Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, May 12, 2019

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት የአፋር ሶስት ቀበሌዎች ይመለሱ ሲል ያሳለፈው ውሳኔ አግባብነት የሌለው ነው ሲል የአፋር ህዝብ ፓርቲ አስታወቀ


የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር ኮንቴ ሙሳ ከኢሳት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት ከሆነ ከሶማሌ ክልል ተወስደዋል የተባሉት ቀበሌዎች ድንበር ላይ ያሉ ሳይሆኑ 300 ኪሎ ሜትር ወደ አፋር ክልል የገቡ ናቸው።
ይህ ባለበት ሁኔታ አይነቱን ጥያቄ ማንሳት አግባብነት የሌለውና የህዝብን መብት የሚገፍ ነው ብለዋል።
ቀበሌዎቹ ምናልባትም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው መሆናቸውና ያ ጥቅማቸው የተነካባቸው ሰዎች የቀሰቀሱት ሊሆን ይችላሉም ብለዋል።
የአፋር አርብቶ አደር ሳይገደል ያደረበት ቀን የለም ያሉት ዶክተር ኮንቴ እንዲህ አይነቱ ኢሰብአዊ ድርጊት ሊቆም ይገባዋል ሲሉ ገልጸዋል።
ዶክተር ኮንቴ እንደሚሉት ከሆነ ዋናው ነገር የአካባቢው ሰላም ተጠብቆ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ እንዲጠናከር ሁሉም ወገኖች ችግሩን በሰላም ለመፍታት መጣር አለባቸው ብለዋል።
የሶማሌ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አማካሪ አቶ ጀማል ደርዬ በበኩላቸው እነዚህ ቀበሌዎች ያለህዝብ ይሁንታ ወደ አፋር ክልል እንዲካለሉ ተደርገዋል ነው ያሉት።
ይሄ ውሳኔ ደግሞ የህዝብ ቁጣን ቀስቅሷል በዚህም ምክንያት የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ወደዚህ ውሳኔ ተሸጋግሯል ብለዋል።
አሁን ላይ ግን በሁለቱ ክልሎች መካከል ችግሮች መፈጠራቸውንና እነዛን ችግሮች ለመፍታት ደግሞ ውይይቶች እየተካሄዱ ነው ብለዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials