Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, August 19, 2019

በፓሪስ ዝግ ያለው አስተናጋጅ በጥይት ተገደለ



በፈረንሳይዋ መዲና ፓሪስ አካባቢ በምትገኝ ቦታ ሳንድዊች እንዲያመጣ የታዘዘ አስተናጋጅ በፍጥነት አላመጣም በሚል የተናደደ ደንበኛ በጥይት ተኩሶ ገድሎታል።
ግድያው የተከሰተው አርብ እለት በምስራቃዊዋ ፓሪስ በምትገኘው ኖይሲ ለ ግራንድ ፣ ፒዛና ሳንድዊች መሸጫ ቦታ ነው።
ፖሊስ እንዳሳወቀው ተጠርጣሪው ወዲያው ከአካባቢው ተሰውሯልም ብሏል።

የአምቡላንስ ሰራተኞች ጀርባው አካባቢ በጥይት የተመታውን የ28 አመቱን አስተናጋጅ ለማዳን ጥረት ቢያደርጉም ቦታው ላይ ህይወቱ አልፏል ተብሏል።
የአስተናጋጁ የስራ ባልደረቦች እንደገለፁት ትእዛዙን ለማስተናገድ የወሰደበት ጊዜ ረዘም ያለ በመሆኑ ደንበኛው በከፍተኛ ሁኔታ ተበሳጭቶ ነበር ብለዋል።

ግድያው የሬስቶራንቱን ሰራተኞችን እንዲሁም የአካበባቢውን ነዋሪዎች በከፍተኛ ሁኔታ አስደንግጧል።
"በጣም አሳዛኝ ክስተት ነው። ከጥቂት ወራት በፊት የተከፈተችው ይህች ሬስቶራንት ፀጥ ረጭ ያለችና ምንም ችግር የሌለባት ነች" በማለት አንዲት የ29 አመት ግለሰብ ለፈረንሳይ ሚዲያ ተናግራለች።

አንዳንድ ነዋሪዎች በበኩላቸው በአካባቢው የወንጀል ተግባራት እየተበራከቱ ሲሆን በተለይም ከአደንዛዥ እፅ ዝውውርና ከመጠጥ ጋር ተያይዞ ችግሮች እንዳሉም ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials