Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, January 28, 2019

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከአቶ ሙስጠፋ ኡመርና የአቶ አህምድ ሽዴ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት አስታውቋል::

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ኡመርና የኢትዮጲያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አህምድ ሽዴ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት አስታውቋል::

ዶ/ር አብይ ከሙስጠፋ ኡመር እና አህመድ ሺዴ ጋር ከስብሰባው በፊት የተነሱትን ፎቶ አድርጎ ባሰራጨው ዘገባው ዉይይቱም የተኮረው በሶማሌ ክልል ልማትና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ሲሄን ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድም የክልሉን ልማት የበለጠ በማጠናከር ረገድ አቅጣጫ ሰጥተዋል ሲል ጽህፈት ቤቱ ጠቅሷል::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች በበኩላቸው ስብሰባው እንዳልተጠናቀቀና እስከነገ ድረስ እንደሚቀጥል ገልጸውልናል::  በዚህ ስብሰባ ላይ 11 አባላት ያሉት የሶማሌ ክልል ባለስልጣናት የተገኙ ሲሆን ስብሰባው እንዳለቀ መረጃ እንደሚያቀብሉን ቃል ገብተውልናል:: እንደደረሰን መረጃውን ለዘ-ሐበሻ ቤተሰቦች እናደርሳለን::

No comments:

Post a Comment

wanted officials