Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, May 17, 2019

ቦይንግ የ737 ማክስ ሶፍትዌርን አሻሽያለሁ አለ


ቦይንግ 737 ማክስ ሶፍትዌር ላይ እያደረገ የነበረውን ማሻሻያ መጨረሱን ይፋ አድርጓል። ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰከሰውን አውሮፕላን ጨምሮ በ737 ማክስ ሁለት የከፉ አደጋዎች መድረሳቸው ይታወሳል።
ቦይንግ የሶፍትዌር ማሻሻያ ባደረገባቸው 737 ማክስ አውሮፕላኖች 207 በረራ ማድረጉን አሳውቋል።

አብራሪዎች አውሮፕላኑን ስለሚቆጣጠሩበት መንገድ ለፌደራል አቪዬሽን አድሚንስትሬሽን (ኤፍኤኤ) መረጃ እንደሚሰጥም ተገልጿል። የኤፍኤኤ ባለሙያዎች ቦይንግ ማሻሻያው እንዲጸድቅለት መረጃውን በሚቀጥለው ሳምንት ለኤፍኤኤ እንዲያስረክብ ይጠብቃሉ።
መጋቢት ላይ ኢቲ 302 ቦይንግ 737 ማክስ ሲከሰከስ አውሮፕላኑን ተሳፍረው የነበሩ 157 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። ከኢቲ በፊት የኢንዶኔዥያው ላየን ኤር ተከስክሶ 189 ሰዎች መሞታቸውም አይዘነጋም።

ሁለቱም አደጋዎች በቦይንግ 737 ማክስ ችግር ምክንያት መከሰታቸው ተገልጿል። የተሻሻለው ሶፍትዌር የቦይንግ 737 ማክስ ላይ የነበረውን ክፍተት የሚሞላ ነው ተብሏል።
ቦይግን እንዳለው፤ አውሮፕላን አብራሪዎች እንዴት በተሻሻለው ሶፍትዌር እንደሚገለገሉ የሚጠቁም መረጃ ለኤፍኤኤ ከሰጠ በኋላ፤ የሙከራ በረራ ያደርጋል። ከዛም ማረጋገጫ ሰርተፍኬት እንደሚያገኝም ቦይንግ ገልጿል።
ባለፈው ወር ኢቲ 302 ቦይንግ 737 ማክስ ሲከሰከስ አውሮፕላኑን ተሳፍረው የነበሩ 157 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል

No comments:

Post a Comment

wanted officials