ ገዳዎች፥ በሽማግሌዎች፥ በከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲሁም በዩኒቨርስቲው አካላትና መምህራን ቢለመኑም አሻፍረኝ ማለታቸው ተጠቅሷል።
የክልሉ መንግስት ጸጥታው አስተማማኝ ነው ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰው ጥያቄያቸውን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ ይችላሉ ቢልም ተማሪዎቹ አልተቀበሉትም ።
በተመሳሳይም የደቡብ ተወላጅ ተማሪዎች ዩንቨርስቲውን ለቀው በመውጣት ላይ መሆናቸውም ታውቋል።

ጦሩ ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙጋቤ በአደባባይ ታዩ

ጦሩ ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙጋቤ በአደባባይ ታዩ
ሙጋቤ ሰማያዊ እና ቢጫ ቀለም ያለው ቆብ አድርገው ይታያሉ
የሃገሪቱ ጦር ከሶስት ቀናት በፊት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ሮበርት ሙጋቤ በአደባባይ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የታዩት።
በዚምባብዌ መዲና በሆነችው ሃራሬ በተማሪዎች የምረቃት ፕሮግራም ላይ ለህዝብ የታዩት።
ላለፉት ጥቂት ቀናት ሙጋቤ በቁም እስር ላይ መቆየታቸው ይታወቃል።
አርብ ጠዋት የዚምባብዌው ሄራልድ ጋዜጣ ሙጋቤ የጦሩን መሪ ጀነራል ኮንስታኒቲኖ ቺዌንጋንና የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ(ሳድክ) ተወካዮች ጋር በቤተመንግሥት ሲነጋግሩ የሚያሳዩ ፎቶዎችን አውጥቶ ነበር።
ሙጋቤ ከሥልጣን አልወርድም እያሉ ነው
ሬውተርስ የዓይን እማኝን ጠቅሶ እንደዘገበው ሙጋቤ በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ካደረጉ በኋላ ከተመራቂዎች ሞቅ ያለ ድጋፍ አጊንተዋል።
ሙጋቤ ለቤት ውስጥ እስር ከዳረጋቸው የሀገሪቱ ጦር መሪ ጋር ሲጨባበጡና ሲወያዩ ቢታዩም እስከቀጣዩ ምርጫ ሥልጣኔን አልለቅም ማለታቸውን የመረጃ ምንጮች እየገለጹ ነው።
የሃገሪቱ ጦር ከሶስት ቀናት በፊት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ሙጋቤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ።
BBC.COM

በሊቢያ አፍሪካውያን ስደተኞች ለባሪያ ንግድ የጨረታ ሽያጭ ይቀርባሉ ተባለ

Gambian migrants returning home from Libya carry bags from UN agency the International Organization for Migration.

በሊቢያ አፍሪካውያን ስደተኞች ለባሪያ ንግድ የጨረታ ሽያጭ እንደሚቀርቡ የሚያሳይ በምስል የተደገፈ መረጃ ይፋ ሆነ።
ሲ ኤን ኤን ይፋ ባደረገው በዚህ መረጃ ከ10 በላይ የሚሆኑና ከኒጀር የመጡ ስደተኞች በ6 ደቂቃ ውስጥ በጨረታ መሸጣቸውን አጋልጧል።
ይህ ክስተት ከዘመናት በፊት የተሻረውን የሰው ልጅን እንደሸቀጥ የመሸጥ አስከፊነት እንደገና እንዲታወስ አድርጓል ሲል ዘገባው አመልክቷል።
በሊቢያ የሚገኙ ሕገወጥ አዘዋዋሪዎች ከተለያዩ አፍሪካ ሀገራት የሚሄዱ ስደተኞችን በጨረታ እንደሚሸጧቸው ሲ ኤን ኤን በምስል አስደግፎ ያወጣው መረጃ አጋልጧል።
ሲ ኤን ኤን በቅድሚያ የተላከለትንና ከምዕራብ አፍሪካ የመጡ ስደተኞች በጨረታ ሲሸጡ የሚያሳየውን ምስል መሰረት አድርጎ የራሱን ጋዜጠኞችና የምስል ባለሙያዎች በመላክ የባሪያ ንግዱ በጨረታ ሲከናወን የሚያሳየው ሪፖርት ከረጅም አመታት በፊት የተሻረውን የባሪያ ንግድ አስከፊ ገጽታ እንደገና እንዲታወስ አድርጓል።
“ትልቅ ጠንካራ ልጆች ለግብርና ስራ” ይላል ፊቱን የሸፈነው አጫራቹ ተጫራቾችም እጃቸውን እያወጡ “400,500,800 ፓውንድ” እያሉ ንግዱን ሲያጧጡፉ ያሳያል ሲ ኤን ኤን በምስል አስደግፎ ይፋ ያደረገው መረጃ።
ወደ አውሮፓ ለመሻገር ተስፋን ሰንቀው በሊቢያ በርሃ ላይ ጉዟቸውን የጀመሩ ከኒጀር፣ማሊ፣ናይጄሪያና ጋና የሄዱ ስደተኞች ከሊቢያ መዲና ትሪፖሊ ወጣ ብላ በምትገኝ ከተማ በአማካኝ በ400 ዶላር በጨረታ ሲሸጡ ተስተውሏል።
በዚህ ሲ ኤን ኤን በለቀቀው ምስል ውስጥ ከ10 በላይ የሚሆኑና ከኒጀር የመጡ ስደተኞች በ6 ደቂቃ ውስጥ በጨረታ ተሽጠዋል።
በወር ሁለት ጊዜ ለሚካሄደው ለዚሁ ጨረታ የሚመረጡት ስደተኞች እንደ እድለኛ ነው የሚቆጠሩት።
አጫራቾቹም ስደተኞቹን “ባዳዬ” ብለው ይጠሯቸዋል።”ሸቀጥ” እንደማለት ነው በአረብኛ።
“ወደ ሀገራችን ይውሰዱን እዚህም የመጣነው ተሽጠን ነው።” “ተመልከቺ የገላዬን ጠባሳ የተደበደብኩት ነው” ያላሉ አንዳንዶቹ ለሲ ኤን ኤን ጋዜጠኛ ኒማ ኤልባገር።
ብዙዎቹ ጓደኞቻቸው በየመንገዱ እንደሞቱም ስደተኞቹ ተናግረዋል።
ከጨረታው በኋላ የሲ ኤን ኤን ጋዜጠኛ ለማናገር የሞከረቻቸው ሁለት ለጨረታ የቀረቡ ስደተኞች በሆነው ነገር እጅግ ከመደናገጣቸውና ሁሉንም ሰው ማመን ካለመቻላቸው ጋር ተያይዞ ምንም አይነት ቃል መናገር አልቻሉም።
ሲ ኤን ኤን ጨረታውን የሚያሳየውን ምስል ለሊቢያ ባለስልጣናት ማሳየቱንና ባለስልጣናቱም ምርመራ እንደሚያካሂዱ ተናግረዋል።
በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን በየአመቱ ወደ አውሮፓ ለመሻገር የሊቢያን ድንበር አቋርጠው ይገባሉ።
ብዙዎቹ ያሰቡበት ሳይደርሱ ግን መንገድ ላይ ይቀራሉ።–ተረፉ የተባሉትም ለባሪያ ንግድ ተጋልጠዋል።
በሚያዚያ 2008 30 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በአይሲስ አሸባሪ ቡድን አሰቃቂ በሚባል ሁኔታ መገደላቸው አይዘነጋም።
መስቀልና ሌሎች ክርስትናን የሚያመላክቱ ነገሮችን በመያዛቸው ከፊሎቹ በቢላ ሲታረዱ ሌሎቹ ደግሞ በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ የሚያሳየው ምስል አሁንም ከኢትዮጵያውያን ሕሊና አልጠፋም።
በጨረታ የተሸጡት እነዚህ አፍሪካውያንም ከዘመናት በፊት የተሻረውን የሰው ልጅን እንደሸቀጥ መሸጥ አስከፊነት እንደገና እንዲታወስ አድርጓል።

Friday, November 17, 2017

ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን አስወግደው በጋራ ለመንቀሳቀስ መወሰናቸውን አስታወቁ


በአሜሪካ ሚኒሶታ ግዛት የሚኖሩና በተለያዩ ማህበረሰቦች የተደራጁ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን አስወግደው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በጋራ ለመንቀሳቀስ መወሰናቸውን አስታወቁ።
በዚህም በግጭት የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመታደግ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያውያኑ በጋራ ያስተባበሩትና ለተፈናቃዮች መደገፊያ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ የሙዚቃ ዝግጅት ነገ በሴንትፖል ሚኒሶታ እንደሚካሄድ ታውቋል።
በአሜሪካ ሚኒሶታ ግዛት የሚኖሩትና በተለያዩ ማህበረሰቦች ተደራጅተውና ሳይደራጁ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በአንድነት ለመንቀሳቀስ ወደ 6 ወራት የፈጀ ውይይት ማድረጋቸው ተመልክቷል።
በዚህም በተፈጠረው ቅርርብና ትብብር የሃይማኖት መሪዎች፣አባገዳዎች እንዲሁም አዛውንቶች በተገኙበት ባለፈው መስከረም መጨረሻ ሰፊ ውይይት አካሂደው የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ለወገኖቻቸው ያላቸውን አጋርነትም አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያውያን በአካባቢና በብሔር እንዲሁም የእምነት ግጭት እንዳይፈጥሩ፣ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትንም እንዲመክቱ በጋራ ጥሪ አቅርበዋል።
በሚኒሶታ የሚኖርቱ ኢትዮጵያውያን በግጭት የተፈናቀሉትን ለመርዳት በገቡት ቃል መሰረት ነገ ጥቅምት 18/2017 የሙዚቃ ፕሮግራም ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ከቀትር በኋላ 4pm ተጀምሮ ለሊት 2AM በሚጠናቀቀው የሙዚቃና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚኒያፖሊስና በሴንት ፖል ከተሞች የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን እንዲገኙ ጥሪ አቅርበዋል።

Thursday, November 16, 2017

በጭልጋ የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዩች ከሱዳን የገባ የህወሓት/ወያኔ ነዳጂ በጫነ ቦቲ እና አጃቢወቹ ላይ ጥቃት ፈፀሙ !!

በጭልጋ የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዩች ከሱዳን የገባ የህወሓት/ወያኔ ነዳጂ በጫነ ቦቲ እና አጃቢወቹ ላይ ጥቃት ፈፀሙ !!
ከጎንደር አዘዞ እስከ ጭልጋ መተማ ድረስ ውጥረቱ በርትቷል።
ህዳር 7 ምሽት ላይ በጭልጋ ወረዳ ጓንግ ወንዝ አካባቢ ባደረሱት ጥቃት መኪናውና የጫነው ነዳጂ ከጥቅም ውጭ ሲሆን በአጃቢወች በወያኔ ወታደሮች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በአካባቢው ከጎንደር እስከ ጭልጋ መተማ ድረስ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ሲሆን በአጋዚ ጦር ፍተሻ እየተካሄደ ቀጣይ የሚሆነውን መገመት ቢከብድም ውጥረቱ የነበረውን ትኩሳት ይበልጥ አግሎታል።
በብዙ የአጋዚ ጦር ተሰትሮ እንዴት ጥቃት ይሰነዘርብናል የወያኔ ካድሬወች ቀልብ የሚያስት የውርደት ቁጭት ነው። ህዝቡ ዛሬም ከአርበኞች ጋር መስለፉን በደስታ አረግልግጧል።
ጎንደር ዙሪያው ከንጋት ጀምሮ በአሳሽ ግብረ ሃይሉ ተወራለች። መግቢያ መውጫዋ ጓዳ ጎድጓዳዋ አልቀረም ፍተሻው ጠንክሯል። ወዲህ ደግሞ ህዝብ አምርሯል!!
ድል ለአርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል!!

Wednesday, November 15, 2017

በሻኪሶ ዛሬ ከባድ ሕዝባዊ ተቃውሞ ተካሄደ


በሻኪሶ ዛሬ ከባድ ሕዝባዊ ተቃውሞ ተካሄደ።
በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የከተማዋና የአካባቢው ነዋሪዎች ለተቃውሞ የወጡት ሜድሮክ ኢትዮጵያ በአካባቢው የሚያከናውነውን የወርቅ ማውጣት ስራ ለተጨማሪ 10 አመት እንዲታደስለት ጥያቄ ማቅረቡን ተከትሎ ነው።
የሰልፈኞቹ ለተቃውሞ መውጣት ምክንያቱ ይህ ነው ይባል እንጂ ዋነኛ ጥያቄያቸው ግን የወያኔ ስርአት ይብቃን የሚል ነው።
ሜድሮክ ኢትዮጵያ በሻኪሶ የወርቅ ማዕድን ለማውጣት ከህወሃት መንግስት ጋር የተፈራርመው የ20 አመት ውል ጊዜው ተጠናቋል።
ነገር ግን ተቋሙ አሁንም በአካባቢው የወርቅ ማውጣት ስራውን ለማከናወን እንዲችል ውሉ ለ10 አመት እንዲታደስለት ጥያቄ አቅርቧል።
ነገር ግን ላቀረበው ጥያቄ ከሕወሃት መንግስት ምላሽ ከማግኘቱ በፊት የአካባቢው ነዋሪ በራሱ ምላሽ ሰጥቶታል።
በአራቱም አቅጣጫዎች እየተመመ በሻኪሶ ከተማ ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰአት ላይ ለሰላማዊ ተቃውሞ የተሰባሰበውና 6 ኪሎሜትር ያህል በመጓዝ ድምጹን ያሰማው ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ቀላል የሚባል አይደለም።–በ10 ሺዎች የሚቆጠር እንደነበር በሰልፉ ላይ የተገኙት የከተማዋ ነዋሪ አረጋግጠውልናል።
እሳቸው እንደሚገልጹት ከሆነ ሰልፈኞቹ ሜድሮክ ኢትዮጵያ የሰራው ለራሱ ጥቅም እንጂ ለእኛ አይደለም የሚል መልዕክትን ይዘዋል።
ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እስከ መንግስት ሰራተኞችና ሌሎቹን የሕብረተሰብ ክፍሎች ያካተተው የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ የወርቁ ጉዳይ ብቻ አልነበረም ይላሉ።
ሰለፈኞቹ በወያኔ ስርአት አላግባብ የተጫነብን ግብር ይነሳልን ሲሉም ከፍ ባለ ድምጽ አቤቱታቸውን አሰምተዋል።
ሰልፈኞቹ ያሰሙት በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ይበቃናል የሚለው መልዕክትም ሌላው ነበር ይላሉ ለኢሳት መረጃውን ያደረሱ ነዋሪ።
ሰልፈኞቹ ወደ ተቃውሞ ሲወጡ 5 ያህል ጥያቄዎችን በመያዝ ነበር።
ሰልፈኞቹ በማጠቃለያቸው የያዟቸውን ጥያቄዎች ለአባገዳዎች ያቀረቡ ሲሆን እነዚህ ጥያቄዎቻቸው በአስቸኳይ ምላሽ ካላገኙ ለሌላ ተቃውሞ እንደሚነሱ አስረግጠው ተናግረዋል።
ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ህዝብ ድምጹን አሰምቶ በሰላማዊ መንገድ ከጨረሰ በኋላ የሀገር ሽማግሌዎች በምርቃታቸው ሰልፉ እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው መግለጫ ችግሮችን እንዳባባሰ ተገለጸ


(ኢሳት ዜና–ሕዳር 8/2010) የትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተከሰቱ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ችግሮቹን እንዳባባሰ ተገለጸ።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የችግሮቹ ዋነኛ ምንጭ ትንሽ የሚባሉ ተማሪዎች ናቸው ሲል የሰጠው ሰበባዊ መግለጫ ለችግሩ መባባስ በምክንያትነት ተቀምጧል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌጤ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ያጋጠሙ ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ በተቋማቱ የተፈጠረው ችግር በ20ና 30 ተማሪዎች ማሳበባቸው ችግሩን እንዳባባሰው ነው ለኢሳት አስተያየታቸውን የሰጡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የገለጹት።
በከፍተኝ ትምህርት ተቋማት ችግር ፈጣሪዎቹ ከ20ና 30 የማይበልጡ ተማሪዎች ከሆኑ እንዴት ችግሩን መፍታት ያቅተዋል በማለት ተማሪዎቹ ጠይቀዋል።
የተማሪን ጥያቄ በማድበስበስና በማሳነስ የመጣ ለውጥ ባለመኖሩ የትምህርት ሚኒስትሩ በይፋ ይቅርታ ጠይቀው ለተማሪው ጥያቄ ምላሽ ቢሰጡ ይሻላል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌጤ ለመንግስትና የፓርቲ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል የሚማሩ ተማሪዎችን የማዟዟር ውሳኔ የወሰነው የትምህርት ሚኒስቴር እንደሆነ ገልጸዋል።
የውሳኔው መነሻም በሁለቱ ክልሎች ጥቂት የጥገኛ ሃይሎች በፈጠሩት ችግር ምክንያት መሆኑንም አክለው ተናግረዋል።
የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሀመድ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምደባ ቅያሬ አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን መመሪያ እንደማያምኑበት በግልጽ ማስቀመጣቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
የሁለቱን ክልል ሕዝብ በጠላትነት እንዲፈራረጅ የሚያደርግና የፌደራሊዝም ስርአቱን የሚያበላሽ እንደሆነም ተናግረው ነበር።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስትም ቢሆን እንዲህ አይነቱን አሰራር የሚያምንበት አይመስለኝም ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ላይም ሆነ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት በሰጡት አስተያየት ላይ በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም።

አዘዞ በሚገኘው የ24ኛው ክፍለጦር ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ተፈጸመ


 ጎንደር አጠገብ አዘዞ በሚገኘው የ24ኛው ክፍለጦር ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ አስታወቀ።
ዛሬ ንጋት ላይ በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት የካምፑ የተወሰኑ ቤቶች በቃጠሎ መውደማቸውን ንቅናቄው አስታውቋል።
በተያያዘ ዜና ከሱዳን ነዳጅ ጭኖ ሲጓዝ በነበረ ከባድ ተሽከርካሪ /ቦቴ/ ላይ በተወሰደ ርምጃ ተሽከርካሪው ከጫነው ነዳጅ ጋር መውደሙን አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ገልጿል።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተሽከርካሪው የተቃጠለው የመገልበጥ አደጋ ደርሶበት ነው ሲሉ በግል የፌስ ቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል።
ከጎንደር በ7ኪሎ ሜትር ትርቃለች። በአቅራቢያዋ በሚገኘው የ24ኛው ክፍለጦር ካምፕ በይበልጥ ስሟ ይነሳል። አዘዞ።
ዛሬ ንጋት ላይ በዚሁ 24ኛ ክ/ጦር ካምፕ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የሚያሳዩ መረጃዎች ለኢሳት ደርሰዋል።
በካምፑ የሚገኙ ቤቶች በእሳት መያያዛቸውን የሚገልጹት መረጃዎች አካባቢው በመንግስት ጦር በመከበቡ መጠጋት እንዳልተቻለም የሚያሳዩ ናቸው።
አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ እንዳስታወቀው የንቅናቄው ታጣቂዎች በወሰዱት ርምጃ የካምፑ መጋዘን በከፊል ወድሟል።
የአካባቢው ነዋሪዎች መጋዘኑ በሚቃጠልበት ጊዜ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽና ፍንዳታ ይሰማ እንደነበር ለኢሳት ገልጸዋል።
የጎንደር አየር መንገድና የጎንደር እሳት አደጋ ቡድን ቃጠሎውን መቆጣጠር ባይችሉ ኖሮ ካምፑ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት ይደርስበት እንደነበረ ለማወቅ ተችሏል።
በአሁኑ ሰዓት ካምፑና በዙሪያው ያሉ መንደሮች በልዩ ሃይልና በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት እየተጠበቁ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
በአዘዞ የ24ኛ ክ/ጦር ካምፕ ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ተረኛ መኮንን የነበሩትና የዘብ ጠባቂዎች የታሰሩ ሲሆን በካምፑ ጭልጋ በር በሚባለው መጠበቂያ ማማ ላይ የነበሩ ሁለት ወታደሮች ከነትጥቃቸው መሰወራቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሌላ በኩል ትላንት አመሻሽ ላይ ከሱዳን ነዳጅ ጭኖ ወደ ሰሜን ጎንደር ሲጓዝ በነበረ ነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪ ቦቴ ላይ ጥቃት መፈጹሙን አርበኞች ግንቦት ሰባት አስታወቋል።
በወታደር መኪና ታጅቦ የነበረው ተሽከርካሪ ጭልጋ ወረዳ ጓንግ ወንዝ ድልድይ ከመድረሱ በፊት ጥቃት የተፈጸመበት መሆኑን የገለጸው አርበኞች ግንቦት ሰባት በጥቃቱም ተሽከርካሪው ከጫነው ነዳጅ ጋር ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል አሽከርካሪው ከባድ ጉዳት ደርሶበት ወደአይከል የህክምና ማዕከል መወሰዱን አስታውቋል።
ይህን ጥቃት በተመለከተ በግል የፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ‘’አደጋው የመገልበጥ ነው’’ ሲሉ የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገልጸዋል።
አቶ ንጉሱ እንደሚሉት የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 3 090485 የሆነ ነዳጅ የጫነ ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ በእሳት ተያይዞ የተቃጠለ ሲሆን የጸጥታ አባላት በአካባቢው ክትትል እያደረጉ ነው። አርበኞች ግንቦት ሰባት እንዳስታወቀው በተሽከርካሪው ላይ ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ማዋከብ እየተካሄደ ነው።

Migrants from west Africa being ‘sold in Libyan slave markets’





UN migration agency says selling of people is rife in African nation that has slid into violent chaos since overthrow of Gaddafi

Gambian migrants returning home from Libya carry bags from UN agency the International Organization for Migration. Photograph: Luc Gnago/Reuters

Emma Graham-Harrison




West African migrants are being bought and sold openly in modern-day slave markets in Libya, survivors have told a UN agency helping them return home.

Trafficked people passing through Libya have previously reported violence, extortion and slave labour. But the new testimony from the International Organization for Migration suggests that the trade in human beings has become so normalised that people are being traded in public.

“The latest reports of ‘slave markets’ for migrants can be added to a long list of outrages [in Libya],” said Mohammed Abdiker, IOM’s head of operation and emergencies. “The situation is dire. The more IOM engages inside Libya, the more we learn that it is a vale of tears for all too many migrants.”


'They were psychopaths': how chaos in Libya fuels the migration crisis



The north African nation is a major exit point for refugees from Africa trying to take boats to Europe. But since the overthrow of autocratic leader Muammar Gaddafi, the vast, sparsely populated country has slid into violent chaos and migrants with little cash and usually no papers are particularly vulnerable.

One 34-year-old survivor from Senegal said he was taken to a dusty lot in the south Libyan city of Sabha after crossing the desert from Niger in a bus organised by people smugglers. The group had paid to be taken to the coast, where they planned to risk a boat trip to Europe, but their driver suddenly said middlemen had not passed on his fees and put his passengers up for sale.

“The men on the pick-up were brought to a square, or parking lot, where a kind of slave trade was happening. There were locals – he described them as Arabs – buying sub-Saharan migrants,” said Livia Manante, an IOM officer based in Niger who helps people wanting to return home.

She interviewed the survivor after he escaped from Libya earlier this month and said accounts of slave markets were confirmed by other migrants she spoke to in Niger and some who had been interviewed by colleagues in Europe.

“Several other migrants confirmed his story, independently describing kinds of slave markets as well as kinds of private prisons all over in Libya,” Manente said. “IOM Italy has confirmed that this story is similar to many stories reported by migrants and collected at landing points in southern Italy, including the slave market reports. This gives more evidence that the stories reported are true, as the stories of those who managed to cross-match those who are returning back to their countries.”

After his sale, the Senegalese migrant was taken to a makeshift prison of a kind that has been well documented in Libya. Those held inside are forced to work without pay, or on meagre rations, and their captors regularly call family at home demanding a ransom. His captors asked for 300,000 west African francs (about £380), then sold him on to a larger jail where the demand doubled without explanation.

Men who lingered there too long without the ransom being paid were taken away and killed, he said. Some wasted away on meagre rations in unsanitary conditions, dying of hunger and disease, but overall numbers never fell. “If the number of migrants goes down, because of death or someone is ransomed, the kidnappers just go to the market and buy one,” Manente said.

His terrified family began scraping together loans. As he spoke fluent English, French and some local languages, he translated for his jailers to win time for relatives to collect the money.

Many other migrants flee Libya with similar stories, said Giuseppe Loprete, chief of mission at IOM Niger. “Its very clear they see themselves as being treated as slaves,” he said.

Loprete’s office has arranged for the repatriation of 1,500 people in the first three months of this year – almost the same number as in the whole of 2015. He fears more horrors are likely to emerge.


Bodies of dozens of people wash ashore in western Libya


“There are now more migrants coming back from Libya, so that’s also why all these stories are coming to the surface,” he said. “And conditions are worsening in Libya so I think we can also expect more in the coming months.”

Even growing international awareness of the problems migrants face is being exploited. IOM has had credible reports of criminals posing as aid groups that help migrants to lure in people who have escaped or bought their freedom and want to return home.

The organisation is working to spread awareness across west Africa of the horrors of the journey through the personal stories of those who return. Though most migrants know the boat trips to Europe are extremely risky, fewer realise they may face even worse dangers in Libya before even reaching the coast.

“Tragically, the most credible messengers are migrants returning home with IOM help,” said spokesman Leonard Doyle. “Too often they are broken, brutalised and have been abused. Their voices carry more weight than anyone else’s.”

ሙጋቤና ተከታዮቻቸው ስልጣኑን የ52 አመቷ ግሬስ ሙጋቤ እንዲረከቡ ይፈልጋሉ

የዚምባቡዌ ወታደራዊ አዛዦች ከሚኒስትሮችና ከሮበርት ሙጋቤ ጋር በድርድር ላይ ናቸው

(ኢሳት ዜና–ሕዳር7/2010)
በዚምባቡዌ የሀገሪቱን ስልጣን የተቆጣጠሩት ወታደራዊ አዛዦች ከሚኒስትሮችና በቁም እስር ላይ ከሚገኙት ሮበርት ሙጋቤ ጋር በድርድር ላይ መሆናቸው ታወቀ።
ድርድሩን በዋናነት የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ ሳድክ እየመራው መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካ ሕብረት በበኩሉ የወታደራዊው ሃይል ስልጣኑን በሃይል መቆጣጠሩን እንደማይቀበለው አስታውቋል።
በዚምባቡዌ ወታደራዊ አዛዦች የሀገሪቱን መንበረ ስልጣን መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ዛሬ ወታደራዊ አዛዦቹ ከሚኒስትሮች እንዲሁም በቁም እስር ላይ ከሚገኙትና ሀገሪቱን ለ37 አመታት ከመሩት ሮበርት ሙጋቤ ጋር በድርድር ላይ መሆናቸው ተነግሯል።
ቢቢሲ ከሐራሬ እንደዘገበው ድርድሩ እየተመራ ያለው ሳድክ በመባል በሚታወቀው የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ አማካኝነት ነው።
የዚምባቡዌ የተቃዋሚ መሪ የሆኑት ሞርጋን ቫንጊራይ ሙጋቤ ስልጣኝቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንዲለቁ ጠይቀዋል ተብሏል።
ቢቢሲ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው የ93 አመቱ ሮበርት ሙጋቤ ሕጋዊ ፕሬዝዳንት ነኝ በማለት ስልጣናቸውን ላለመልቀቅ እያንገራገሩ መሆኑ ተሰምቷል።
የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር የጊኒው አልፋ ኮንዴ ሕብረቱ የወታደራዊው ሃይል ስልጣኑን በሃይል መቆጣጠሩን አይቀበለውም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ኮንዴ ወታደራዊ ሃይሉ ወደ መጣበት ጦር ሰፈር እንዲመለስና ሕገ መንግስቱ እንዲከበርም ጠይቀዋል።
ዚምባቡዌ ከነጮች አገዛዝ ነጻ ከወጣችበት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1980 ጀምሮ በስልጣን ላይ የቆዩት የ93 አመቱን ሙጋቤን ማን ይተካው የሚለው ውዝግብ በመሪው ፓርቲ ዛኑ ፒ ኤፍ ውስጥ ክፍፍልን ፈጥሯል።
ሙጋቤና ተከታዮቻቸው ስልጣኑን የ52 አመቷ ግሬስ ሙጋቤ እንዲረከቡ ይፈልጋሉ።
ላለፉት 21 አመታት በትዳር ከሮበርት ሙጋቤ ጋር የቆዩት ግሬስ ሙጋቤ ከሳምንት በፊት ምክትል ፕሬዝዳንቱን ኤመርሰን ናንጋጋዋን ከስልጣን በማስወገድ ረገድ ሚና እንደነበራቸው ታውቋል።
በዛኑ ፒ ኤፍ ውስጥ የሙጋቤና የባለቤታቸው ተቀናቃኞች ደግሞ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ናንጋጋዋ ስልጣኑን እንዲረከቡ ይፈልጋሉ።
የምክትል ፕሬዝዳንቱን ከስልጣን መወገድ ተከትሎ ነበር ወታደራዊ ባለስልጣናት ዛኑ ፒ ኤፍ ፓርቲ ውስጥ ያለውን የስልጣን ሽኩቻ እናስቆማለን በሚል ጣልቃ የገቡት።
ወታደራዊ ባለስልጣናቱ የምክትል ፕሬዝዳንቱ ደጋፊዎች እንደሆኑም ይነገራል።
ከዚህ በተጨማሪም ወታደራዊው ክፍል ግሬስ ሙጋቤና ተከታዮቻቸው ስልጣኑን ለመቆጣጠር እያደረጉ ያለውን ጥረት ለማስቆም እየሰሩ እንደሆነም እየተነገረ ነው።
ለረጅም አመታት ሙጋቤን የሚያውቋቸው የሮማ ካቶሊክ ቄስ የሆኑት ፊደሊስ ሙኮኖሪ በመኖሪያ ቤታቸው በቁም እስር ላይ ያሉት ሙጋቤ ወደፊት ከወታደራዊ ሃይሉ ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት ድርድር ላይ መሆናቸውም ተሰምቷል።

Tuesday, November 14, 2017

በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ በታች መሆናቸው ተገለጸ

 በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ በታች መሆናቸውን አንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን ገለጹ።

የቻይናው ዜና አገልግሎት ዥንዋ በኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር የፕላኒንግ ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ኤልያስ ግርማን ጠቅሶ እንደዘገበው 89 በመቶ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ ዝቅ ያሉ ሆነው ተገኝተዋል።
በሰው ሃይል፣በትምህርት አሰጣጥ፣በመሰረተ ልማት፣በተማሪዎቹ ብቃት በአጠቃላይ በሀገሪቱ በተደረገ ጥናት 30 ሺ 605 ትምህርት ቤቶች ከአለም አቀፍ መመዘኛ በታች ሆነው ናቸው።
ይህም በሀገሪቱ ካሉ አጠቃላይ ትምህርት ቤቶች 89 በመቶውን እንደሚሸፍንም ይፋ አድርገዋል።
የፕላኒንግ ዳይሬክተሩ እንደሚሉት ወሳኝ የሆኑ መመዘኛዎችን መሰረት በማድረግ በተደረገ ጥናት አለም አቀፍ መስፈርትን አሟልተው አገልግሎት የሚሰጡት የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች 11 በመቶ ብቻ ናቸው።

wanted officials