Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, August 20, 2019

ኬንያዊቷ ሼፍ ለሰባ አምስት ሰአታት ያህል በማብሰል 'ሬኮርድ ሰበረች'

ለሰባ አምስት ሰዓታት ያህል ያለማቋረጥ ምግብ በማብሰል ኬንያዊቷ ማሊሃ ሞሃመድ የአለም የምግብ ማብሰል ሬኮርድን እንደሰበረች ተዘግቧል።
ማሊሃ ሞሃመድ
በባህር ዳርቻዋ በምትገኘው ቦምባሳ ተቀማጭነቷን ያደረገችው ማሊሃ መሀመድ ሙከራዋን የጀመረችው ጥዋት ሐሙስ አራት ሰዓት ላይ ነው።
ምግብ ማብሰሏ ለቀናትም ቀጥሎ እሁድ ሰባት ሰዓት ላይ አቁማለች።

የጊነስ ወርልድ ሬኮርድ የማጣራቱን ስራ ያልጨረሰ ሲሆን ከተረጋገጠም በአሜሪካዊው ምግብ አብሳይ ሪኪ ለምፕኪን ተይዞ የነበረውን የ68 ሰዓት ሬኮርድ ታሻሽላለች ተብሏል።
ማሊሃ አራት መቶ ያህል የኬንያና አለም አቀፍ ምግቦችን ካዘጋጀች በኋላ መጠለያ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ለግሳለች።
ያለማቋረጥ በሰራችባችው ሰባ አምስት ሰዓታት ውስጥ በየአስራ ሁለት ሰዓቱ ለሰላሳ ደቂቃ ያህል ብቻ አርፋለች።

የምግብ ማብሰሏን በድል ካጠናቀቀች በኋላ ለጋዜጠኞች እንደተናገረችው "ጉዞው አድካሚ ነበር። እግሮቼ እየተብረከረኩ ነው፤ አይኖቼም እንቅልፍ በማጣት ብዛት ይቆጠቁጡኛል። ነገር ግን ይህንን በማሳካቴ በጣም ደስተኛ ነኝ"

የሞምባሳ አስተዳዳሪ አሊ ሃሰን ጆሆ የ36 አመቷን ምግብ አብሳይ እንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላልፈውላታል።
በፌስቡካቸውም ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍም "ለሞምባሳና ለኬንያ ብቻ ሳይሆን መላው አፍሪካውያንን አኩርተሻል" ብለዋታል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials