Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, May 12, 2019

የሰባት የፖለቲካ ሃይሎች ውህደት የሆነው አዲሱ ፓርቲ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ በሚል ስያሜውን አጸደቀ።

አዲሱ ፓርቲ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ በሚል ስያሜውን አጸደቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 1/2011) የሰባት የፖለቲካ ሃይሎች ውህደት የሆነው አዲሱ ፓርቲ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ በሚል ስያሜውን አጸደቀ።

መስራች ጉባዔውን ዛሬ በአዲስ አበባ የጀመረው አዲሱ ፓርቲ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከ300 በላይ ወረዳዎች በተወከሉ የመስራች ጉባዔ አባላት መተዳደሪያ ደንብ፣ አወቃቀር እና አርማ ላይ ውሳኔ በመስጠት እየተካሄደ መሆኑን የመስራች ጉባዔው አስተባባሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል።
በድምጽ የሚሳተፉ 1200 የጉባዔ አባላት የአዲሱ ፓርቲ አመራሮችን ይመርጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ፓርቲው በማህበራዊ ፍትህ ላይ መሰረት በማድረግ የዜግነት ፖለቲካን እንደሚያራምድም በመስራች ጉባዔው ላይ ተገልጿል።
አቶ አንዱዓለም አራጌ የመስራች ኮሚቴ አባል ጉባዔው ታሪካዊ ነው ሲሉ ገልጸውታል።

ኢዜማ የፓርቲውን መሪዎች በመምረጥ ጉባዔውን አጠናቀቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2011) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ የፓርቲውን መሪዎች በመምረጥ የመስራች ጉባዔውን አጠናቀቀ።

የሰባት ፓርቲዎች ውህድ በመሆን የተመሰረተው ኢዜማ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የፓርቲው መሪ፣ አቶ አንዱዓለም አራጌን በምክትልነት መርጧል።
አቶ የሺዋስ አሰፋን የፓርቲው ሊቀመንበር፣ ዶክተር ከበደ ጫኔን ደግሞ በምክትል ሊቀመንበርነት መምረጡ ታውቋል።
ከ300 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመላክ በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ጉባዔውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ዜግነት ላይ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ መስመር እንደሚከተልም ይፋ አድርጓል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials