Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, January 26, 2019

መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብሱን ሊቀይር ነው

መከላከያ ሰራዊት የመለያ ደንብ ልብስ በመልበስ በሰራዊቱ ስም ወንጀል የሚፈፅሙ አካላትን ለመቆጣጠር የአባላቱን የመለያ ደንብ ልብስ የቀለምና የዲዛይን ለውጥ ሊያደርግ ነው፡፡

የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሜጀር ጀነራል አብዱራህማን እስማኤል ለመንግስት ሚዲያዎች ዛሬ እንደተናገሩት ደረጃውን የጠበቀ የደንብ ልብስ ለመለወጥ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ ፋውንዴሽኑ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በተሰጠው ስልጣን መሰረት ለሰራዊቱ አልባሳትና ሌሎች ወታደራዊ ግብዓቶችን አምርቶ ወይም ገዝቶ የሚያቀርብ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የሚለወጠው የደንብ ልብስ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሚወዱት፣ በጥራት፣ በቀለምና በዲዛይን የተሻለ የመለያ ልብስ እንዲሆን ከተለያዩ አገሮች ተመክሮ መወሰዱን ገልጸዋል። የመከላከያ ጥናትና ምርምር ማዕከል ሃላፊ ብርጋዴር ጀኔራል ተሾመ ገመቹ በበኩላቸው የመከላከያ ሰራዊቱን አልባሳት መልበስ የሚችለው የሰራዊቱ አባል ብቻ መሆኑን ጠቁመው ይሁንና ተገቢ ቁጥጥር ባለመደረጉ የማይመለከታቸው ግለሰቦች ሲለብሱት መታየቱን ጠቁመዋል፡፡ አዳዲስ አልባሳት በሚቀርቡበት ወቅት አሮጌዎቹ በአግባቡ ሳይወገዱ በመቅረታቸው ልብሱ በማይመለከታቸው አካላት እጅ እየገባ የሰራዊቱን ስምና ክብር የሚያጎድፉ የተለያዩ ወንጀሎች እየተፈጸሙበት መሆኑን ገልጸዋል። የመከላከያ ሰራዊቱን የመለያ ደንብ ልብስ በመልበስ ወንጀል የሚፈጽሙ አካላት ካሉ በወንጀል እንደሚጠየቁ ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials