Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, November 11, 2017

በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ

(ኢሳት ዜና–ጥቅምት 30/2010)በቅርቡ ስልጣን በለቀቁት በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢሳት ምንጮች ገለጹ።

በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ ከተገነባው ደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ የተጀመረው ምርመራ ሙሉ በሙሉ የሆቴሉ ግንባታ የገንዘቡ ምንጭ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህም የተፈጸመው በአቶ በረከት ስምኦን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሊቀመንበርነት ግዜ እንደሆነ መረጋገጡን ምንጮቹ ጨምረው ገልጸዋል።
በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ መቀጠሉን ነው የኢሳት ምንጮች የገለጹት።
በምርመራውም በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የደብል ትሪ ሆቴል የገንዘብ ምንጭም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑና አቶ በረከት የቦርድ ስብሳቢ በነበሩበት ጊዜ የተፈጸመ መሆኑንም አረጋግጧል።
የደብል ትሪ ሆቴል ባለቤት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋውም የዳሽን ባንክ ቦርድ ሰብሳቢ ቢሆኑም ለዚህ ሆቴል ግንባታ በሚል ከዳሽን ባንክ ምንም አይነት ብድር እንዳልወሰዱም ታውቋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር በዋናነት እንዲሰጥ የተቀመጠውን የመንግስት ፖሊሲ በመጻረር ብድሩ እንደተለቀቀም ለማወቅ ተችሏል።
በዋናነት በአምራችነትና በወጭ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ብድር እንዲሰጥ በፖሊሲ ደረጃ አቅጣጫ የተቀመጠለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሆቴሉ ግንባታ የሚውለውን ወጪ መቶ በመቶ ማበደሩንም ምርመራው አረጋግጧል።
በቅድሚያ ሁለት መቶ ሚሊየን፣በቀጣይ ደግሞ 100 ሚሊየን ብር በአጠቃላይ 300 ሚሊየን ብር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወጪ የሆነው በአቶ በረከት ስምኦን ትዕዛዝና በባንኩ ፕሬዝዳንት በአቶ በቃሉ ዘለቀ አስፈጻሚነት እንደሆነም ለኢሳት የደረሰው ማስረጃ ያሳያል።
ባንኩ ብድር ከመልቀቁ በፊት ተበዳሪው 30 በመቶ መነሻ ማቅረብ እንዳለበት ተደንግጓል።
በዚህ ሆቴል ግንባታ ግን ከተበዳሪው ወገን አንድም ሽራፊ ሳንቲም እንዳልቀረበና መቶ በመቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገንዘብ ሆቴሉ መገንባቱን ምርመራው አረጋግጧል።
የኢሳት ምንጮች የምርመራ ቡድን አሁንም ስራውን መቀጠሉን አስታውቀዋል።
መቀሌ የተጀመረው የሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ስብሰባ ላይ እነ አቶ አባይ ወልዱ መልሰው የበላይነታቸውን ካላረጋገጡ በአቶ በረከት ላይ የተጀመረው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በመገናኛ ብዙሃን ይፋ እንደሚደረግም ምንጮቹ ጨምረው ገልጸዋል።
አንዳንድ ወገኖች እንደሚሉት በአቶ በረከት ስምኦን ላይ ከደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ በዚህ ወቅት ምርመራ የተጀመረው የሆቴሉ ባለንብረት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት ስለሚወዳደሩ የሕወሃት ሰዎች የእርሳቸውን ተቀናቃኝ የሕወሃቱን ተክለወይኒ አሰፋን ለማስመረጥ የሚደረግ ማሸማቀቅ ሊሆን ሲሉ ስጋታቸውን ይገልጻሉ።
ንብረትነቱ የአቶ በረከት ስምኦን በሚል ምርመራ የተጀመረበት፣ በአለም አቀፍ ደረጃ የተገነባውና በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የሚገኘው ደብል ትሪ ሆቴል በመጪው ሰኔ ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።
ጠቅላላ ወጪው 300 ሚሊየን ብር የፈጀው ደብል ትሪ ሆቴል ባለ 11 ፎቅ ሲሆን 106 መኝታ ክፍሎች እንዳሉትም ታውቋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials