Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 3, 2019

Pakistanni Diplomat stealing wallet የኩዌት ባለስልጣን በፓኪስታን ዲፕሎማት የኪስ ቦርሳቸው ተሰረቀ


የኩዌት ባለስልጣን በፓኪስታን ዲፕሎማት የኪስ ቦርሳቸው ተሰረቀ


CCTV footage purporting to show a senior bureaucrat (top right) taking a wallet from a table during a meeting in Islamabad



Asenior Pakistani civil servant sparked an embarrassing diplomatic incident when he was allegedly caught on CCTV stealing the wallet of a visiting Kuwaiti delegate.

The Kuwaitis made a complaint to Pakistani officials during a mission to discuss investment plans when one visitor said his wallet had gone missing during the meeting.

Officials searched the Economic Affairs Division of the finance ministry and frisked employees in the hunt for the wallet, Dawn, a leading Pakistani newspaper reported.

It was only when CCTV in the meeting hall was checked that a senior bureaucrat with the Pakistan Administrative Services was seen taking the wallet. A six-second clip said to show the incident was widely shared on social media. The clip showed a man taking a wallet from a conference table and putting it in his pocket.

The official reportedly denied involvement until he was confronted with the video and then produced the missing wallet.

Pakistani officials at first refused to tell their guests who the culprit was, until the furious Kuwaitis insisted and were shown the film.

Imran Khan


Sources in the ministry told the paper an internal inquiry was now underway against the bureaucrat and further action would be taken according to its conclusions.



Pakistan's new prime minister, Imran Khan, has long pledged to clean up government and has for years railed against the graft and corruption among senior politicians and officials.

When questioned about the incident, Fawad Chaudhry, information minister, told a press conference that most of the civil service had their “moral training” during the previous governments.


Image copyrightYOUTUBE

በፓኪስታን ከፍተኛ የመንግስት ተቀጣሪ የሆነ ሰው የኩዌት ልኡካን ቡድን አባል ያስቀመጠውን የኪስ ቦርሳ ሲሰርቅ የሚያሳይ ምስል ከተለቀቀ በኋላ ፓኪስታን በሰውዬው ላይ ምርመራ መጀመሯን አስታውቃለች።

ነገሩ ይባስ ብሎ በሃገር ውስጥ መገናኝ ብዙሃን እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጣሪው ዛራር ሃይደር ክሃን ይሄ ነው ተብሎ የተለቀቀው ምስል ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው በአሜሪካ የሚኖር ሰው ነው።

የፓኪስታን የመረጃ ሚኒስትሩ ፋዋድ ቻድሪይ እንዳሉት ተጠርጣሪው በሃገሪቱ የኢንዱስትሪና ምርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ሃላፊነት ያለው ተቀጣሪ ሲሆን፤ ሃገሪቱን የማይወክል ተግባር እንደሆነ ገልጸዋል።


የፓኪስታን መንግስት እንዳስታወቀው አቶ ሃይደር ከስራቸው ተሰናብተዋል፤ ተግባሩም መላው የሃገሪቱን ዜጎችና መንግስትን ያዋረደ ነው ብሏል።

በኩዌትና ፓኪስታን መካከል የንግድ ሁኔታዎችን ለመነጋገር ፓኪስታን የገባው ልኡካን ቡድን አባል የሆኑት ሰው የኪስ ቦርሳቸውን የተቀመጡበት ጠረጴዛ ላይ ትተውት የሄዱ ሲሆን፤ ተጠርጣሪውም የኪስ ቦርሳቸውን ሲያነሳ በተንቀሳቃሽ ምስል ተቀርጿል።

የኪስ ቦርሳቸው መጥፋቱን ያስተዋሉት የኩዌት ሃላፊም ጉዳዩን ለፓኪስታን ሃላፊዎች አሳውቀው፤ ተጠርጣሪው መታወቁን በሰሙ ጊዜም አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድና ማንነቱ እንዲነገራቸው ጠይቀዋል።



በቦርሳው ውስጥም ጠቀም ያለ የኩዌት ዲናር እንደነበረ አንድ የፓኪስታን ጋዜጣ ዘግቧል።

እጅግ በፈጠነ ሁኔታ ታዋቂነትን ያተረፈው የኪስ ቦርሳው ሲሰረቅ የሚሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል በሃገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችም ጭምር የታየ ሲሆን፤ ብዙ ፓኪስታናውያን አዋረደን በማለት ቁጣቸውን እየገለጹ ነው።

መልኩን በደንብ መለየት በማይቻለው ተንቀሳቃሽ ምስል ምክንያት ተጠርጣሪ ተብሎ ፎቶው በመገናኛ ብዙሃን የቀረበው ሰው ግን ዛራር ሃይደር ሳይሆን አሜሪካ ውስጥ የአደጋ መከላከል ባለሙያ የሆነውና ተቀራራቢ ስም ያለው ዛይድ ሃይደር ነው።

በተለይ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያዎች በተሰራጨው የተሳሳተ የዛይድ ሃይደር ምስል ስር ብዙ ፓኪስታናውያን ቁጣቸውን በስድብና አዋረድከን መልዕክቶች እየገለጹ ነው።

በጉዳዩ ዙሪያ የተጠየቀው የአሜሪካ ነዋሪው '' እኔ ምንም የማውቀው ነገር ነገር የለም፤ ስሜ ዛራር ሃይደር ሳይሆን ዛይድ ሃይደር ነው።'' ብሏል። እስካሁንም ግን የተጠርጣሪው ዛራር ሃይደር ትክክለኛ ምስል አልተገኘም።

በፓኪስታን የተንሰራፋውን የሙስና ችግር ለማጥፋት እዋጋዋለሁ ብለው ከሁለት ወራት በፊት የተመረጡት የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ክሃን ገና ከጅምሩ ያልጠበቁት አጋጣሚ ወዳጃቸው ኩዌትን አስቆጥቶባቸዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials