Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, December 1, 2018

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሊቨርፑል ደጋፊዎች ደረሰላቸው



በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ውድድር ዛሬ ምሽት ሊቨርፑልና ሪያል ማድሪድ ኬቭ ላይ ይፋለማሉ፡፡
የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜን ውድድር ለመከታተል ደጋፊዎች በዩክሬን ዋና ከተማ ኬቭ መከተማቸው ተነግሯል፡፡
የዘንድሮውን የቻምፒየንስ ሊግ ውድድር ሪያል ማድሪድ የሚያነሳ ከሆነ ለአስራ ሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፥ እንዲሁም ለሶስት ተከታታይ ዓመታት ለማሸነፍ ነው የሚፋለመው፡፡
ሊቨርፑል ዋንጫውን የሚያነሳ ከሆነ ደግሞ በታሪኩ ለስድስተኛ ጊዜ ያነሳ ተብሎ ታሪክ ይጻፍለታል፡፡
አስገራሚው ዜና ይህ ነው:: ዛሬ ቅዳሜ ምሽት በኪየቭ ዩክሬን ለሚደረገው የሻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ውድድር፣ የሊቨር ፑል ደጋፊዎች የሚወስዳቸው አውሮፕላን እጥረት ተፈጥሮ ነበር። ነገር ግን በከተማውና በቡድኑ ጥረት ለሚታወቁ አየር መንገዶች ኮንትራት በመስጠት ጉዞውን ለማቀላጠፍ ጥረት ተደርጓል። በዚህ መሰረት ከተመረጡት መካከል የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንዱ ሆኖ፣ የሊቨርፑል ደጋፊዎችን ዛሬ ዓርብ ጠዋት ከሊቨርፑሉ ጆን ሌኖን አየር ማረፊያ ኪየቭ ዩክሬን ድረስ አመላልሷል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሊቨርፑል ደጋፊዎች ደረሰላቸው ተብሏል::
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ 100 አውሮፕላን በመጨመር ከአፍሪካ ቀዳሚነቱን አረጋግጧል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials