Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 24, 2013

ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል በሰብአዊ መብት ጋዜጠኝነት መስፈርት አራት ጊዜ ኣዋርድ አሸናፊ ጋዜጠኛ በጋምቤላ ክልል ታሰረ

 ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል በሰብአዊ መብት ጋዜጠኝነት መስፈርት አራት ጊዜ ኣዋርድ  አሸናፊ ጋዜጠኛ በጋምቤላ  ክልል ታሰረ

ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል በሰብአዊ መብት ጋዜጠኝነት መስፈርት አራት ጊዜ ኣዋርድ አሸናፊነቱ የሚታወቀው የናሽናል ጂኦግራፊ የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ ሮቢን ሃሞንድ በጋምቤላ ክልል በቁጥጥር ስር መዋሉን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ፓሪስ ከሚገኘው የኢትዩጵያ ኢምባሲ ቪዛ ያገኘው ሮቢን በኢትዩጵያ በተለያዩ ክልሎች በመዘዋወር ፎቶ ግራፍ የማንሳት እቅድ እንደነበረው ተነግሯል፡፡የፎቶግራፍ ጋዜጠኛው ከኢትዩጵያዊ ረዳቱ ጋር ለእስር የተዳረገው 4000 የአሜሪካ ዶላር በእጁ ይዞ በመገኘቱ ነው ሲል ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘግቧል  ፡፡ወደ አገር የሚገባ ማንኛውም የውጪ አገር ዜጋ በእጁ የሚገኘውን ገንዘብ ማሳወቅ የሚገባው ቢሆንም ሮቢን ወደ አገር ሲገባ ከገለጸው ገንዘብ በላይ ይዞ መገኘቱ ለእስሩ እንደምክንያት ተወስዷል፡፡
ሮቢን በ2007 በዚምባቡዌ በሁለት አጋጣሚዎች ለእስር ተዳርጎ ነበር፡፡የሮበርት ሙጋቤ አስተዳደር በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን ኢ ሰብአዊ ድርጊትና በአገሪቱ የተንሰራፋውን ድህነት በፎቶ ግራፉ ቀርጾ በማስቀረቱ ለ26 ቀናት ታስሮ በመጨረሻ አገሪቱን ለቅቆ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡በጋምቤላ ለእስር የተዳረገበትን ሁኔታየመንግስት ደጋፊዎች ከተናገሩት ውጪ ከገለልተኛ ወገን ማጣራት አልተቻለም ሲል ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘገባውን አጠናቋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials