Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, July 15, 2017

በኦሮሚያ ትክክለኛ ባልሆነ የግብር ተመና የተነሳው ህዝባዊ አመፅ እና አድማ እየተደረገ ነው ።

በኦሮሚያ ትክክለኛ ባልሆነ የግብር ተመና የተነሳው ህዝባዊ አመፅ እና አድማ እየተደረገ ነው ።
በአምቦ አውቶብስ መናህሪያ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አይታይም ፤ወደ ተለያዩ ቦታወች የሚሄዱ ቢኖሩም ትራንስፓርት ባለመኖሩ እንዲቆዩ ተገደዋል።
በጊንጪ ከተማ ላይ ወደ አምቦ ፤ ጀልዱና ግንደበረት የሚወስደው መንገድ ዝግ ነው:: ከጊንጪ ወደ አንቦ ትራንስፓርት የለም። ሱቆች ዝግ ናቸው። ባንኮች በተጨማሪ ልዩ ወታደሮች እየተጠበቁ ነው።ሁሉም ነገር ዝግ ነው ።በከተማዋ ወጣቶች ተሰባስበው ቁጣቸውን እየገለፁ ሲሆን በሌላ በኩል የፌደራል ፖሊሶች ከተማዋን አንዳንድ ቦታወች ይሯሯጣሉ ። ህዝባዊ ጥያቄን በአፈሙዝ ለምልፈን እየተንቀሳቀሰ ያለው እና አንድ እግሩ መቃብር ውስጥ የገባው የህወሓት ቡድን ወጣቶቹን ለማስቆም የሀይል እርምጃ ለመውሰድ አሰፍስፈዋል።
በዶዶላ ከተማ በተመሳሳይ ውጥረት አለ። ህዝባዊ ቁጣው ፈንድቷል። የወያኔ ወንበዴ ቡድን በተለያዩ ተሽከርካሪወች ወደ ኦሮሚያ ከተሞች ተጨማሪ ወታደራዊ ሃይል እያስገባ ነው።
ህዝብ ምንጊዜም ያሸንፉል!!

No comments:

Post a Comment

wanted officials