Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, December 1, 2018

የምትመለከቱት አፅም በአንጎለላ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን የሚገኝ የፊታውራሪ ገበየሁ ነው።



ይሄ ክቡር የሆነ አፅም አንተ ሰው ሆነህ በሰውነትህ እንድትኮራ የተከሰከሰልህ አፅም ነው።የአፅሟ ፍንካች የነጻነት ምልክት ናት።ጫት ይዘህ መፈረሻ ላይ እንደ ድመት ስትድበለበል ከመዋል፥ጃቦ ከምትገለብጥ መፅሐፍ ግዛና አንብብ!!
ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) በ25 አመቱ ጀብድ የፈጸመ ብላቴና ነበር።
"ያ ጎራው ገበየሁ
አላጌ በሩ ላይ ማልዶ ቢገጥማቸው
ለምሳም ሳይደርሱ ቁርስ አደረጋቸው"ተብሎ የተገጠመላቸው ፊታውራሪ ገበየሁ በእንዳ ኪዳነ ምህረት በኩል የመጣውን እና በጄኔራል አልበርቶኒ የሚመራውን የጠላት ጦር አፈር ደም አስግጠው ለእናት ሀገሩ በለጋ ዕድሜው የተሰዋ አጸበራቂ ኮኮብ ነበር።
ከዓድዋ ድል በኋላ በጃንሜዳ የጦር አበጋዞች በፈረስ ሲያልፉ የፊታውራሪ ገበየሁ አባ ጎራው ፈረስ ብቻውን ከፊት ሲያልፍ ያዩት አፄ ምኒልክ ተንሰቅስቀው ያለቀሱት ገብርዬን እንዳአጡት አጼ ቴዎድሮስ ያን ትንታግ የ25 አመቱን ወጣት ገበየሁን በማጣታቸው ነው።
የምትመለከቱት አፅም በአንጎለላ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን የሚገኝ የፊታውራሪ ገበየሁ ነው።

No comments:

Post a Comment

wanted officials