Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, August 19, 2019

አይፈተሹም የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት መኪናዎች በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆሙ ተደርጓል።

አይፈተሹም የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት መኪናዎች በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆሙ ተደርጓል።
********
መተማ ላይ አምስት የመከላከያ መኪናዎች ወደሱዳን ለማለፍ ሲሞክሩ "አንፈተሽም" በማለታቸው ከሕዝቡ ጋር አለመግባባት ተፈጥሮ በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆሙ ተደርገዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት "ወደ ዳርፉር እየሄድን ነው" ቢሉም ማለፊያም ሆነ ወደ ዳርፉር የሚሄዱበትን ማስረጃ ማቅረብ አለመቻላቸው ተገልፆአል። የመኪናዎቹ ታርጋዎች እንዳይለዩ በግሪስ የተቀቡ መሆናቸው በሕዝብ ጥርጣሬ መፍጠሩን የአካባቢው ምንጮች ገልፀዋል።
የመከላከያ ሰራዊት አባላት መኪናዎቹ እንዲፈተሹ ባለመፍቀዳቸው ሕዝቡ ኬላ ዘግቶ አስቁሟቸዋል ተብሏል። እስካሁን ባለው ሁኔታ የአማራ ክልል ልዩ ኃይልም ሕዝቡ ያቀረበው ጥያቄ ትክክል መሆኑን መግለፁ ተነግሯል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials