Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, August 25, 2017

በመላ ኦሮሚያ የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።

በመላ ኦሮሚያ የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
ሱቆቹ ፣ የገበያ ማዕከሎች፣ መደብሮች ፣ የግል የንግድ ባንኮች ሁሉም ዝግ ናቸው። ምንም አይነት የትራንስፓርት እንቅስቃሴ የለም ማንኛውም ተሽከርካሪ ቁሟል።
ወደ ኦሮሚያ የሚገቡ ሆነ የሚያልፉ ፣ወደ አዲስ አበባ የሚሄዱ ተሽከርካሪወች በወታደራዊ አጀብ ማለፋ ያልቻሉት በየመንገዱ ቁመው ምሽቱን እየጠበቁ ይገኛል።
አባይን ተሻግሮ ያሉ የአማራ ከተሞች በሁለት አበይት አቅጣጫወች የነፃነት ትግሉን ለመቀላቀል ተዘጋጂተዋል። ምንም አይነት የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ የማይችለው እብሪተኛው የህውሓት ወያኔ ቡድን በህዝባዊ አመፅ እና ህዝባዊ እምቢተኝነት ስርዓቱን የቆመበትን የህዝብ ጭንቃ ላይ ለማውረድ ማሽመድመድ እንደሚቻላ በጥቂት አመት ውስጥ ያየነው እውነት ነው። የወያኔ አምባገነን ስርዓት ለኢትዩጲያ ህዝብ አያስፈልግም። የስርዓት ለውጥ ይፈልጋል ይሄም በተግባር እምቢ በማለት ከአፈሙዝ ታጣቂወች ጋር እየተፋለመ ይገኛል ። እጂግ ብዙ ምክንያቶች የስራ ማቆም አድማ እንድናደርግ በቂ ናቸው።
እንዳጠቃላይ የስርዓቱን እድሜ ለማሳጠር ሁሉም በጋራ እንዲነሳ ዛሬም ባለመሰልቸት የትግላችን አካል እንሁን።
ነፃነት በነፃ አይገኝም !!
አንድነት ለአንድ ወያኔ ጠላት!!

No comments:

Post a Comment

wanted officials