Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, May 17, 2019

በደቡብ ሱዳን የምሽት ክለቦች ታገዱ

በደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ የሚገኙ የምሽት ክለቦች ሙሉ በሙሉ መታገዳቸውንና መጠጥ ቤቶች ላይ የሰአት እላፊ መጣሉን ቃል አቀባዩ ሜጀር ጀነራል ዳንኤል ጀስቲን ለቢቢሲ ኒውስ ደይ አሳውቀዋል።
" የምሽት ክለቦች ሙሉ በሙሉ እንዲዘጉ የተላለፈው ውሳኔ ተግባራዊ እየሆነ ነው። የከተማው ነዋሪዎች ለከተማው ምክር ቤት የምሽት ክለቦች እየረበሿቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲያማርሩ ነበር" ብለዋል።

የጁባ አስተዳዳሪ አውግስቲኖ ጃዳላ ዋኒ በበኩላቸው ከሳምንት በፊት በፌስቡክ ባስተላለፉት መልዕክት "ያልተገቡ" ተግባራትን ለመከላከል የምሽት ክለቦች እንዲዘጉና በመጠጥ ቤቶችም የሰአት እላፊ አዋጅ እንዲተላለፍ መወሰኑን አሳውቀው ነበር።

በሰአት እላፊው አዋጅ መሰረት መጠጥ ቤቶች የሚሰሩበት ሰአት ከቀኑ ስምንት ሰአት እስከ ምሽቱ 1 ሰአት ድረስ ብቻ እንደሆነ ሱዳን ትሪቢውን ዘግቧል።

ከዚህም በተጨማሪ በሆቴል መቆየት የሚፈልጉ ጥንዶች ባለትዳር መሆን የሚጠበቅባቸው ሲሆን የጋብቻ ማስረጃ ሰርቲፊኬትም ሊያሳዩ እንደሚገባም ተደንግጓል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials